هذه الخدمة مُتوفّرة أيضًا بلغتك. لتغيير اللغة، اضغطEnglish
Best analytics service

Add your telegram channel for

  • get advanced analytics
  • get more advertisers
  • find out the gender of subscriber

all posts ዳጉ-ጆርናል/Dagu-Journal

The best fiction is far more true than any journalism 📢 ተዓማኒ የመረጃ ምንጭ ፤ ለሙያው ስነምግባር ተገዢ በሆኑ ጋዜጠኞች ብቻ 👉 በፌስቡክ ገፆቻችን  https://www.facebook.com/simon.dereje.56  👉  https://www.facebook.com/mik0Man  
عرض المزيد
40 690-8
~5 990
~18
19.62%
تقييم تيليجرام العام
عالميًا
29 690المكان
من 78 777
223المكان
من 396
في الفئة
1 938المكان
من 3 169
أرشيف المنشورات
1 572
1
በሙስና ወንጀል ሲፈለግ የነበረው ተጠርጣሪ ከተደበቀበት ሆቴል ውስጥ በቁጥጥር ስር ዋለ!! በሙስና ወንጀል ተጠርጥሮ ሲፈለግ የነበረ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ልደታ ክፍለ ከተማ የመሬት ልማት ጽ/ቤት ተወካይ ኃላፊ አቶ ቴዎድሮስ ፀጋዬ በስካይ ላይት ሆቴል በቁጥጥር ሥር መዋሉ ተገልጿል። ግለሰቡ የኮሪደር ልማትን ሽፋን በማድረግ ከመንግሥት አሠራር እና ውሳኔ ውጪ በመደራደር ባልተገባ መንገድ የግል ጥቅም ለማግኘት ሲል የካሳ ግምት በማናር ውስን የሆነውን የሕዝብ እና የመንግሥትን መሬት ለግለሰቦች አሳልፎ በመስጠት ተጠርጥሮ ሲፈለግ እንደነበር የተገለጸ ሲሆን በትላንትናው ዕለት ከተሸገሽገበት እስካይ ላይት ሆቴል ተይዟል። ተጠርጣሪው እስከ ዛሬ ተሸሽጎ የቆየው “ከሀገር ውጪ ወጥቷል” የሚል ማጭበርበሪያ በማስነገር የሕግ ማስከበር ሒደቱ እንዲስተጓጎል በማድረግ እንደሆነ ነው የተገነረው። ተጠርጣሪው ኃላፊነት ላይ በነበረበት ወቅት በልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 4 ውስጥ በኮሪደር ልማት ፕላን ልማት ውስጥ የማይካተቱ 6 የመኖሪያ እና አንድ የንግድ ቤት “ዋይልድ አፓርትመንት” ከተባለ ሕንፃ ባለቤት ጋር በመመሳጠር፣ ከመመሪያ እና አሠራር ውጪ ቤቶቹ እንዲፈርሱ በማድረግ ለሕንፃው ማስፋፊያ እንዲውል መስጠቱ ተገልጿል። የመንግሥት ቤት ውስጥ ይኖሩ የነበሩ ግለሰቦች የዕቃ ማጓጓዥያ ሳይከፈል እንዲነሡ በማድረግ እንዲሁም ምትክ ቦታ እስጣችኋለው፤ ቦታ አስቀይርላችኋለው እና የተለያዩ የማጭበርበር ወንጀሎችን በመፈፀም ኅብረተሰቡን ሲያደናግር እና ያልተገቡ ጥቅሞችን ሲያጋብስ እንደነበረም የአዲስ አበባ የፀረ-ሙስና ግብረ ኃይል ማስታወቁን ከአዲስ አበባ ኮሙዩኒኬሽን ቢሮ የተገኘው መረጃ ያመለክታል። ምንጭ:- AMN
عرض المزيد ...
2 605
14
ቀያይ ሰይጣኖቹ ነጥብ ተጋሩ በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ማንቼስተር ዩናይትድ እና ክሪስታል ፓላስ ያደረጉት ጨዋታ በአቻ ውጤት ተጠናቋል፡፡ በኳስ ቁጥጥር ማንቼስተር ዩናይትድ ተሽሎ በተገኘበት ጨዋታ ምንም ጎል ሳይቆጠር በአቻ ውጤት ተጠናቅቋል፡፡
5 144
1
Attention | በጊዜያዊነት አገልግሎት ይቋረጣል የተከበራቹሁ የባንካችን ደንበኞች ዛሬ ከለሊቱ 06፡00 ሰዓት እስከ ነገ ከጠዋቱ 12፡00 ሰዓት ድረስ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሲቢኢ ብር አገልግሎት በጊዜያዊነት አገልግሎት ይቋረጣል። ለሚፈጠረው የአገልግሎት መቋረጥ ከልብ ይቅርታ እንጠይቃለን። በዚህ ጊዜ ውስጥ ለሚኖርዎት ትዕግስት እያመሰገንን፤ በሎሎች የዲጂታል አማራጮች የሚፈልጉትን አገልግሎት ማግኘት የሚችሉ መሆኑን እናሳውቃለን።
5 976
12
የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ውጤቶች ጎሎች 👉
5 280
0
በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ውጤቶች ዌስትሀም 0-3 ቼልሲ ⚽️⚽️ኒኮላስ ጃክሰን ⚽️ኮል ፓልመር ቼልሲ ከሜዳ ውጪ ሶስት ጨዋታዎች ድል ማድረግ ችሏል 💪🔵 ሊቨርፑል 3-0 ቦርንመውዝ ⚽️⚽️ሉዊስ ዲያዝ ⚽️ዳርዊን ኑኔዝ ጎሎች 👉
5 925
3
በሀረር ከተማ ቁማር ሲጫወቱ የነበሩ 13 ግለሰቦች በሚስቶቻቸው ጥቆማ በቁጥጥር ስር ዋሉ በግሮሰሪ ቤት ውስጥ በር ዘግተው ቁማር ሲጫወቱ  የነበሩ ግለሰቦች የገዛ የትዳር አጋሮቻቸዉ እና ቤተሰቦቻቸዉ በሰጡት ጥቆማ በቁጥጥር  ስር መዋላቸው ተሰምቷል፡፡ በሀረር ከተማ ጀኒላ ወረዳ ቀበሌ 16 መጠጥ ቤት  በር ዘግተው ቁማር ሲጫወቱ የነበሩ 13 ግለሰቦች እጅ ከፍንጅ በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የጂኒላ ወረዳ ፖሊስ አዛዥ የሆኑት ኮማንደር ሙፍቲ  ከድር  በተለይም ለብስራት ሬዲዮ እና ቴሌቪዥን ተናግረዋል። ግለሰቦቹ ከፍተኛ ገንዘብ እያስያዙ ቁማር ሲጫወቱ የነበረ ሲሆን ባለቤቶቻቸው እንዲሁም ከቤተሰቦቻቸው ለፖሊስ በደረሰ ጥቆማ በቁጥጥር  ስር ሊውሉ መቻላቸው ተገልጿል ። በቁጥጥር ስር በዋሉበት ሰዓት ሰላሳ ሺህ ስምንት መቶ ብር እጅ ከፍንጅ  ተይዟል። ቁማር ከሚጫወቱት ግለሰቦች መካካል አብዛኛዎቹ ለፖሊስ የጠቆሙት የትዳር  አጋሮቻቸው ሲሆኑ ለቤተሰባቸው ትልቅ ችግር እንዲሁም ለኑሯቸው እንቅፋት  ሆኖባቸው እንደነበረ ተረጋግጧል። ይህንን ድርጊት ለመከላከል ፖሊስ ከማህበረሰቡ  ጋር በመተባበረ  እርምጃ የመውሰድ ስራ እንደሚሰራ ኮማንደር ሙፍቲ ከድር ጨምረው ለብስራት ሬዲዮ እና ቴሌቪዥን ተናግረዋል ። በኤደን ሽመልስ
عرض المزيد ...
5 805
8
✅ በ አይነቱ ልዩ የሆነ በ ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ 4 ትልቅ ለውጥን መፍጠር የሚችሉ የ ስራ ዘርፎችን ልክ እንደ ግራፊክስ ዲዛይን ቪዲዮ ኤዲቲንግ ዲጂታል ማርኬቲንግ እና አኘ ወርክ በ አንድ ላይ ያካተተ ስልጠና ተጀመረ። 📌 ይሄ ስልጠና መቀመጫውን አሜሪካ አና አዚው ሀገራችን ላይ ባደረጉ ለውጥ ፈጣሪ ትውልደ ኢትዮጵያውያን የተቋቋመ ዘውድ ቴክ በተባለ ድርጅት የተዘጋጀ ነው። 📌 ባለፈው ሳምንት ቅዳሜ በማዶ ሆቴል የዘውድ ቴክ የስራ አጋሮች እና ታዋቂ የሚዲያ ሰዎች በተገኙበት መክፈቻ ፕሮግራምም ተካሂዱዋል። 📌 ዘዉድ ቴክ በኢትዮጵያ የመጀመሪያ ያስባለው የ 25/75% ክፍያ ያመቻቸ ሲሆን  አንድ ሰልጣኝ ለመመዝገብ ዘውድ ቴክ ከሚጠይቀው ክፍያ ላይ 25% ብቻ ከፍሎ ሙሉ የ 3ወሩን ስልጠና የሚወስድ ሲሆን የተቀረውን 75% የሚከፍለው በዘውድ ቴክ በኩል በሚመቻችለት የስራ እድል ከዛላ ከሚያገኘው ገቢ በ አመት ውስጥ እየከፈለ የሚጨርስ ይሆናል 📌ስልጠናውን ላጠናቀቀ certificate እንዲሁም ነፃ የ ኢንተርናሽናል ክፍያ መፈፀምያ ማስተር ካርድ የሚያገኝ ይሆናል 📌ስልጠናው ሙሉ በሙሉ ኦንላይን እንደመሆኑ ማንኛውም ሰው ከትምህርት እና ስራ ሰዓት በኋላ መማር ይችላል። ⚠️ያለው ቦታ ውስን ስለሆነ ከታች በተቀመጠው ሊንክ የዘውድ ቴክ ቻናልን ተቀላቅላችሁ እዛ ላይ የሚገኘውን የስልጠና ገለፃ ቪድዮ ተመልክታችሁ ባሉት ስልክ ቁጥሮች መደወል እና መልዕክት ማስቀመጥ ትችላላችሁ። 👇የዘውድ ቴክ ቻናልን ለመቀላቀል መልካም እድል!
عرض المزيد ...
5 581
3
የ15 ዓመት ታዳጊን ለአራት በመሆን የአስገድዶ መድፈር ወንጀል የፈፀሙ ተከሳሾች በእስራት ተቀጡ በኮንታ ዞን አመያ ዙሪያ ወረዳ ኦፓላሼ ቀበሌ ለአራት በመሆን የ15 ዓመት ታዳጊን አስገድዶ መድፈር ወንጀል የፈፀሙ ተከሳሾች በእስራት ተቀጡ። ተከሳሾች በቁጥር አራት ሲሆን አስፋቸው አለሙ፣ አሻግሬ አበራ፤  ማቲዎስ ደዋና እና አስማማው አሉላ የተባሉ ግለሰቦች ናቸው። ግለሰቦቹ በአመያ ዙሪያ ወረዳ በግምት 8:00 አካባቢ  ጫሬ ዶቄ ቀበሌ ቤተሰብ ለመጠየቅ ወደ ኦፓላሼ ቀበሌ እየሄደች የምትገኝ የ15 አመት ታዳጊ አስገድደው መድፈራቸውን የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች  ክልል ፖሊስ ኮሚሽን የህዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር ኢንስፔክተር ደጀኔ አሰፋ ለብስራት ሬዲዮ  እና  ቴሌቪዥን ተናግረዋል ። በአስገድዶ መድፈር ወንጀል ጥፋተኛ ሆነው ክስ የቀረበባቸው ወንጀለኞች ጳግሜ 5 ቀን 2016 ዓ.ም  በዋለው ችሎት ከ1ኛ እስከ 3ኛ ተከሳሾች እያንዳንዳቸው 7 ዓመት ፅኑ እስራት  ተቀጥተዋል። አራተኛ ተከሳሽ ዕድሜው ከ10 እስከ 13 ዓመት በመሆኑ ተከሳሹ  መታሰር የማይችልና እንደዚህ ዓይነት ታዳጊ እስረኞችን ተቀብሎ   በማረምያ ተቋም በዞኑ ባለመኖሩ ምክንያት ቤተሰቡ ፈርሞ ወስዶት ክትትልና በቁጥጥር እንዲያደርግ በማለት ውሳኔ መሰጠቱን ኢንስፔክተር ደጀኔ አሰፋ ለብስራት ሬዲዮ  እና  ቴሌቪዥን ተናግረዋል ። በሳምራዊት ስዩም
عرض المزيد ...
7 445
17
የደራሲ ሃዲስ አለማየሁ ወራሾች ለ"ፍቅር እስከ መቃብር" ፊልም ሥርጭት እግድ ለዋስትና የተጠየቁትን ገንዘብ ካልከፈሉ ድራማዉ አይቋረጥም የደራሲ ሃዲስ አለማየሁ ወራሾች ለ"ፍቅር እስከ መቃብር" ፊልም ሥርጭት እግድ ለዋስትና የተጠየቁትን ገንዘብ ካልከፈሉ በኢቢሲ የሚተላለፈው የፊልሙ ሥርጭት እንደማይታገድ ዋዜማ ተረድታለች። የፌደራሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ይህን ውሳኔ የሰጠው፣ የደራሲው ወራሾች የፊልሙ ሥርጭት ባስቸኳይ እንዲቆም ያቀረቡትን አቤቱታ ከመረመረና የኢቢሲንና ዋልታን ምላሽ ካዳመጠ በኋላ ነው። ፍርድ ቤቱ፣ በፊልሙ ሥርጭት ላይ እገዳ ሊጣል የሚችለው፣ ከሳሾች ፊልሙ በመቋረጡ ለሚደርሰው ኪሳራ ዋስትና የሚኾን ገንዘብ ገቢ ካደረጉ በኋላ እንደሚኾን ገልጧል።
8 565
16
ሸገር ከተማ መነ አቢቹና ሱሉልታ ክፍለ ከተሞች ለኮሪደር ልማት በርካታ የመኖሪያና ንግድ ቤቶች ያለምንም ካሳና ተለዋጭ ቦታ እንዲፈርሱ ተወስኗል ተባለ በኦሮሚያ ክልል ሸገር ከተማ መነ አቢቹና ሱሉልታ ክፍለ ከተሞች ለኮሪደር ልማት በርካታ የመኖሪያና ንግድ ቤቶች ያለምንም ካሳና ተለዋጭ ቦታ እንዲፈርሱ የተላለፈውን ውሳኔ ተከትሎ፣ ባለ ይዞታዎች ከፍተኛ ስጋት ላይ መውደቃቸውን ለዋዜማ ተናግረዋል። ከይዞታቸው እንደሚነሱ የተነገራቸው ነዋሪዎች፣ በቱፋ ሙና፣ ወሰርቢ እና አባገዳ ወረዳዎች የሚገኙ ናቸው። የክፍለ ከተሞቹ ሠራተኞችና ጸጥታ ኃይሎች ያለ ቅድመ ማስጠንቀቅያ፣ ምልክት ሲያደርጉ እንደሰነበቱና ትናንት በከፊል ማፍረስ እንደጀመሩ ዋዜማ ሰምታለች። ከሚፈርሱት ይዞታዎች መካከል፣ ነዳጅ ማደያዎች፣ ባንኮች፣ ግንባታ ላይ ያሉ ሕንጻዎችና ሆቴሎች ይገኙበታል ተብሏል።
8 349
20
ትራንስፖርት ቢሮው አዲስ የስምሪት ውሳኔውን እንዲቀር ማድረጉን ገለጸ ቢሮው ከትምህርት መከፈት ጋር ተያይዞ ሊፈጠሩ የሚችሉ መጨናነቆችን ለመቀነስ የተወሰኑ የከተማዋ መስመሮች ለብዙሀን ትራንስፖርት አግልግሎት ብቻ ክፍት እንዲሆኑ ወስኖ ነበር ትራንስፖርት ቢሮው አዲስ የስምሪት ውሳኔን እንዲቀር ማድረጉን ገለጸ። የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ ከትምህርት መከፈት ጋር ተያይዞ ሊፈጠሩ የሚችሉ የትራፊክ መጨናነቆችን ለመቀነስ የተወሰኑ የከተማዋ መስመሮች ለብዙሀን ትራንስፖርት አግልግሎት ብቻ ክፍት እንዲሆኑ ወስኖ ነበር። በአዲስ አበባ ለብዙሀን ትራንስፖርት ብቻ አገልግሎት የሚሰጡ 14 መስመሮች ይፋ ሆኑ ቢሮው አሁን ከመሸ ባወጣው መግለጫ ይህን ውሳኔውን እንዲቀር አድርጎታል። እቅዱ ከባለድርሻ አካለት ጋር ውይይት እስከሚደረግበት ድረስ የትራንስፖርት እንቅስቃሴው ባለበት ይቀጥላል ብሏል ቢሮው። ትራንስፖርት ቢሮው ቀደም ሲል ባወጣው መግለጫ የብዙሃን ትራንስፖርት አገልግሎት እንዲሰጡ 14 መስመሮችን ይፋ አድርጎ ነበር። ለብዙሃን ትራንስፖርት አገልግሎት እንዲሰጡ ተለይተው የነበሩት መስመሮች ከቦሌ- ፒያሳ፣ ከቦሌ- ሜክሲኮ፣ ከቦሌ- አራት ኪሎ፣ ከቦሌ አውቶቢስ ተራ፣ ከቦሌ- ሽሮሜዳ፣ ከጀሞ- ፒያሳ እና ከጀሞ- ሜክሲኮ፣ ከፒያሳ- ቦሌ፣ ከሜክሲኮ- ቦሌ፣ ከአራት ኪሎ- ቦሌ፣ ከአውቶቡስ ተራ- ቦሌ፣ ከሽሮ ሜዳ- ቦሌ፣ ከፒያሳ ጀሞ እና ከሜክሲኮ - ጀሞ ነበሩ። የብዙሃን ትራንስፖርት ከ8 ሰው በላይ መያዝ የሚችሉ ተሽከርካሪዎችን የሚያጠቃልል ነው።
عرض المزيد ...
8 730
24
በሀረር ከተማ ወርቅ ሰርቀው ሲሸጡ በተፈጠረ አለመግባባት ፀብ ውስጥ የገቡ ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ዋሉ በሀረር ከተማ ሁለት ግለሰቦች ከድሬዳዋ ከተማ ወርቅ መሸጫ መደብር ዉስጥ ወርቅ ሰርቀው በመሸጥ በገንዘብ ክፍፍል በተፈጠረ አለመግባባት በተፈጠረ ፀብ ፖሊስ በቁጥጥር ስር ሊያውላቸው ችሏል። የሀረሪ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን የህዝብ ግንኙነት እና የኮሙኒኬሽን ፅህፈት ቤት ሀላፊ ኮማንደር ጣሰው ቻለው  እንደገለፁት በሀረር ከተማ አንደኛ መንገድ ተብሎ በሚጠራ ስፍራ ሁለት ግለሰቦች በፈጠሩት አለመግባባት ከፍተኛ ፀብ ፈጥረው ድብድብ ውስጥ በመግባታቸው በጥበቃ እንቅስቃሴ ላይ በነበሩ የፖሊስ አባላት ሁለቱን ግለሰቦች በማገላገል በቁጥጥር ስር አውለው ወደ ፖሊስ ጣቢያ ይዘዋቸው እንደሄዱ ገልፀዋል። ፖሊስም ሁለቱን ግለሰቦች በቁጥጥር ስር አውሎ ወደ ፖሊስ ጣቢያ ከወሰዳቸው በኋላ የፀባቸው መንስኤ ሲያጣራ እና የያዙት ቦርሳ ሲፈትሽ በቦርሳው ውስጥ ሰባ አራት ሺህ የኢትዮጵያ ብር ሊገኝ ችሏል።ፖሊስ ብሩን ከየት እንዳመጡት በምርመራ ሂደት ሲጠይቃቸው ከድሬዳዋ ከተማ 17.62 ግራም ወርቅ ከ አንድ የወርቅ መሸጫ መደብር ሰርቀው በመውሰድ ሀረር ከተማ አንደኛ መንገድ ከሚገኝ አንድ ወርቅ ቤት በ መቶ ሺህ የኢትዮጵያ ብር መሸጣቸው ሊያረጋግጥ ችሏል። ሁለቱም ግለሰቦች ከሽያጩ ላይ ሀያ ስድስት ሺህ ብር ደግሞ ማታ አብረዋቸው ሲዝናኑ እና ለሊቱን አብረዋቸው ካሳለፉ ሁለት የሆቴል ቤት እንስቶች እንደሰጧቸው ለፖሊስ ተናግረዋል። ፖሊስ ሁለቱን የሆቴል ቤት እንስቶች በቁጥጥር ስር አውሎ አስራ ሰባት ሺህ አምስት መቶ ብር ከደበቁበት በፍተሻ ማግኘት መቻሉን ገልፀዋል።በአጠቃላይ በሁለቱ ግለሰቦች እና ከሁለቱ እንስቶች ዘጠና አንድ ሺህ አምስት መቶ ብር ከተጠርጣሪዎቹ በቁጥጥር ስር የዋለ ሲሆን የስርቆት ወንጀሉን የፈፀሙት ከድሬደዋ ከተማ ፖሊስ ከሀረር ከተማ ፖሊስ ጋር በጥምረት በመሥራት በአስቸኳይ ለፍትህ እንደሚያቀርባቸው ኮማንደር ጣሰው   ቻለው ጨምረው ገልፀዋል።በሌላ በኩል በሀረር ከተማ ለኮሪደር ልማት ተብሎ በተቆፈረ ጉድጓድ ውስጥ ንብረት እየሰረቁ የሚያከማቹ ግለሰቦች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የጂኔላ ፖሊስ አስታውቋል። የጂኔላ ወረዳ ፖሊስ አዛዥ  ኮማንደር  መሱድ ከድር እንደገለፁት በሀረር ከተማ  ጂኔላ ወረዳ ቀበሌ 16 አካባቢ ሁለት ግለሰቦች ለኮሪደር ልማት ተብሎ የተቆፈረው ጉርጎድ ውስጥ ሁለት ባለ 43 ኢንች ፍላት ቴሌቭዥን ሁለት ባለ 32 ኢንች ቴሌቭዥን፣ ሁለት የዲሽ ሪሲቨር ዘርፈው በመውሰድ ሶፊ ወረዳ  ደከር ትምህርት ቤት በሚጠራው አካባቢ ለኮሪደር ልማት የተቆፈረ ጉድጎድ ውስጥ  እንደሚያጠራቅሙ በህብረተሠቡ በደረሰ ጥቆማ በቁጥጥር ስር ሊውሉ ችለዋል። ሁለቱ ግለሰቦች ለኮሪደር ልማት የተቆፈረውን ጉርጓድ ለስርቆት መጠቀሚያ በማድረግ በርካታ እቃዎችን በጨለማ እየሰረቁ በጉርጎድ ውስጥ እየደበቁ እያወጡ ሲሸጡ እንደነበረ የተናገሩት ኮማንደሩ ኮማንደር መሱድ ከድር  ህብረተሰቡ ለኮሪደር ልማት ተብሎ የተቆፈሩ ጉርጓዶችን በመጠበቅ የስርቆት ወንጀልን እንዲከላከል ኮማንደር  የሱፍ  ከድር ጨምረው ገልፀዋል። ሰመዓል አለባቸዉ
عرض المزيد ...
8 004
7
በቦረና ዞን 99 ኪሎ ግራም አደንዛዥ እፅ በሞተር ብስክሌት ሲጓጓዝ በቁጥጥር ስር ዋለ በቦረና ዞን በጎምቦሌ ወረዳ በሞተር ብስክሌት ሲጓጓዝ የነበረ 99 ኪሎ ግራም አደንዛዥ እፅ በቁጥጥር ስር መዋሉን የወረዳዉ ፖሊስ ፅህፈት ቤት አስታዉቋል፡፡ የጎምቦሌ ወረዳ ፖሊስ አዛዥ ተወካይ ምክትል ኢንስፔክተር ዮናስ ዳሊስ ለብስራት እንደተናገሩት መስከረም 7 ቀን 2017 ዓ.ም ከለሊቱ 7 ሰአት ላይ ሞተር ብስክሌት በመጠቀም 99 ኪሎ ግራም ካናቢስ የተሰኘ አደንዛዥ እፅ ከምዕራብ ጉጂ ዞን ወደ ቦረና ዞን ጎምቦሌ ወረዳ ሲጓጓዝ ቱላ ዋዩ ቀበሌ በተደረገዉ ድንገተኛ ፍተሻ በቁጥጥር ስር መዋሉን ተናግረዋል፡፡ በቁጥጥር ስር የዋለዉ 99 ኪሎ ግራም ካናቢስ የተሰኘዉ እፅ በሞተር ብስክሌት በድብቅ ሲጓጓዝ ህብረተሰቡ ለፖሊስ በሰጠዉ ጥቆማ መሰረት በቁጥጥር ስር የዋሉ በመሆኑ ማህበረሰቡ የአደንዛዥ እፅ ዝዉዉር በሀገር ላይ የሚያስከትለዉን የወንጀል ቀዉስ ተረድቶ አዘዋዋሪዎችን አጋልጦ ለፀጥታ አካላት እየሰጠ እንደሚገኝ ምክትል ኢንስፔክተር ዮናስ ዳሊስ  ገልፀዋል፡፡  ካናቢስ የተሰኘዉን 99 ኪሎ ግራም አደንዛዥ እፅ በሞተር ብስክሌት ሲያጓጉዙ የነበሩ ግለሰቦች የምርመራ መዝገባቸዉ ተጣርቶ በቅርብ ቀን በአስቸካይ ለፍትህ እንደሚቀርብ ተመላክቷል፡፡ በመባ ወርቅነህ
عرض المزيد ...
7 855
5
በ“ኬጂ” ደረጃ ተቋርጦ የነበረው የእንግሊዘኛ ቋንቋ ትምህርት በድጋሚ ሊሰጥ ነው! ባለፈው ዓመት ተቋርጦ የነበረው የቅድመ መደበኛ (ኬጂ) የእንግሊዘኛ ቋንቋ ትምህርት፤ በዚህ ሳምንት በተጀመረው የ2017 ዓ.ም. የትምህርት ዘመን በሳምንት ለአምስት ጊዜ ሊሰጥ ነው።የአዲስ አበባ ከተማ ትምህርት ቢሮ ለቅድመ መደበኛ ትምህርት ያዘጋጀው የእንግሊዘኛ ቋንቋ የተማሪዎች መፅሐፍ እና የመምህራን መምሪያ ለመንግሥት ትምህርት ቤቶች መሠራጨቱን ቢቢሲ ያነጋገራቸው ርዕሰ መምህራን እና መምህራን ገልጸዋል። ሕጻናት ወደ አንደኛ ክፍል ከመሸጋገራቸው አስቀድሞ ባለው ቅድመ መደበኛ ደረጃ ለሚማሩ ተማሪዎች ሲሰጥ የነበረው የእንግሊዘኛ ትምህርት የተቋረጠው፤ በ2016 ዓ.ም. አዲስ ሥርዓተ ትምህርት (ካሪኩለም) መተገበር በመጀመሩ ነበር።ለመጀመሪያ ጊዜ የተዘጋጀው የቅድመ መደበኛ ሥርዓተ ትምህርት፤ ከዚህ ቀደም ለ“ኬጂ” ተማሪዎች ትምህርት ሲሰጥ የነበረበትን መንገድ የቀየረ ነው።አዲሱ ሥርዓተ ትምህርት፤ የቅድመ መደበኛ ትምህርት በሌሎች ደረጃዎች እንደሚደረገው ሒሳብ፣ ሳይንስ፣ ቋንቋ በሚሉ የትምህርት ዓይነቶች እንዳይከፋፈል ያደረገ ነው።
عرض المزيد ...
7 601
8
📱🌼Broz mobile and computer 🌼📱 🍏Original iPHONE, Samsung & Tab  አዳዲስ እንዲሁም ያገለገሉ ስልኮችን በተመጣጣኝ ዋጋ እና ያሎት ስልክ ላይ በመጨመር ከበቂ ዋስትና  እና ጥገና ጋር  እኛው  ጋር  ያገኛሉ ። Telegram Channel ቀድመው ይደውሉ 👇 Contact us ☎️      251911120707      251904818881 📍ቦሌ መድሃኒአለም
7 297
0
እስከ መስከረም 15 ሃብታቸውን ለማስመዝገብ ፈቃደኛ በማይሆኑ አመራርና ሰራተኞች ላይ እርምጃ  ይወሰዳል ተባለ በአዲስ አበባ የንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ሰራተኞች፣ ቡድን መሪዎችና አመራሮች በሙሉ ሃብታቸውን ማስመዝገብ እንዳለባቸው የክፍለ ከተማው የስነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ቡድን አስታውቋል ። የአዲስ አበባ ስነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን በሃብት ማሳወቂያና ማስመዝገቢያ አዋጅ ቁጥር 668/2002 የተዘጋጀ ማኑዋልን መሰረት በማድረግ በክፍለ ከተማው የሚገኙ  ሰራተኞች፣ ቡድን መሪዎችና አመራሮች እስከ መስከረም 15 ቀን 2017 ዓ.ም ድረስ ሃብታቸውን ማስመዝገብ እንዳለባቸው ተጠቁሟል። በተጠቀሰው የጊዜ ገደብ ውስጥ ሃብቱን ያላስመዘገበ አካል 1000 ብር ቅጣት ከፍሎ በ5 ቀናት ውስጥ ማስመዝገብ እንደሚቻል ተገልጿል ። ይሁን እንጂ ሃብቱን ለማስመዝገብ ፈቃደኛ ያልሆነ ሰው በወንጀል የሚጠየቅና እንደ መስሪያ ቤቱ አስተዳደር ውስጠ ደንብ መሰረት አስተዳደራዊ እርምጃ  እንደሚመወሰድ ተገልጿል ። ሰራተኞችና አመራሮች ለተጨማሪ ወጪ እንዲሁም ቅጣት እንዳይዳረጉ በተቀመጠው የጊዜ ገደብ በክፍለ ከተማው በሚገኘው የስነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ቡድን ክፍል በመገኘት ሃብታቸውን ማስመዝገብ እንደሚገባ ተገልጿል ።
عرض المزيد ...
7 312
9
✅ በ አይነቱ ልዩ የሆነ በ ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ 4 ትልቅ ለውጥን መፍጠር የሚችሉ የ ስራ ዘርፎችን ልክ እንደ ግራፊክስ ዲዛይን ቪዲዮ ኤዲቲንግ ዲጂታል ማርኬቲንግ እና አኘ ወርክ በ አንድ ላይ ያካተተ ስልጠና ተጀመረ። 📌 ይሄ ስልጠና መቀመጫውን አሜሪካ አና አዚው ሀገራችን ላይ ባደረጉ ለውጥ ፈጣሪ ትውልደ ኢትዮጵያውያን የተቋቋመ ዘውድ ቴክ በተባለ ድርጅት የተዘጋጀ ነው። 📌 ባለፈው ሳምንት ቅዳሜ በማዶ ሆቴል የዘውድ ቴክ የስራ አጋሮች እና ታዋቂ የሚዲያ ሰዎች በተገኙበት መክፈቻ ፕሮግራምም ተካሂዱዋል። 📌 ዘዉድ ቴክ በኢትዮጵያ የመጀመሪያ ያስባለው የ 25/75% ክፍያ ያመቻቸ ሲሆን  አንድ ሰልጣኝ ለመመዝገብ ዘውድ ቴክ ከሚጠይቀው ክፍያ ላይ 25% ብቻ ከፍሎ ሙሉ የ 3ወሩን ስልጠና የሚወስድ ሲሆን የተቀረውን 75% የሚከፍለው በዘውድ ቴክ በኩል በሚመቻችለት የስራ እድል ከዛላ ከሚያገኘው ገቢ በ አመት ውስጥ እየከፈለ የሚጨርስ ይሆናል 📌ስልጠናውን ላጠናቀቀ certificate እንዲሁም ነፃ የ ኢንተርናሽናል ክፍያ መፈፀምያ ማስተር ካርድ የሚያገኝ ይሆናል 📌ስልጠናው ሙሉ በሙሉ ኦንላይን እንደመሆኑ ማንኛውም ሰው ከትምህርት እና ስራ ሰዓት በኋላ መማር ይችላል። ⚠️ያለው ቦታ ውስን ስለሆነ ከታች በተቀመጠው ሊንክ የዘውድ ቴክ ቻናልን ተቀላቅላችሁ እዛ ላይ የሚገኘውን የስልጠና ገለፃ ቪድዮ ተመልክታችሁ ባሉት ስልክ ቁጥሮች መደወል እና መልዕክት ማስቀመጥ ትችላላችሁ። 👇የዘውድ ቴክ ቻናልን ለመቀላቀል መልካም እድል!
عرض المزيد ...
6 478
14
በአዲስ አበባ ለብዙሃን ትራንስፖርት ብቻ አገልግሎት የሚሰጡ መስመሮች ይፋ ሆኑ ከትምህርት ቤቶች መከፈት ጋር ተያይዞ የትራፊክ መጨናነቅ እንዳይፈጠር የብዙሃን ትራንስፖርት አገልግሎት ከመጪው እሑድ ጀምሮ በተመረጡ መስመሮች ላይ ተግባራዊ እንደሚደረግ የከተማዋ ትራንስፖርት ቢሮ አስታውቋል።መስመሮቹም ከቦሌ- ፒያሳ፣ ከቦሌ- ሜክሲኮ፣ ከቦሌ- አራት ኪሎ፣ ከቦሌ- አውቶቢስ ተራ፣ ከቦሌ- ሽሮሜዳ፣ ከጀሞ- ፒያሳ እና ከጀሞ- ሜክሲኮ መሆናቸው ተገልጿል፡፡ በተመሳሳይ ከፒያሳ- ቦሌ፣ ከሜክሲኮ- ቦሌ፣ ከአራት ኪሎ- ቦሌ፣ ከአውቶቡስ ተራ- ቦሌ፣ ከሽሮ ሜዳ- ቦሌ፣ ከፒያሳ ጀሞ እና ከሜክሲኮ - ጀሞ የብዙሃን ትራንስፖርት አገልግሎት ብቻ መሰጠት እንደሚጀምር ተመላክቷል፡፡ቢሮው " የአገልግሎቱ መጀመር የመንገድ መዘጋጋቱን ለመቀነስ እና ብዙ የሰው ቁጥር ያለው ተጓዥ በአንድ ጊዜ ማመላለስ ያስችላል " ብሏል። በዚህም ተማሪና መምህራን ብሎም ሌሎች ተገልጋዮች በሰዓታቸው ወደ ሚፈልጉት ቦታ በመንቀሳቀስ አገልግሎት እንዲያገኙ ያግዛል ተብሏል፡፡" በከተማዋ ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴው የተነቃቃ እንዲሆን ጉልህ አስተዋጽኦ ያበረክታል " ሲልም አክሏል። ዜጎች የሚያጋጥሟቸውንና የሚስተዋሉ ችግሮችን በአቅራቢያ ለሚገኙ የትራንስፖርት ቁጥጥር ሰራተኞች ወይም በ9417 ነፃ የስልክ መስመር ጥቆማ እንዲሰጡ ተጠይቋል፡፡
عرض المزيد ...
7 239
13
በዩክሬን ጦርነት ከ70 ሺ በላይ የሩሲያ ወታደሮችና ወዶ ገብ ተዋጊዎች መገደላቸው ተሰማ በቢቢሲ የተተነተነ መረጃ እንደሚያሳየው ከ 70,000 በላይ ሰዎች በሩሲያ ጦር ውስጥ እየተዋጉ በዩክሬን መገደላቸውን አመላክቷል። በጎ ፈቃደኛ ተዋጊዎች እና ጦርነቱ ከተጀመረ ወዲህ ወደ ጦር ሰራዊቱ የተቀላቀሉ ሲቪሎች ላይ በ 2022 ሩሲያ ሙሉ ወረራ ከጀመረ ወዲህ ከፍተኛውን የሞት ቁጥር ተመዝግቧል ። በየእለቱ በዩክሬን የተገደሉት ሰዎች ስም፣ የቀብር ስነ ስርዓታቸው እና ፎቶግራፎች በመላው ሩሲያ በመገናኛ ብዙሃን እና በማህበራዊ አውታረመረቦች ላይ ይታተማሉ። ቢቢሲ ረስኪ እና ሚድያዞና የተባለው ገለልተኛ ድህረ ገጽ እነዚህን ይፋ የሚደረጉ ስሞች ከሌሎች ምንጮች ጋር በማከል መረጃ አጋርተዋል።መረጃው የሟቾችን ሪፖርት ወይም የሟች ዘመዶች ያካፈሉት መሆኑን እና በጦርነቱ ውስጥ እንደሞቱ የተረጋገጡ ናቸው። አዳዲስ መቃብሮች በዩክሬን የተገደሉትን ወታደሮች ስም ለማወቅ አግዘዋል። ብዙውን ጊዜ በመከላከያ ሚኒስቴር በተላኩ ባንዲራዎች እና የአበባ ጉንጉኖች በሟቾች ላይ ምልክት ይደረግባቸዋል ።በዩክሬን የተገደሉትን የ 70 ሺ 1 መቶ 12 የሩስያ ወታደሮችን ስም ለይተናል ነገር ግን ትክክለኛው ቁጥር ከተገለፀውም እጅግ ከፍ ያለ ነው ተብሎ ይታመናል። አንዳንድ ቤተሰቦች የዘመዶቻቸውን ሞት በአደባባይ ይፋ የማያደርጉ በመሆናቸው በትንታኔው የተገለፀው ቁጥር ከዚህ የላቀ ነው። ይህ የሟቾች ቁጥር በዩክሬን ምሥራቃዊ ክፍል በራሺያ የተያዙትን የዶኔትስክ እና ሉሃንስክ ግዛቶች ውስጥ የተገደሉትን የታጣቂዎች ቁጥር አያካትትም። ከሟቾቹ መካከል 13 ሺ 7 መቶ 81 ያህሉ ወይም 20 በመቶ ገደማ በጎ ፈቃደኛ ተዋጊዎች ናቸው። የበጎ ፈቃደኛ ተዋጊዎች ሞት ከሌሎች የውጊያ አውድማ ውስጥ ካሉት በልጧል። ለወንጀላቸው ይቅርታ እንዲደረግላቸው የተቀላቀሉት የቀድሞ እስረኞች ሞት ቀደም ሲል ከፍተኛው ነበር። ነገር ግን አሁን ከተረጋገጡት ሞት 19 በመቶ ያህል ድርሻ አላቸው። ከጦርነቱ በፊት ከሩሲያ ጦር የተቀነሱ ወታደሮች ዳግም ለመዋጋት ከተጠሩት መካከል ከሟቾች ድርሻ 13 በመቶ ይይዛሉ። ካለፈው አመት ጥቅምት ወር ጀምሮ በየሳምንቱ የበጎ ፈቃደኞች ሞት ከ100 በታች አልተመዘገበም። በአንዳንድ ሳምንታት ከ310 በላይ የሩሲያ ጦር የበጎ ፈቃደኞች ሞት ተመዝግቧል። በግንባር ቀደምትነት ከሚሞቱት አብዛኞቹ በጎ ፈቃደኞች መካከል እድሜያቸው ከ42 እስከ 50 ዓመት የሆኑ ሲሆን በተጠቀሰው የእድሜ ክልል ውስጥ ያሉ ቁጥራቸው 4,100 ያህል ወንዶች ህልፈት ተመዝግቧል። በጦርነቱ የተገደሉት አንጋፋው በጎ ፈቃደኛ የሩሲያ ጦር አባል የ71 ዓመት አዛውንት ሲሆኑ በአጠቃላይ ከ60 ዓመት በላይ የሆናቸው 250 በጎ ፈቃደኞች በጦርነቱ ተገድለዋል።ዩክሬን በጦር ሜዳ ላይ ስለሞቱባት ወታደሮች የሞት መጠን በይፋ አስተያየት አትሰጥንም ። በየካቲት ወር ፕሬዚዳንቱ ቮሎዲሚር ዘለንስኪ 31,000 የዩክሬን ወታደሮች መገደላቸውን ቢናገሩም በአሜሪካ የስለላ ድርጅት መረጃ ላይ የተመሰረቱ  ግምቶች ግን ከዚህ የበለጠ ኪሳራ ዩክሬን እንደደረሰባት ይጠቁማል። በስምኦን ደረጄ
عرض المزيد ...
7 299
1
7 094
0
በ2016 ዓመት ብቻ በክፍያ መንገዶች ላይ 651 የትራፊክ አደጋዎች ደርሰዋል አደጋዎቹ የደረሱት ኢንተርፕራይዙ በሚያስተዳድራቸው የክፍያ መንገዶችን በሆኑ አዲስ አበባ-አዳማ ፣ ድሬደዋ-ደወሌ እና የሞጆ-ባቱ መንገዶች ላይ መሆኑን የኢትዮጵያ ክፍያ መንገዶች ኢንተርፕራይዝ አስታውቋል። የኢንተርፕራይዙ የኮሙኒኬሽን ባለሙያ አቶ ስንታየው መኮንን ለብስራት ሬዲዮ እና ቴሌቪዥን እንደተናገሩት ኢንተርፕራይዙ በሚያስተዳድራቸው ሶስቱ መንገዶች በደረሱት 651 የትራፊክ አደጋዎች 47 ሰዎች ሲሞቱ  169 ሰዎች ላይ ከባድ እና 352 ደግሞ ቀላል አደጋዎች ደርሰዋል። በደረሱት የትራፊክ አደጋዎቹ በሚሊየን የሚቆጠር ንብረት መውደሙ ታውቋል። ለአደጋዎቹ መከሰት ዋና ዋና ተብለው ከተቀመጡት ምክንያቶች መካከል የቴክኒክ ችግር ያለባቸው ተሽከርካሪዎች ፣ ከፍጥነት ወሰን በላይ ማሽከርከርና የአሽከርካሪዎች የስነምግባር ጉድለት ዋና ዋና መሆናቸው አቶ ስንታየው ጨምረው ነግረውናል ፡፡ አሁን ያለንበት የክረምት ወቅትም በመሆኑ ወደ ፈጣን መንገዶች የሚገቡ አሽከርካሪዎች የትራፊክ መመሪያዎችን ተግባራዊ እንዲያደርጉ እና ፍጥነታቸው እንዲቆጣጠሩ አሳስበዋል፡፡ በትግስት ላቀው
عرض المزيد ...
7 862
2
ባለፈዉ ዓመት ህይወታቸዉ ባለፈዉ ቢሊየነሩ ሞሃመድ አል ፋይድ የአስገድዶ መደፈር ጥቃት ተፈጽሞብናል ያሉ ሴቶች ቅሬታ አቀረቡ አምስት ሴቶች በለንደን የቅንጦት ምርቶች መሸጫ መደብር ውስጥ ሲሰሩ በቀድሞው የሃሮድስ አለቃ መሀመድ አል ፋይድ እንደተደፈሩ ተናግረዋል ።ባለፈው አመት በ94 አመታቸው ከዚህ አለም በሞት የተለዩት ቢሊየነሩ አስገድዶ መድፈርን ጨምሮ ጾታዊ ጥቃት የፈጸሙባቸዉ ሴቶች ቁጥር ከ20 በላይ እንደሚደርስ የቀድሞ ሰራተኞች ምስክርነታቸውን ተሰምቷል። ከ 20 በላይ ጥቃት የደረሰባቸዉ ሴቶች ሁሉም የፋይድ የቀድሞ ሰራተኞች የነበሩ ሲሆን ወሲባዊ ጥቃት እና በደል እንዳይጋለጥ ተሸፋፍኖ መቆየቱን ተናግረዋል፡፡የቅንጡ መደብሩ የአሁን ባለቤቶች በክሱ "በጣም መደናገጣቸዉን በመግለጽ" ተጎጂዎችን ይቅርታ ጠይቀዋል። እ.ኤ.አ. በ2010 ሃሮድስን የሸጠው ፋይይድ ባለፈው አመት በ94 አመቱ ከዚህ አለም በሞት ተለይቷል። ዘ ጋርዲያን ላይ በሟች ህይወት ላይ በቀረበዉ መጽሃፍ በሴት ሰራተኞች ላይ የፆታዊ ትንኮሳ ተደጋጋሚ ክሶች እንደነበሩ ተናግሯል። በስምኦን ደረጄ
عرض المزيد ...
7 409
4
የኢትዮጵያን የሻይ ቅጠል ምርት 99 በመቶ የምትገዛዉ እንግሊዝ መሆኗ ተነገረ ኢትዮጵያ በተጠናቀቀው የ2016 በጀት አመት 1ሺህ 1መቶ 42 ቶን  የሻይ ምርትን ለውጪ ገበያ በመላክ 2.3 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር ገቢ ማግኘት ችላለች ሲል የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታውቋል:: በባለስልጣኑ የህዝብ ግንኙነትና የኮሚኒኬሽን ስራ አስፈፃሚ አቶ ሳህለማርያም ገብረ መድህን ለብስራትu ሬዲዮና ቴሌቪዥን እንደተናገሩት አፈጻጸሙ ከባለፈው በጀት ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ከተላከው ጋር ሲነጻጸር የተሻለ ገቢ የተገኘበት ነው::በመጠን  ደረጃ 2መቶ 92.43 ቶን  እና በገቢ 0.33 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ጭማሪ ተመዝግቧል ያሉት አቶ ሳህለ ማርያም ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የ50 ሺህ ቶን ብልጫ እንዳለው ተናግረዋል:: ምንም እንኳን በበጀት አመቱ ከሻይ ምርት ወጪ ንግድ የተሻለ ገቢ  ማግኘት ቢቻልም ኢትዮጵያ  ካላት አቅም አንጻር  ግን ብዙ መሥራት የሚጠይቅ ነው ሲሉ ጨምረው ለጣቢያችን ተናግረዋል።ኢትዮጵያ ለሻይ ምርት ምቹ የሆነ የአየር ጸባይና የአፈር ሁኔታ ያላት አገር ብትሆንም ባለኃብቶች በዘርፉ በስፋት ባለመሳተፋቸው ማግኘት ያለባትን የውጭ ምንዛሬ እንዳታገኝ እንቅፋት ሆኖባታል ተብሏል። አያይዘዉም በአሁኑ ወቅት የሻይ ቅጠል ምርትን የማስፋት ሥራ በስፋት እየተከናወነ ይገኛል ብለዋል፡፡ምርቱን ለማስፋት 460 ሚሊዮን ችግኞችን በማባዛት በ2016 በጀት ዓመት 30 ሺህ ሄክታር የሚሸፍን የሻይ ቅጠል ምርት ተተክሏል፡፡ ቀደም ሲል በኢትዮጵያ በቀዳሚነት ተጠቃሽ የሆነው የውሽውሽና ጉመሮ ምርት በ5 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ ብቻ ያረፈ ነበር ሲሉ የገለፁት አቶ ሳህለ ማርያም በዚህም እስካሁን ከሻይ ቅጠል የሚገኘው የውጭ ምንዛሬ በዓመት ከ3 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር የሚበልጥ አልነበረም ነው ያሉት ። ከሻይ ምርት ወጪ ንግድ የሚገኘውን ገቢ ለማሳደግ በኦሮሚያ ክልል ቀደም ሲል በተበታተነ መልኩ ይካሄድ የነበረውን የሻይ ተከላ ስራ  ከ2014 በጀት ዓመት ጀምሮ በክላስተር ደረጃ ማምረት ተጀምሯል ሲል ባለስልጣኑ አስታውቋል፡፡ ኢትዮጵያ 99 በመቶ የሚሆነውን የሻይ ምርት ወደ እንግሊዝ ትልካለች፡፡ በቅድስት ደጀኔ
عرض المزيد ...
7 877
3
ተወዳጇ ከያኒ አዜብ ወርቁ ከግማሽ ቀን እስር በኃላ ተፈታች አሁን በስልክ ደውዬ አጣርቻለሁ። ትላንት በቁጥጥር ስር ውላ የነበረችው አዜው ወርቁ ለግማሽ ቀን ያህል በእስር ከቆየች በኋላ ከጥቂት ደቂቃዎች በፊት መለቀቋን ከቤተሰቦቿ ለማረጋገጥ ችያለሁ። Via ያሬድ ሹመት
8 051
4
ዴቪድ ራያ በዚህ የቶማስ ፓርቴ ስህተት የተገኘውን የፍፁም ቅጣት ምት ፤  ሬቴጊዪ ቢመታትም ያውም ሁለቴ ማዳን ችሏል 🔥 ተመልከቱ 👉
8 337
2
ላሚን ያማል የመጀመሪያውን የሻምፒዮንስ ሊግ ጎሉ አስቆጥሯል 🌟 ይኸውም በሻምፒዮንስ ሊግ ታሪክ ከአንሱ ፋቲ በመቀጠል ሁለተኛው ወጣት ግብ አስቆጣሪ ያደርገዋል 👶 ጎሉን 👉
8 329
2
አንሄል ዲ ማሪያ በ15ኛ የሻምፒዮንስ ሊግ ተሳትፎው አሁንም የጨዋታው ኮከብ ሽልማቱን እየተቀበለ ይገኛል 👏
8 234
2
ኤሪክ ጋርሲያ ሚናሚኖ ላይ በሰራው ጥፋት በቀጥታ በቀይ ካርድ ወጥቷል 😳 ይህ የሆነው በጋርሲያ እና ግብ ጠባቂው ቴር ስቴገን መካከል ያለመግባባት በመፈጠሩ በተገኘ አጋጣሚ ነበር ... ግቦችን ለመከታተል 👉
7 826
2
✅ በ አይነቱ ልዩ የሆነ በ ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ 4 ትልቅ ለውጥን መፍጠር የሚችሉ የ ስራ ዘርፎችን ልክ እንደ ግራፊክስ ዲዛይን ቪዲዮ ኤዲቲንግ ዲጂታል ማርኬቲንግ እና አኘ ወርክ በ አንድ ላይ ያካተተ ስልጠና ተጀመረ። 📌 ይሄ ስልጠና መቀመጫውን አሜሪካ አና አዚው ሀገራችን ላይ ባደረጉ ለውጥ ፈጣሪ ትውልደ ኢትዮጵያውያን የተቋቋመ ዘውድ ቴክ በተባለ ድርጅት የተዘጋጀ ነው። 📌 ባለፈው ሳምንት ቅዳሜ በማዶ ሆቴል የዘውድ ቴክ የስራ አጋሮች እና ታዋቂ የሚዲያ ሰዎች በተገኙበት መክፈቻ ፕሮግራምም ተካሂዱዋል። 📌 ዘዉድ ቴክ በኢትዮጵያ የመጀመሪያ ያስባለው የ 25/75% ክፍያ ያመቻቸ ሲሆን  አንድ ሰልጣኝ ለመመዝገብ ዘውድ ቴክ ከሚጠይቀው ክፍያ ላይ 25% ብቻ ከፍሎ ሙሉ የ 3ወሩን ስልጠና የሚወስድ ሲሆን የተቀረውን 75% የሚከፍለው በዘውድ ቴክ በኩል በሚመቻችለት የስራ እድል ከዛላ ከሚያገኘው ገቢ በ አመት ውስጥ እየከፈለ የሚጨርስ ይሆናል 📌ስልጠናውን ላጠናቀቀ certificate እንዲሁም ነፃ የ ኢንተርናሽናል ክፍያ መፈፀምያ ማስተር ካርድ የሚያገኝ ይሆናል 📌ስልጠናው ሙሉ በሙሉ ኦንላይን እንደመሆኑ ማንኛውም ሰው ከትምህርት እና ስራ ሰዓት በኋላ መማር ይችላል። ⚠️ያለው ቦታ ውስን ስለሆነ ከታች በተቀመጠው ሊንክ የዘውድ ቴክ ቻናልን ተቀላቅላችሁ እዛ ላይ የሚገኘውን የስልጠና ገለፃ ቪድዮ ተመልክታችሁ ባሉት ስልክ ቁጥሮች መደወል እና መልዕክት ማስቀመጥ ትችላላችሁ። 👇የዘውድ ቴክ ቻናልን ለመቀላቀል መልካም እድል!
عرض المزيد ...
7 301
42
ሊባኖስ ፔጀርስን፣ ዎኪ-ቶኪዎችን በሁሉም በረራዎች ላይ ጥቅም ላይ እንዳይዉሉ አገደች የሊባኖስ የሲቪል አቪዬሽን ዋና ዳይሬክተር ተሳፋሪዎች በማንኛውም አውሮፕላን ላይ ፔጀር እና ዎኪ ቶኪዎችን ይዘዉ እንዳይሳፈሩ የሚያግድ አዲስ መመሪያ ማውጣቱን የመንግስት የዜና ወኪል ኤን ኤን ዘግቧል።እገዳው በቤሩት ራፊክ ሃሪሪ አለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በሚያልፉ ጭነት ፣የሚፈተሹ እና በእጅ ሻንጣዎች ላይ የሚተገበር ሲሆን የአየር ማረፊያው ጥበቃ እነዚህን መሳሪያዎችን ይዞ የተገኘ ማንኛውንም መንገደኛ ይወርሳል። አዲሱ ህግ ወዲያውኑ ተግባራዊ የሚሆን ሲሆን የማሻሻያ ማስታወቂያ እስኪወጣድረስ ተግባራዊ ይሆናል።ፔጀር የሬዲዮ ዌቭ የሚጠቀም የመገናኛ ዘዴ ነው። ሰዎች መረጃ ሲልኩ የሚተላለፈውም የሬዲዮ ፍሪክዌንሲ በመጠቀም ነው። መልዕክት የተላከለት ሰው መልዕክቱ እንደደረሰው በንዝረት መልዕክት መስጠት የሚችል ሲሆን አጭር የጽሑፍ ወይም የድምፅ መልዕክቶችን ማስተላለፍ ይችላል።እ.አ.አ 1980ዎቹ እንዲሁም 90ዎቹ በስፋት ጥቅም ላይ ይውል የነበረ የግንኙነት መሳሪያ አሁን ላይ በሞባይል ስልክ ቢተካም አሁንም ድረስ በተለያዩ ቦታዎች ጥቅም ላይ ይውላል። በሌላ መረጃ ቱርክ እስራኤል በጋዛ ያለውን ጦርነት ወደ ሊባኖስ ለማስፋት እየፈለገች ነው ስትል ከሳለች።የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሃካን ፊዳን በመንግስት የሚተዳደረው ቲአርቲ ቴሌቪዥን ላይ ቀርበዉ በሰጡት መግለጫ "በአካባቢው ያለው ዉጥረት መባባስ አሳሳቢ ነው" ብለዋል። እስራኤል ጥቃቷን በደረጃ ወደ ሊባኖስ ስትወስድ እናያለን ሲሉ አክለዋል።እስራኤል በፍንዳታው ዙሪያ የተናገረችው መረጃ ባይኖርም ቱርክ ሀገሪቱን ተጠያቂ አድርጋለች። በእስራኤል የተከናወኑ ጸብ ቀስቃሽ ተግባራት በአጸፋ ምላሹም ኢራን፣ ሂዝቦላህ እና ለእነሱ ቅርብ የሆኑ አካላት ዝምታን አይመርጡም ሲሉ ፊዳን ተናግረዋል። በስምኦን ደረጄ
عرض المزيد ...
7 949
2
✅ በ አይነቱ ልዩ የሆነ በ ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ 4 ትልቅ ለውጥን መፍጠር የሚችሉ የ ስራ ዘርፎችን ልክ እንደ ግራፊክስ ዲዛይን ቪዲዮ ኤዲቲንግ ዲጂታል ማርኬቲንግ እና አኘ ወርክ በ አንድ ላይ ያካተተ ስልጠና ተጀመረ። 📌 ይሄ ስልጠና መቀመጫውን አሜሪካ አና አዚው ሀገራችን ላይ ባደረጉ ለውጥ ፈጣሪ ትውልደ ኢትዮጵያውያን የተቋቋመ ዘውድ ቴክ በተባለ ድርጅት የተዘጋጀ ነው። 📌 ባለፈው ሳምንት ቅዳሜ በማዶ ሆቴል የዘውድ ቴክ የስራ አጋሮች እና ታዋቂ የሚዲያ ሰዎች በተገኙበት መክፈቻ ፕሮግራምም ተካሂዱዋል። 📌 ዘዉድ ቴክ በኢትዮጵያ የመጀመሪያ ያስባለው የ 25/75% ክፍያ ያመቻቸ ሲሆን  አንድ ሰልጣኝ ለመመዝገብ ዘውድ ቴክ ከሚጠይቀው ክፍያ ላይ 25% ብቻ ከፍሎ ሙሉ የ 3ወሩን ስልጠና የሚወስድ ሲሆን የተቀረውን 75% የሚከፍለው በዘውድ ቴክ በኩል በሚመቻችለት የስራ እድል ከዛላ ከሚያገኘው ገቢ በ አመት ውስጥ እየከፈለ የሚጨርስ ይሆናል 📌ስልጠናውን ላጠናቀቀ certificate እንዲሁም ነፃ የ ኢንተርናሽናል ክፍያ መፈፀምያ ማስተር ካርድ የሚያገኝ ይሆናል 📌ስልጠናው ሙሉ በሙሉ ኦንላይን እንደመሆኑ ማንኛውም ሰው ከትምህርት እና ስራ ሰዓት በኋላ መማር ይችላል። ⚠️ያለው ቦታ ውስን ስለሆነ ከታች በተቀመጠው ሊንክ የዘውድ ቴክ ቻናልን ተቀላቅላችሁ እዛ ላይ የሚገኘውን የስልጠና ገለፃ ቪድዮ ተመልክታችሁ ባሉት ስልክ ቁጥሮች መደወል እና መልዕክት ማስቀመጥ ትችላላችሁ። 👇የዘውድ ቴክ ቻናልን ለመቀላቀል መልካም እድል!
عرض المزيد ...
63
0
የመንግሥት የጸጥታ ኃይሎች በደቡብ ጎንደር ዞን በሚገኙ ከአምስት ወረዳዎች ለቀው ወጡ በደቡብ ጎንደር ዞን በሚገኙ ከአምስት ወረዳዎች ከ2016 ዓ.ም ማብቂያ ጀምሮ የመንግሥት የጸጥታ ኃይሎች ለቀው መውጣታቸውን ዋዜማ ዘግባለች።   የፌደራል እና የክልሉ የጸጥታ ኃይሎች እስቴ መካነ ኢየሱስ፣ አንዳቤት፣ ሙጃ፣ ስማዳ እና ታች ጋይንት ከሚባሉ ወረዳዎች ከነሐሴ ዕኩሌታ ጀምሮ እስከ ጳጉሜ መጨረሻ ባሉት ጊዜያት ሙሉ በሙሉ ለቀው መውጣታቸውን ዋዜማ ተገንዝባለች።  የመንግስት ኀይሎች ለምን ከአካባቢው እንደወጡ በይፋ አልተናገሩም። በወረዳዎቹ የነበሩ የወረዳ እና የቀበሌ አመራሮች እንዲሁም የፖሊስ እና የሚሊሻ አባላት ሙሉ ቤተሰቦቻቸውን ይዘው ከፌደራል የጸጥታ አካላት ጋር ወደ ዞኑ መቀመጫ ደብረታቦር ገብተዋል። ይህን ተከትሎም በወረዳዎች ኹሉም ዓይነት የመንግሥት አገልግሎቶች የተቋረጡ ሲሆን፣ በፖሊስ እና በሚሊሻ የሚሰጡ አገልግሎቶችም በተመሳሳይ ቆመዋል።  በአንጻሩ በእነዚህ ወረዳዎች ባንኮች እና የጤና ተቋማት አገልግሎት እየሰጡ ነው ተብሏል። ትምህርት ቤቶች እስካሁን ምዝገባ አላከናወኑም።  የአማራ ክልል መንግስት የኮምኒኬሽን ቢሮ ስለጉዳዩ ላቀረብንለት ጥያቄ ጉዳዩን መመለስ የሚችለው የኮማንድ ፖስቱ ነው ከማለት ውጪ ምላሽ ለመስጠት አልፈቀደም። የመንግሥት የጸጥታ ኃይሎች ከወረዳዎቹ ለቀው መውጣታቸውን ተከትሎ በቦታው የተተኩት የፋኖ ታጣቂዎች የራሳቸውን የአስተዳደር መዋቅር ለመዘርጋት ጥረት እያደረጉ ነው። በአንጻሩ የዞኑ ዋና መቀመጫ ደብረታቦር እንዲሁም ንፋስ መውጫ፣ ፎገራ እና ደራ ወረዳዎች ዋና ከተሞቻቸው በመንግሥት የጸጥታ ኃይሎች ስር ይገኛሉ። ሆኖም በዞኑ ዋና ከተማ ደብረታቦር ዙሪያ ታጣቂዎች በብዛት እንደሚገኙ ሰምተናል።  በሰሜን ጎንደር፣ ምዕራብ ጎንደር እና ማዕከላዊ ጎንደር ዞኖችም ሰሞኑን በኹለቱ ኃይሎም መካከል ከፍተኛ ውጊያ ሲካሄድ ቆቷል።  ሰሞኑን በመንግስት ወታደሮች እና በፋኖ ታጣቂዎች መካከል የዞን አስተዳደር መቀመጫ በሆኑት በጎንደር እና በደባርቅ ከተሞች በከባድ መሳሪያ የታገዘ ውጊያ ሲካሄድ ሰንብቷል። ይህን ተከትሎም በርካታ ሰላማዊ ሰዎች ለሞት እና ለአካል ጉዳት መዳረጋቸውን ተገንዝበናል። በክልሉ በመንግሥት የጸጥታ ኃይሎች እና በፋኖ ታጣቂዎች መካከል ከአንድ ዓመት በላይ ባስቆጠረው ግጭት በርካታ ሰላማዊ ሰዎች ለሞትና ለአካል ጉድት መዳረጋቸውን ብሎም ከፍተኛ የንብረት ውድመት መድረሱን የተለያዩ የሰብዓዊ መብት ተቋማት የሚያወጧቸው ሪፖርቶች ያሳያሉ።   Via ዋዜማ
عرض المزيد ...
8 551
10
8 236
5
አንዲት እናት አራት ህፃናት በሠላም ተገላገሉ ዕድሜያቸው 42 ዓመት የሆኑት አንዲት እናት በፓዊ አጠቃላይ ሆስፒታል አራት ህፃናትን በሠላም ተገላግላለች። ወይዘሮ አደባባይ የሺነህ የሚባሉ ሲሆን  ነዋሪነታቸው በአዊ ብሔረሰብ ዞን ጃዊ ወረዳ አሊኩራንድ ቀበሌ ናቸው። በዛሬው ዕለትም በፓዊ አጠቃላይ ሆስፒታል ሶስት ወንድና አንድ ሴት በድምሩ አራት ህፃናትን በሰላም ተገላግላ፥ በአሁኑ ስዓትም ጨቅላ ህፃናቶች በሰባት ወራት ጊዜያቸው ሳይደርስ የተወለዱ ስለሆነ በህፃናት ፅኑ ህሙማን ክፍል በዶ/ር አብዮት ጎበና እና ሳቀታ ማሩ (የጨቅላ ህፃናት ነርስ) ጥብቅ ክትትል እየተደረገላቸው እንደሚገኝ ተገልጿል ። በዚሁ ሆስፒታል መንታ መውለድና አልፎ አልፎም አንዲት እናት እስከ ሶስት ህፃናትን በአንድ ጊዜ መገላገል የተለመደ ሲሆን በዛሬው ዕለት የተከሰተው በአንድ ጊዜ አራት ህፃናትን መገላገል ግን በሆስፒታሉ አዲስ ክስተት መሆኑ  ሚድዋይፍ ባለሙያ ሞገስ ጌታቸው ተናግረዋል። ወላጅ እናት የአሁኑን ጨምሮ ለስድስተኛ ጊዜ የወለዱ ሲሆን በአሁኑ ስዓት በሙሉ ጤንነት እንደሚገኙ ገልፀው በሰላም እንድትገላገል ለረዷቸው  ለሆስፒታሉ የህክምና ባለሙያዎችና የፓዊ ወረዳ ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ጽህፈት ቤት ላደረጉላቸው ድጋፍ ምስጋና ማቅረባቸውን ብስራት ሬዲዮ እና ቴሌቪዥን ከወረዳው ኮሙኒኬሽን ያገኘው መረጃ ያመላክታል።
عرض المزيد ...
7 239
11
📱🌼Broz mobile and computer 🌼📱 🍏Original iPHONE, Samsung & Tab  አዳዲስ እንዲሁም ያገለገሉ ስልኮችን በተመጣጣኝ ዋጋ እና ያሎት ስልክ ላይ በመጨመር ከበቂ ዋስትና  እና ጥገና ጋር  እኛው  ጋር  ያገኛሉ ። Telegram Channel ቀድመው ይደውሉ 👇 Contact us ☎️      251911120707      251904818881 📍ቦሌ መድሃኒአለም
7 655
2
ኢትዮቴሌኮም በ2016 በጀት ዓመት 98.7 ቢሊዮን ብር ገቢ ማግኘቱን አስታወቀ ኢትዮ ቴሌኮም መሪ የእድገት ስትራቴጂ በሚል የሶስት ዓመት እቅድ ያወጣ ሲሆኑ እቅዱ የማክሮ ኢኮኖሚ    ጭማሪውን  ታሳቢ  ያደረገመሆኑን የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈጻሚ  የሆኑት ወይዘሪት ፍሬህይወት ታምሩ ገልጸዋል።በ2017 በዲጂታል ኢትዮጵያ ጉዞ ውስጥ በቴክኖሎጂ  ሁሉንም ዘርፍ የሚያነቃቃ እና በጅማሬ ላይ ያሉ እንዲሁም አዳዲስ ቢዝነሶች የሚያድጉበት እና ውጤታማ እንዲሆኑ ማስቻል ከእቅዶቹ መካከል ቀዳሚ መሆኑን መናገራቸውን ብስራት ሬዲዮ እና ቴሌቪዥን ሰምቷል። ኢትዮ ቴሌኮም በ2017 በጀት ዓመት ለሚያከናውናቸው ስራዎች 1 ቢሊዮን ዶላር መመደቡን እንዲሁም በርካታ አዳዲስ ስራዎችን  እንደሚሰራም ተጠቁሟል። ተቋም በ2016 በጀት ዓመት 98.7 ቢሊዮን ብር ገቢ ያገኘ ሲሆን  በ2017 በጀት ዓመት ገቢውን ወደ 163.7 ቢሊዮን ብር ለማሳደግ  ማቀዱን አስታውቋል። በሌላ በኩል በዓመቱ  መሰረተ ልማቶችን  ማጠናከር እንዲሁም አዳዲስ መገንባት እና  የሞባይል ሽፋን አሁን ካለበት የተሻለ ለማድረግ  1298  አዳዲስ የሞባይል  ጣቢያ በመገንባት አሁን ካለው በ15.6 % ለማሰደግ  እየሰራ መሆኑን አስታውቋል ። እቅዱ በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች በተለይም በገጠራማ አካባቢዎች ላይ የሞባይል  አገልግሎት ተጠቃሚዎችን ቁጥር ማሳደግን ያካተተ ሲሆን በዓመቱ  የደንበኞቹን ቁጥር 83 ሚሊዮን ለማድረስ የታቀደ መሆኑም ተጠቁሟል። በተጨማሪም 920 ኪ.ሜ የፋይበር ማስፋፊያ  እንደሚደረግ የተነገረ ሲሆን የኢንተርኔት አገልግሎት ለማስፋፋት የ4ጂ እና አድቫንስድ 4ጂ ማስፋፋይ  ስራ የሚሰራ ሲሆን በ500 የ4ጂ የኢንተርኔት  አገልግሎት ባላገኙ  ከተሞች የ4ጂ ተጠቃሚ ማድረግ  እና 15 የሚሆኑ ከተሞች ላይ ደግሞ የ5ጂ  አገልግሎት ተጠቃሚ  እንደሚሆኑ ወይዘሪት ፍሬህይወት ታምሩ ገልጸዋል ። በኤደን ሽመልስ
عرض المزيد ...
8 387
7
8 021
2
በሊባኖስ በቀናት ልዩነት ለሁለተኛ ጊዜ በደረሰ የኮሙኒኬሽን መሳሪያ ፍንዳታ 20 ሰዎች ሲገደሉ 450 ያህሉ ቆሰሉ በሊባኖስ ውስጥ በገመድ አልባ የመገናኛ መሳሪያዎች በደረሰ ፍንዳታ ቢያንስ 20 ሰዎች ሲገደሉ ከ450 በላይ ቆስለዋል ሲል የሀገሪቱ የጤና ሚኒስቴር አስታውቋል። በዋና ከተማይቱ ቤይሩት ደቡባዊ ዳርቻዎች፣በካአ ሸለቆ እና በደቡባዊ ሊባኖስ እንደ ምሽግ በሚታዩ አካባቢዎች ታጣቂው ቡድን ሂዝቦላ የሚጠቀምባቸው የኮሙኒኬሽን መሳሪያዎች ላይ ፍንዳታው ደርሷል። ፍንዳታው የተከሰተው ማክሰኞ የሂዝቦላህ አባላት ላይ ፔጀርስ ፈንድተው የተገደሉ 12 ሰዎች በቀብር ስነ-ስርዓት ወቅት ነው። ለዚያ ጥቃት ሂዝቦላህ እስራኤልን ተጠያቂ አድርጓል። እስራኤል በጉዳዩ ላይ እስካሁን አስተያየት አልሰጠችም። ጥቃቶቹ የደረሱት የእስራኤል የመከላከያ ሚኒስትር ዮአቭ ጋላንት “በጦርነቱ ውስጥ አዲስ ምዕራፍ” መጀመሩን ካስታውቁ እና የእስራኤል ጦር ክፍል ወደ ሰሜናዊ ክፍል እንዲሰማራ ትዕዛዝ ከሰጡ በኃላ ነው። የእስራኤል የስለላ ድርጅት ሞሳድ በሊባኖስ ቡድን ሂዝቦላህ ትእዛዝ ማስተላለፊያ የኮሙኒኬሽን መስመር ላይ በታይዋን የተሰሩ 5 ሺ ፔጃሮች ውስጥ አነስተኛ መጠን ያለው ፈንጂ በመትከል  የማክሰኞው ፍንዳታ እንዲሳካ ማድረጉን የሊባኖስ ከፍተኛ የደህንነት ምንጭ ገልጿል። ይህ ሴራ ብዙ ወራትን ያስቆጠረ ነው። ጥቃቱ በሂዝቦላህ ላይ ያነጣጠረ ሲሆን በሊባኖስ የሚገኙ ሆስፒታሎችን እንዲጨናነቅ አድርጓል ። አንዳንድ ተጎጂዎች ለዓይነ ስውርነት ሲዳረጉ ሌሎች ደግሞ የሰውነት አካል መቆረጥ ያስፈልጋቸዋል ።በሊባኖስ እና በሶሪያ ከተከሰቱት ገዳይ ፍንዳታዎች ጋር የተገናኘው የታይዋኑ ፔጀርስ አምራች ጎልድ አፖሎ ፔጀሮቹ የተሰሩትየጀሮ ማ በአውሮፓውያን ባሲ ድርጅት ነው ብሏል። የታይዋኑ ኩባንያ ፔጀሮቹ በሃንጋሪ ዋና ከተማ ቡዳፔስት ላይ መቀመጫውን ላደረገው ባሲ ምርቱን እንዲሰራ ፍቃድ ሰጥቶታል። ፔጀር የሬዲዮ ዌቭ የሚጠቀም የመገናኛ ዘዴ ነው። ሰዎች መረጃ ሲልኩ የሚተላለፈውም የሬዲዮ ፍሪክዌንሲ በመጠቀም ነው። መልዕክት የተላከለት ሰው መልዕክቱ እንደደረሰው በንዝረት መልዕክት መስጠት የሚችል ሲሆን አጭር የጽሑፍ ወይም የድምፅ መልዕክቶችን ማስተላለፍ ይችላል።እ.አ.አ 1980ዎቹ እንዲሁም 90ዎቹ በስፋት ጥቅም ላይ ይውል የነበረ የግንኙነት መሳሪያ አሁን ላይ በሞባይል ስልክ ቢተካም አሁንም ድረስ በተለያዩ ቦታዎች ጥቅም ላይ ይውላል። በስምኦን ደረጄ
عرض المزيد ...
12 130
10
ቶተንሀም በካራባኦ ካፕ ከመሰናበት ተርፏል በኮቬንትሪ ሊሰናበት ደቂቃዎች ብቻ ቀርተውት የነበረው ቶተንሀም በስፔንስ እና ጆንሰን ግቦች አሸንፏል ።
8 670
2
የ ቻምፒየንስ ሊግ ጨዋታዎች ውጤት                             ማንቸስተር ሲቲ 0-0 ኢንተር ሚላን        ሴልቲክ 5-1 ስሎቫን ብራቲስላቫ       ⚽ ስኬልስ         ⚽ ዊመር       ⚽ ፉሩሀሺ       ⚽ ኤንገልስ       ⚽ ማኤዳ       ⚽ ኢዳህ   ክለብ ብሩጅ 0-3 ዶርቱመንድ ⚽⚽ ጊቴንስ   ⚽ ጉራሲ ፒኤስጂ 1-0 ጅሮና ⚽ ሜንዴስ
8 440
0
ከቀናት በኋላ ከመድፈኞቹ ጋር ፍልሚያ ያለበት ማንችስተር ሲቲ ፤ ወሳኝ ተጫዋቹ ኬቨን ደ ብረይነ በምሽቱ የሻምፒዮንስ ሊግ ጨዋታ በጉዳት ተቀይሮ ከሜዳ ወጥቷል 😬 👉
8 698
3
ከቃሊቲ ማረሚያ ማዕከል ሰባት ታራሚዎች ወደ ዩኒቨርሲቲ ገቡ በፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን በቃሊቲ ማረሚያ ማዕከል በመደበኛ የትምህርት መርሃ ግብር ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የቆዩ ታራሚዎች ዩኒቨርሲቲ ለመግባት የሚያስችለውን ውጤት ማምጣት ችለዋል በፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን በቃሊቲ ማረሚያ ማዕከል በመደበኛ የትምህርት መርሃ ግብር ትምህርታቸውን ሲከታተሉ ከነበሩ 21 የተፈጥሮ ሳይንስ የህግ ታራሚ ተማሪዎች መካከል ሰባቱ ወደ ዩኒቨርሲቲ ለመግባት የሚያስችለውን ውጤት ማምጣት ችለዋል፡፡ የቃሊቲ ማረሚያ ማዕከል የመጀመሪያ ደረጃና አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር አቶ ሳምሶን ወንድሜነህ የህግ ታራሚ ተማሪዎች ምንም እንኳ በህግ ጥላ ስር ቢሆኑም ትምህርታቸውን በአግባቡ ሲከታተሉ መቆየታቸውንና ለውጤት መብቃታቸውን ገልፀዋል፡፡ ተማሪ የህግ ታራሚዎቹ የመልቀቂያ ፈተናውን ከመውሰዳቸው በፊት በሀገር አቀፍ ደረጃ የተዘጋጀውን የሙከራ ሞዴል ፈተና መውሰዳቸው ለውጤታቸው አበርክቶ እንደነበረው ተናግረዋል፡፡ ተማሪ የህግ ታራሚዎቹን የትምህርት ሚኒስቴርም ሆነ የሚመለከታቸው የባለድርሻ አካላት ተገቢውን ድጋፍ እንዲያደርጉላቸው ጥሪ አቅርበዋል፡፡ የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ውጤት ያመጡት የህግ ታራሚ ተማሪዎች እንደሚሉት በማረሚያ ቤት ውስጥ በእርምት ላይ ሆነው ፈተናውን መውሰድ ከባድ ተፅዕኖ ቢኖረውም ውጤታማ መሆን ችለናል ብለዋል፡፡ ያመጡት ውጤት ለመታረማቸው ማሳያ በመሆኑ የፍትህ ሚኒስቴር በይቅርታና ምህረት መልቀቅ የሚችልበትን እድል እንዲያገኙ ካልሆነም  ትምህርታቸውን በርቀት እንዲከታተሉ ዩኒቨርሲቲዎችን እንዲያመቻችላቸው ጠይቀዋል፡፡ Via EBC
عرض المزيد ...
8 458
21
ከቃሊቲ ማረሚያ ማዕከል ሰባት ታራሚዎች ወደ ዩኒቨርሲቲ ገቡ በፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን በቃሊቲ ማረሚያ ማዕከል በመደበኛ የትምህርት መርሃ ግብር ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የቆዩ ታራሚዎች ዩኒቨርሲቲ ለመግባት የሚያስችለውን ውጤት ማምጣት ችለዋል በፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን በቃሊቲ ማረሚያ ማዕከል በመደበኛ የትምህርት መርሃ ግብር ትምህርታቸውን ሲከታተሉ ከነበሩ 21 የተፈጥሮ ሳይንስ የህግ ታራሚ ተማሪዎች መካከል ሰባቱ ወደ ዩኒቨርሲቲ ለመግባት የሚያስችለውን ውጤት ማምጣት ችለዋል፡፡ የቃሊቲ ማረሚያ ማዕከል የመጀመሪያ ደረጃና አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር አቶ ሳምሶን ወንድሜነህ የህግ ታራሚ ተማሪዎች ምንም እንኳ በህግ ጥላ ስር ቢሆኑም ትምህርታቸውን በአግባቡ ሲከታተሉ መቆየታቸውንና ለውጤት መብቃታቸውን ገልፀዋል፡፡ ተማሪ የህግ ታራሚዎቹ የመልቀቂያ ፈተናውን ከመውሰዳቸው በፊት በሀገር አቀፍ ደረጃ የተዘጋጀውን የሙከራ ሞዴል ፈተና መውሰዳቸው ለውጤታቸው አበርክቶ እንደነበረው ተናግረዋል፡፡ ተማሪ የህግ ታራሚዎቹን የትምህርት ሚኒስቴርም ሆነ የሚመለከታቸው የባለድርሻ አካላት ተገቢውን ድጋፍ እንዲያደርጉላቸው ጥሪ አቅርበዋል፡፡ የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ውጤት ያመጡት የህግ ታራሚ ተማሪዎች እንደሚሉት በማረሚያ ቤት ውስጥ በእርምት ላይ ሆነው ፈተናውን መውሰድ ከባድ ተፅዕኖ ቢኖረውም ውጤታማ መሆን ችለናል ብለዋል፡፡ ያመጡት ውጤት ለመታረማቸው ማሳያ በመሆኑ የፍትህ ሚኒስቴር በይቅርታና ምህረት መልቀቅ የሚችልበትን እድል እንዲያገኙ ካልሆነም ትምህርታቸውን በርቀት እንዲከታተሉ ዩኒቨርሲቲዎችን እንዲያመቻችላቸው ጠይቀዋል፡፡ Via EBC
عرض المزيد ...
61
1
በወረኢሉ ከተማ በትናንትናው እለት የጣለው ዝናብ በመኖሪያ ቤት ላይ ጉዳት አደረሰ በወረኢሉ ከተማ አስተዳደር 02 ቀበሌ ልዩ ስሙ ገበያ ዳር በተባለው አካባቢ መሰከረም 07/2017 ዓ.ም ከሌሊቱ 7:00 ሰዓት አካባቢ የጣለው ዝናብ በመኖሪያ ቤት ላይ ጉዳት አደረሰ። ጉዳት የደረሰበት ቤት ባለቤት አቶ ግሩም አበበ ሲሆኑ በቤቱ ውስጥ አቶ ግሩምን ጨምረው ሁለት ሰዎች ይኖሩ እንደነበር ገልጸው በጉዳቱ በቤተሰባቸው ላይ ጉዳት እንዳላደረሰባቸው ቢገልጹም ነገር ግን ቤቱ ከፊት ለፊት ያለው ግድግዳ ሙሉ በሙሉ በመውደቁ በዉስጡ ለመኖር እንደማያስችላቸው ተናግረዋል። አቶ ግሩም ቤቱን በመጠገንም ሆነ ሌላ ተለዋጭ ቤት እንዲሰጣቸው ለሚኖሩበት 02 ቀበሌና መንግሰታዊም ሆነ መንግስታዊ ላልሆኑ ድርጅቶቾ የሰብዓዊ ድጋፍ ጥያቄ አቅርበዋል። አቶ ግሩም በተጨማሪ ችግራቸውን የከፋ ያደረገባቸው የአካል ጉዳተኛ መሆናቸውና የ70 ዓመት አዛውንት እናታቸው አብረዋቸው ስለሚኖሩና ምንም ዓይነት የገቢ ምንጭ የሌላቸው መሆኑ እንዳሳሰባቸው አስረድተዋል። የችግሩን አሳሳቢነት በተመለከተ የ02 ቀበሌ አስተዳዳሪ አቶ ሹመት ተስፋዬ ምላሽ ሲሰጡ ለኢንቨስትመንት እየተባለ ብዙ ቤቶች እንዲለቀቁ እየተደረገ በመሆኑ ብዙ የቀበሌ ቤት የለም የተለቀቁትም እንደሚፈርሱ ሌሎች የቀበሌ ቤቶች እንደሚሰሩና አሁን ላይ የፈረሰው የእነ አቶ ግሩምን ቤት ቀበሌው ህዝቡን በማስተባበር ቦቦታው እድሳት እንደሚደረግ ተናግረዋል ።
عرض المزيد ...
8 422
3
በፓኪስታን አንድ አባት የልጁን ውሎ ለመከታተል የደህንነት ካሜራ በጭንቅላቷ ላይ አስቀመጠ አንድ ፓኪስታናዊ አባት ለሴት ልጁ የእለት እንቅስቃሴዋን እና ለደህንነቷ በመስጋት በጭንቅላቷ ላይ የስለላ ካሜራ እንዲቀመጥ አድርጎል። መልካም ወላጆች የልጆቻቸውን ደህንነት ለማረጋገጥ የማያደርጉት ነገር የለም። ታዲህ ይህ የፓኪስታን ሰው በለጋ ሴት ልጁ ጭንቅላት ላይ የስለላ ካሜራ በመትከሉ ቀኑን ሙሉ እንቅስቃሴዋን እንዲከታተል እና ደህና መሆኗን እንዲያረጋግጥ ማድረጉን ተከትሎ በኤክስ ላይ ቪዲዮ በስፋት ተሰራጭቷል።ቀጣዩ የደህንነት ደረጃ  በሚል ቪዲዮ ላይ በርካቶች አስተያየት ሰጥተዋል። ፓኪስታናዊቷ ሴት ጭንቅላቷ ላይ ሲሲቲቪ ካሜራ በማድረግ ቃለ መጠይቅ ስትደረግ ትታያለች። ስለ ካሜራው ስትጠየቅ፣ የአባቱ ሃሳብ እንደሆነ ተናግራለች፣ ነገር ግን የአባቷን ውሳኔ እንዳልተቃወመች የምታነሳው ወጣቷ ምክንያቷ ደግሞ ወላጆቼ ስለ ደህንነቴ እጅግ ያሳስባቸዋል ስትል አክላለች። ወጣቷ ከቤት ወደ ውጭ ስትወጣ በባትሪ የሚሰራ ካሜራ ጭንቅላቷ ላይ እንድታደርግ ይህ ሀሳብ የመጣው በካራቺ የአንዲት ወጣት ሴት የግፍ ግድያን ተከትሎ እንደሆነ ትናግራለች። “የግል ጠባቂ” ነው ስትል አባቷ የምትገልፀው ወጣቷ የስለላ ካሜራው በቅርበት እንዲከታተለኝ እንደሚረዳው ነግሮኛል እኔም ለማድረግ ተስማምቻለው ብላለች። ምንም እንኳን ውሳኔው የሞኝነት ድርጊት ነው ሲሉ በርካቶች ቢገልፁም ወጣቷ በካራቺ በሴቶች ላይ የሚደርሰው ጥቃት ግን እጅግ በመበራከታቸው ቤተሰቤ ይህንን ለማድረግ ካላው ችግር አንፃር በቂ ምክንያት አላቸው ብላለች። የስለላ ካሜራ እንዴት እንደሚሰራ ግልፅ ባይሆንም በርካቶች በማህበራዊ ድህረ ገጽ ላይ በሰነዘሩት አስተያየት ካሜራው አንድ ሰው ወጣቷን ቢያጠቃ ብዙም ካሜራው ሊከላከላት እና ሊጠብቃት እንደማይችል ጠቁመዋል። በተቃራኒው ቤተሰቧ የደህንነት ካሜራውን በማየት ብቻ ወጣቷን የሚቀርቡ ሰዎችን በሙሉ መጥፎ አላማ እንዳላቸው ማሰባቸው በቀጣይ ህይወቷ ጉዳት ያስከትልባታል ሲሉ ተደምጠዋል። በስምኦን ደረጄ
عرض المزيد ...
8 175
19
7 863
13

surveillance-camera.webp

1
0
በ2016 በጀት አመት በሽያጭ ከተወገዱ ተሽከርካሪዎችና ንብረቶች ከ200 ሚሊዮን ብር በላይ ለመንግስት ገቢ ተደረገ የመንግስት ግዥ አገልግሎት በበጀት ዓመቱ በሽያጭ ከተወገዱ ተሽከርካሪዎችና ንብረቶች ያገኘው ገቢ በታሪኩ ከፍተኛ የሚባል መሆኑን አስታውቋል፡፡ አገልግሎት በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በሽያጭ ከተወገዱ ተሽከርካሪዎችና ልዩ ልዩ ንብረቶች በአገልግሎቱ ታሪክ ከፍተኛ የሆነውን 213.9 ሚሊየን ብር ለመንግስት ገቢ ማስገኘቱን የመንግስት ግዢ አገልግሎት የሕዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ኃላፊ ወይዘሮ ጎጃም ታደለ ለብስራት ሬዲዮና ቴሌቪዥን የተናገሩ ሲሆን በዚህም ከ2015 በጀት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር የ110ነጥብ9 ሚሊዮን ብር ብልጫ ወይም 106ጥብ7 በመቶ ዕድገት ማሳየቱን ተገልጿል። ይህ ገቢ የተገኘው በ2016 ዓ.ም. ዩኒቨርሲቲዎችን ጨምሮ በአዲስ አበባ በሚገኙ 155 የፌዴራል ባለበጀት መሥሪያ ቤቶች የንብረት ክምችት መለየት የሚያስችል ንቅናቄ በማካሄድ፣ በሁለት ዙር በሽያጭ ከተወገዱ ተሽከርካሪዎችና ልዩ ልዩ ንብረቶች ነውም ተብላል፡፡ የ2017 ዓ.ም. ዕቅዱን አስመልክቶ እንደገለፀው ከመስከረም 2017 ጀምሮ በገንዘብ ሚኒስቴር አስተባባሪነት አገር አቀፍ የንብረት ማስወገድ ንቅናቄ ተግባራዊ ሲደረግ ሁሉንም የፌዴራል ባለበጀት መሥሪያ ቤቶች፣ ክልሎች፣ የከተማ አስተዳደሮችና የመንግሥት ልማት ድርጅቶችን በማሳተፍ በአዲሱ በጀት ዓመት ከ 1 ቢሊዮን ብር በላይ ለመሰብሰብ መታቀዱ የአገልግሎቱ ኮሚኒኬሽን ኃላፊ ወይዘሮ ጎጃም ጨምረው ተናግረዋል፡፡ በትግስት ላቀዉ
عرض المزيد ...
8 216
0
የታንዛኒያ ፕሬዝዳንት አሜሪካ እና ምዕራባውያን በውስጣዊ ጉዳያችን ጣልቃ እየገቡ ነው ሲሉ ከሰሱ የታንዛኒያ ፕሬዝዳንት ዩናይትድ ስቴትስን ጨምሮ በርካታ ምዕራባውያን ሀገራት በታንዛኒያ የሚፈፀመውን ግድያ እና አፈናን ጨምሮ በውስጥ ጉዳያችን ዙሪያ የሚሰጡትን አስተያየት ተችተዋል። ፕሬዝዳንቷ ሳሚያ ሱሉሁ ሀሰን በሰሜን ምስራቅ ኪሊማንጃሮ ክልል ሞሺ አካባቢ በነበራቸው ቆይታ “እኛ ስልጣን ላይ የወጣነው ሀገራችንን እንዴት መምራት እንዳለብን እንዲነገረን አይደለም ብላለች። ሳሚያ ምንም አይነት ኤምባሲዎችን በቀጥታ ሳትጠቅ በዩናይትድ ስቴትስ ውስጥ የተኩስ አመፅ እንዳለ ጠቅሳለች። በሁሉም ሀገር እንዲህ ዓይነት ክስተቶች ይከሰታሉ ነገር ግን ታንዛኒያ "አምባሳደሮቿን በሌሎች ሀገራት የውስጥ ጉዳይ ውስጥ ጣልቃ እንዲገቡ በጭራሽ አላዘዘችም ብለዋል። ፕሬዝዳንቷ ይህንን የተናገሩት የአሜሪካ ኤምባሲ ባወጣው መግለጫ የተነሳ ሲሆን የታንዛኒያ ዋንኛ ተቃዋሚ ፓርቲ የሆነው ቻዴማ መሪ  አሊ ሞሃመድ ኪባኦ ግድያ በገለልተኛ አካል እንዲጣራ ኤምባሲው በማሳሰቡ ነው። የፖለቲከኛው አስከሬን የተቆረጠ የሰውነት አካል በዳሬሰላም ተገኝቷል።የአውሮፓ ህብረት የተልዕኮ ሃላፊ፣ የብሪታንያ እና የካናዳ ከፍተኛ ኮሚሽኖች፣ የኖርዌይ እንዲሁም የስዊዘርላንድ ኤምባሲዎች በጋራ ባወጡት መግለጫ “ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ የጥቃት ድርጊቶች፣ መታገት ፣ የፖለቲካ እና የሰብአዊ መብት ተሟጋቾች ሞት ስጋት እንደፈጠረባቸው ገልፀዋል። ሳሚያ ህገ መንግስቱን ያለምንም ውጫዊ ጫና ለመጠበቅ እና ለመከላከል መንግሥታቸው ያለውን ቁርጠኝነት ገልፀዋል። ታንዛኒያ የራሷ አስተዳደር አላት፤ የውጭ ዲፕሎማቶች ራሳቸውን እንደ ቴክኒክ አማካሪ ከማየት ይቆጠቡ ስትል ፕሬዝዳንቷ አሳስባለች። የታንዛኒያን ደህንነት ለመጠበቅ እና የታንዛኒያን ህገ-መንግስት ለመጠበቅ ቃል ገብተናል። የታንዛኒያን ህዝን ጥበቃ እና ደህንነት ለማሻሻል የተቻለንን ሁሉ እናደርጋለን ምክንያቱም የእኛ ኃላፊነት ነው እናም በዚህ ኃላፊነት ላይ ከማንም አቅጣጫ እንዲሰጠን አንፈልግም በማለት ፕሬዝዳንቷ ተናግራለች። በስምኦን ደረጄ
عرض المزيد ...
8 052
0
7 635
0
ጋዜጠኞቹ ከሀገር መሰደዳቸውን አስታወቁ ከሶስት ወራት በፊት ከእስር የተፈቱት ጋዜጠኛ በቃሉ አላምረው እና በላይ ማናዬ፤ ሀገራቸውን ለቅቀው ለመሰደድ መገደዳቸውን ተናገሩ። ሁለቱ ጋዜጠኞቹ የተሰደዱት፤ በመንግስት የጸጥታ አባላት በተሰጣቸው “ለህይወታቸው የሚያሰጋ” “ማስጠንቀቂያ” እና ከእስር ከተፈቱ በኋላ በሚደረግባቸው “ክትትል” ምክንያት እንደሆነ ገልጸዋል። ጋዜጠኛ በላይ እና በቃሉ 11 ቀናት የፈጀ “አስቸጋሪ ጉዞ” በማድረግ ከሀገር የወጡ ሲሆን ይህም ባለፈው ሳምንት ሰኞ ጳጉሜ 4፤ 2016 መሆኑን አስረድተዋል። ሆኖም ጋዜጠኞቹ በአሁኑ ወቅት ያሉበትን ሀገር፤ “ከደህንነት ስጋት” ጋር በተያያዘ ከመግለጽ ተቆጥበዋል።ሁለቱ ጋዜጠኞች ለእስር ተዳርገው የነበረው፤ ባለፈው ዓመት ግንቦት ወር ባበቃው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ምክንያት ነበር። በአማራ ክልል እና እንዳስፈላጊነቱ ደግሞ “በየትኛውም የኢትዮጵያ አካባቢ” ተፈጻሚነት የነበረው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ እንዲታወጅ በሚኒስትሮች ምክር ቤት ውሳኔ የተላለፈው ሐምሌ 28፤ 2015 ነበር።
عرض المزيد ...
8 586
2
በአዲስ አበበ ከተማ ገቢዎች ቢሮ 100 ሚሊየን ብር እንዲከፍሉ የተጠየቁ ግለሰብን 11 ሚሊየን ብር ጉቦ በማስከፈል ክፍያዉን ያስቀነሱ ሰራተኞችና ደላሎች በቁጥጥር ስር ዋሉ በከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ ከፍተኛ ግብር ከፋዮች ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የታክስ ኦዲት ቡድን አስተባባሪ፤ ባለሙያዎች እና ደላሎች በሙስና ወንጅል ተጠርጥረዉ በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን ቢሮው አስታውቋል። መስከረም 06 ቀን 2017 ዓ.ም በቅርንጫፍ ፅ/ቤቱ በሙስና ወንጅል ተጠርጥረዉ በቁጥጥር ስር ውለዉ ምርመራ እየተጣራባቸው ይገኛል ተብሏል፡፡የታክስ ኦዲት ቡድን አስተባባሪ የሆኑት 1ኛ አቶ ሃብታሙ ግዲሳ ጆቴ 2ኛ.ስምረት ገ/እግዚአብሔር አሰፋ የከፍተኛ ግብር ከፋዮች የታክስ ኦዲት ከፍተኛ ኦፊሰር 3ኛ. አቶ ዮሴፍ ባቡ ሆራ የከፍተኛ ግብር ከፋዮች የታክስ ኦዲት ከፍተኛ ኦፊሰር ናቸዉ፡፡ 4ኛ አቶ አቤኔዘር ቶሎሳ ሙሉ የከፍተኛ ግብር ከፋዮች ታክስ ኦዲት ከፍተኛ ኦፊሰር 5ኛ አቶ ለሚ ሲሌ ከፍተኛ ግብር ከፋይ የታክስ ኦዲት ከፍተኛ ኦፊሰር እና 6ኛ.ወ/ሮ መቅደስ አረጋዊ ገንዘብ ተቀባይ መሆናቸው ተገልፃል፡፡ከ1ኛ እስከ 5ኛ ተራ ቁጥር የተጠቀሱት ተጠርጣሪዎች በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳዳር ገቢዎች ቢሮ ከፍተኛ ግብር ከፋዮች ቅርንጫፍ /ጽ/ቤት የታክስ ኦዲት ቡድን አስተባባሪ፤ ባለሙያዎች ናቸው። ጳጉሜ 05 ቀን 2016 ዓ.ም በአዲስ አበባ ከተማ ቂርቆስ ክ/ከተማ ወረዳ 10 ውስጥ ግብር ከፋይ ከሆኑ ግለሰብ የ2011 እና 2012 ዓመት የግብር ኦዲት እንዲደረግላቸዉ የሚጠበቅበትን ሰነድ ያቀረበላቸዉ ሲሆን መክፈል ያለብህ አንድ መቶ ሚሊየን ብር ነዉ በማለት ይገልፁላቸዋል።ሆኖም ይህን  ያህል አልከፍልም ካልክ ግማሹን አስይዘህ ነዉ ይግባኝ የምታቀርበዉ በማለት ባለሙያዎቹ ይናገራሉ፡፡ ለጊዜዉ በቁጥጥር ስር ያልዋለ ግለሰብ ሂሳብ አስጨራሽ በሚል የቀረበ ደላላ ጉዳዩን አስተካክላለሁ በሚል በማግባባት ለራሱ ሶስት ሚሊየን ብር እና ለሰራተኞቹ ስምንት ሚሊየን ብር በመክፈል ለመንግስት ደግሞ ከመቶ ሚሊየን በመቀነስ አስራ ሶስት ሚለየን ብር  ትከፍላለህ በማለት ይደራደራቸዋል።ስምንት ሚሊየን ብር በቤተሰቦቻቸዉ ስም በመቀበል 13 ሚሊየን ብር የመንግስት የሚከፈለዉን እንዲከፍል መተማመኛ ሲሰጡት በተደረገ ክትትል እጅ ከፍንጅ የተያዙ ሲሆን ምርመራዉ ቀድሞ በነበረዉ ክትትል መሰረት በስፋት እየተጣራ ይገኛል ፡፡
عرض المزيد ...
8 294
47
7 719
42
በአዲስ አበበ ከተማ ገቢዎች ቢሮ 100 ሚሊየን ብር እንዲከፍሉ የተጠየቁ ግለሰብን 11 ሚሊየን ብር ጉቦ በማስከፈል ክፍያዉን ያስቀነሱ ሰራተኞችና ደላሎች በቁጥጥር ስር ዋሉ በከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ ከፍተኛ ግብር ከፋዮች ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የታክስ ኦዲት ቡድን አስተባባሪ፤ ባለሙያዎች እና ደላሎች በሙስና ወንጅል ተጠርጥረዉ በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን ቢሮው አስታውቋል። መስከረም 06 ቀን 2017 ዓ.ም በቅርንጫፍ ፅ/ቤቱ በሙስና ወንጅል ተጠርጥረዉ በቁጥጥር ስር ውለዉ ምርመራ እየተጣራባቸው ይገኛል ተብሏል፡፡የታክስ ኦዲት ቡድን አስተባባሪ የሆኑት 1ኛ አቶ ሃብታሙ ግዲሳ ጆቴ 2ኛ.ስምረት ገ/እግዚአብሔር አሰፋ የከፍተኛ ግብር ከፋዮች የታክስ ኦዲት ከፍተኛ ኦፊሰር 3ኛ. አቶ ዮሴፍ ባቡ ሆራ የከፍተኛ ግብር ከፋዮች የታክስ ኦዲት ከፍተኛ ኦፊሰር ናቸዉ፡፡ 4ኛ አቶ አቤኔዘር ቶሎሳ ሙሉ የከፍተኛ ግብር ከፋዮች ታክስ ኦዲት ከፍተኛ ኦፊሰር 5ኛ አቶ ለሚ ሲሌ ከፍተኛ ግብር ከፋይ የታክስ ኦዲት ከፍተኛ ኦፊሰር እና 6ኛ.ወ/ሮ መቅደስ አረጋዊ ገንዘብ ተቀባይ መሆናቸው ተገልፃል፡፡ከ1ኛ እስከ 5ኛ ተራ ቁጥር የተጠቀሱት ተጠርጣሪዎች በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳዳር ገቢዎች ቢሮ ከፍተኛ ግብር ከፋዮች ቅርንጫፍ /ጽ/ቤት የታክስ ኦዲት ቡድን አስተባባሪ፤ ባለሙያዎች ናቸው። ጳጉሜ 05 ቀን 2016 ዓ.ም በአዲስ አበባ ከተማ ቂርቆስ ክ/ከተማ ወረዳ 10 ውስጥ ግብር ከፋይ ከሆኑ ግለሰብ የ2011 እና 2012 ዓመት የግብር ኦዲት እንዲደረግላቸዉ የሚጠበቅበትን ሰነድ ያቀረበላቸዉ ሲሆን መክፈል ያለብህ አንድ መቶ ሚሊየን ብር ነዉ በማለት ይገልፁላቸዋል።ሆኖም ይህን ያህል አልከፍልም ካልክ ግማሹን አስይዘህ ነዉ ይግባኝ የምታቀርበዉ በማለት ባለሙያዎቹ ይናገራሉ፡፡ ለጊዜዉ በቁጥጥር ስር ያልዋለ ግለሰብ ሂሳብ አስጨራሽ በሚል የቀረበ ደላላ ጉዳዩን አስተካክላለሁ በሚል በማግባባት ለራሱ ሶስት ሚሊየን ብር እና ለሰራተኞቹ ስምንት ሚሊየን ብር በመክፈል ለመንግስት ደግሞ ከመቶ ሚሊየን በመቀነስ አስራ ሶስት ሚለየን ብር ትከፍላለህ በማለት ይደራደራቸዋል።ስምንት ሚሊየን ብር በቤተሰቦቻቸዉ ስም በመቀበል 13 ሚሊየን ብር የመንግስት የሚከፈለዉን እንዲከፍል መተማመኛ ሲሰጡት በተደረገ ክትትል እጅ ከፍንጅ የተያዙ ሲሆን ምርመራዉ ቀድሞ በነበረዉ ክትትል መሰረት በስፋት እየተጣራ ይገኛል ፡፡
عرض المزيد ...
1
0
የአዲስ አበባ ህዝብ የብልፅግና መንግስት የቤት ፈረሳ ይበቃል ሊል ይገባል ከባልደራስ ለእውነተኛ ዲሞክራሲ ፓርቲ የተሰጠ መግለጫ የኦህዴድ ብልፅግና የጎጥ ፖለቲካ ወላጅ አባቱን ተክቶ አራት ኪሎን ከተቆጣጠረ ስድስት አመታትን አስቆጥሯል። በዚህ ሁሉ ጊዜ ከሀሰት ትርክት የተወለደ የጥላቻ ፓለቲካን በተለያዩ የሀገራችን ክፍሎች፣ በከፋ መጠንና በተለያየ ስልት ሳያቋርጥ ሲያራምድ ቆይቷል። እንደ ኦሀዴድ/ብልፅግና ያሉ ጥንፈኛ የነገድ ፖለቲከኞች ፖለቲካቸውን የተቃኜው የዛሬ 40 እና 50 ዓመታት በፊት በፈጠሩት የሃስት ትርክት ላይ ነው፡፡ የኦህዴድ/ብልፅግና ይዞት ከተነሳው የሀሰት ትርክት መካከል 1ኛው የአማራ ጥላቻ ሲሆን፣ ከዚሁ ጋር በተያያዘ ሁኔታ የአዲሰ አበባን ነዋሪ የስነ ህዝብ (ዲሞግራፊ) ሰብጥር የመቀየር ግቡ ደግሞ ሁለተኛው ነው፡፡ በእርግጥ የህዝብ ስብጥር ለውጥ ፖሊሲው በሁሉም ማህበረሰቦች ላይ እየተተገበረ ቢሆንም፤ በተለይ ግን የአማራውን ህዝብ ዋነኛ ኢላማው ማድረጉ የአደባባይ ሚስጥር ነው። የኦህዴድ/ብልፅግና መንግሥት ወንበሩ የተደላደለ እንደመሰለው በቀጥታ የተሸጋገረው የአዲስ አበባ ታሪክ ናቸው ያላቸውን ቅርሶችና ስፍራዎች ወደ ማውደምና በአዲስ አበባ ዳርቻ የሚኖሩ የአዲስ አበባ ነዋሪዎችን ቤት ወደማፍረስ ነው። የአዲስ አበባን ዙሪያ ነዋሪ ቤት በማፍረስ የጀመረው በነገድ ፖለቲካ ላይ የተመሰረተውን ተግባር ወደ መሀል ከተማ በማምጣት ነባር የአዲስ አበባ ሰፈሮችን ወደማጥፋት/erase/ ተሸጋግሯል። በዚህ ሂደትም የነዋሪዎች ህይወት ጠፍቷል፣ አባወራዎች/እማወራዎች ከእነልጆቻቸው ጎዳና ላይ ወድቀዋል፣ ህፃናት ከትምህርት ገበታቸው ተፈናቅለዋል፣ ማህበራዊ መስተጋብር ፈርሷል፣ በአጠቃላይ በአዲስ አበባ ህዝብ ላይ ከፍተኛ በደል እየተፈፀመበት ይገኛል። ይህ በህዝብ ዝምታ ምክንያት እዚህ የደረሰው መኻል ፒያሳን ነፍስ አልባ ያደረገው የብልጭልጭ መብራትና የኮሪዶር ልማት ከመገናኛ እስከ መሪ ፣ ከፒያሳ እስከ ለግሐር፣ ቄራን እና የተለያዩ የአዲስ አበባን አካባቢዎች አዳርሶ አሁን ደግሞ ካዛንችስን፣ ፈረንሳይ ለጋሲዮንን እና ሽሮሜዳን ነፍስ አልባና፣ ታሪክ አልባ፣ ባለቤት አልባ አድርጎ ለማፈራረስ ቀጠሮ ይዟል። ከሰሞኑ የአገዛዙ ካድሬዎች በካዛንችስ፣ በፈረንሳይ እና ሽሮሜዳ የሚገኙ ነዋሪዎችን በመሰብሰብ አንድ ወር በማይሞላ ጊዜ ውስጥ ከሀብት ንብረታቸው እንደሚፈናቀሉና መንደራቸውም እንደሚፈርስ ማስጠንቀቂያ ሰጥቷቸዋል። በስብሰባው ላይ ማናቸዉም መገናኛ ብዙሃን እንዳይገኙ እና ድምፅ ሊቀርፁ ይችላሉ የተባሉ መሳሪያዎች እንዳይገቡ በተደረገባቸው በእነዚህ ስብሰባዎች፣ ነዋሪዎች ተወልደው ካደጉባቸው፣ ለአመታት ከኖሩባቸው ሰፈሮቻቸው አንድ ወር ባልሞላ ጊዜ እንደሚፈናቀሉ መርዶው ተነግሯቸዋል። አንድ ዜጋ ተወልዶ ባደገበት አካባቢ ይቅርና በፈለገው የሀገሪቱ ክፍል ተንቀሳቅሶ፣ ሀብት ንብረት አፍርቶ የመኖር ህገመንግስታዊ መብቱ የተጠበቀ ስለመሆኑ ብልጽግና ሲፈለግ ብቻ የሚያከብረዉ ህገመንገስት ይደነገጋል። አገዛዙ እሞትለታለሁ በሚለው በህገመንግስት አንቀጽ 43 ተራ ቁጥር 4 ላይ "የልማት እንቅስቃሴ ዋና ዓላማ የዜጎችን እድገትና መሠረታዊ ፍላጎቶች ማሟላት ይሆናል" ይላል። የብልጽግና አገዛዝ አዲስ አበባ ላይ እያካሄደ ያለው የኮሪደር ልማት ተብዬው በርግጥ የከተማውን ህዝብ መሠረታዊ ፍላጎትቶች ለማሟላት እየተከናወነ ያለ ነው ወይ? ብለን ስንጠይቅ መልሱ አይደለም ነው። የህዝብ ጥያቄ የሚመልስ የልማት ሥራ የሚጀምረው መሠረታዊ የሆኑ አንገብጋቢ የህዝብ ጥያቄዎችን በመመለስ ነው። የአዲስ አበባ ህዝብ ለዘመናት ሲጠይቃቸው ከኖሩ ጥያቄዎች መካከል ዋነኛው፣ “የአዲስ አበባ ከተማ ራስ ገዝ መሆንና በጎጥ ኮታ የሚመደቡ ካድሬዎች ሊያስተዳድሩት አይገባም፤ አዲስ አበባ በራሷ ልጆች ትመራ” የሚለው ዋነኛው ሲሆን፣ በቀበሌ ቤት የሚኖሩ ነዋሪዎች በሚኖሩበት አካባቢ የመኖሪያ ቤት ችግርን የሚያቃላልሉ በቂ የኮንዶሚኒየም ህንፃዎች እንዲገነቡ፣ የግል ይዞታ ያላቸው በግል ይዞታቸው ላይ የማልማት እድል እንዲሰጣቸው፣ የኑሮ ውድነትን ለማሻሻል የሚያስችሉ ፖሊሲዎች እንዲቀረፁ፣ የመብራት አቅርቦት እንዲሻሻል፣ በቂ የንፁህ ውሃ አቅርቦት እንዲኖር፣ የትራንስፖርት ችግርን የሚፈቱ መፍትሄዎች እንዲቀየሱ፣ ለወጣቱ ትውልድ የሥራ እድል መፍጠር የሚያስችሉ ፖሊሲዎች እንዲነደፉ የሚሉ ጥያቄዎችም ይገኙበታል። የብልፅግናው አገዛዝ ግን በተቃራኒው እራሱ ቃል የገባውን "ከእንግዲህ ማንም ከቀዬው አይፈናቀልም" የሚለውን የማዘናጊያ መሃላውን ሙሉ በሙሉ አጥፎታል። በህገ-መንግሥቱ በአንቀጽ 43 ተራቁጥር 2 ላይ "ዜጎች በብሔራዊ ልማት የመሳተፍ በተለይም አባል የሆኑበትን ማህበረሰብ የሚመለከቱ ፖሊሲዎችና ፕሮጀክቶች ላይ ሀሳባቸውን እንዲሰጡ የመጠየቅ መብት አላቸው" የሚለውን አንቀፅ በመተላለፍና የህዝብን ጥያቄ ወደጎን በመተው፤ በተለይ በአሁኑ ሰዓት በከፍተኛ የኑሮ ውድነት እየተሰቃየ ያለው የአዲስ አበባ ህዝብ ማህበራዊ የአብሮነትና የመደጋገፍ እሴቶቹን በመጠቀም በጉርብትና አንዱ ከሌላው ጋር እየተረዳዳ ችግሩን ለመቋቋም በሚጣጣርበት ወቅት፤ ጭራሽ በኮሪደር ልማት ስም የከተማውን ህዝብ ቤትና ንብረት አፍርሶ ፣ ነባሩን የከተማ ማህበረስብ ከቤተ እምነቶቹ አርቆ፣ የደሃ ደሃ ለማድረግና ከተማውን አስለቅቆ ምንም አይነት የመሠረተ ልማት ባልተዘረጋባቸው ስፍራዎች ለመወርወር እየተጣደፈ ይገኛል። ባልደራስ ለእውነተኛ ዲሞክራሲ ፓርቲ ፣ ከዚኽ በፊት የብልጽግናን መንግሥት ከመነሻው በጎጥ ፖለቲካ ላይ የተመሰረተ አላማውን አውቆና ለይቶ አመራሩ እና አባላቱ ከባድ መስዋእትነቶችን እየከፈሉ ሲታገሉት መቆየቱ የሚታወስ ነው። ባልደራስ አሁንም በመሃል ከተማ የድሃው ቤትና ንብረት ፈርሶ ልማት ተብሎ እየተሠራ ያለው የሳርና ዛፍ ተከላ እንዲሁም የብልጭልጭ መብራት ጋጋታና መናፈሻ የከተማውን ህዝብ መሠረታዊ ችግር እንዲፈታ የታለመ ሳይሆን ነዋሪዎችን በማፈናቀል የብልጽግና መንግስትን የገጽታ ግንባታ ለማድረግ መሆኑን ፓርቲያችን ያምናል። ይህን አይነት በህዝብ ጥቅምና መብት ላይ እየተረማመዱ የመሪዎችን ግለሰባዊ ገጽታ የመገንባት ሂደት ፓርቲያችን አጥብቆ ይቃወማል። አብዛኛውን ደሃውንና፣ መካከለኛ ኑሮ ያለውን ማህበረሰብ ተሳትፎና የጥቅም ተጋሪነት ያላረጋገጠ ልማት ፣ ልማት ሊባል አይችልም። በመኾኑም ባልደራስ ለእውነተኛ ዲሞክራሲ ፓርቲ ከአዲስ ዓመት ዋዜማ ጀምሮ በልማት ሰበብ የመፈናቀል አደጋ የብልፅግና መንግሥት የጋረጠባቸው የሽሮ ሜዳ፣የካሳንቸስና፣ የፈረንሳይ ነዋሪዎች በህገመንግሥቱ የተሠጣቸውን መብት ተጠቅመው በአገዛዙ ከታቀደው የመፍረስ አደጋ እራሳቸውን በህጋዊ መንገድ አንዲከላከሉ እያሳሰበ የሚከተሉትን የአቋም መግለጫ ለማስተላለፍ ይገደዳል። ሀ. ለብልጽግና መራሹ አገዛዝ እና የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የቀረበ ጥሪ፦ 1. መንግሥት በማናለብኝነት አካሄድ የአዲስ አበባን ነዋሪ ሰፈሮች በአጠቃላይ በተለየም ከአዲሱ አመት ወዲህ ደግሞ የሽሮሜዳ፣ የፈረንሳይና፣ የካሳንችስ ማህበረሰብ መኖሪያ ቤቶች በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ አፈርሳለሁ በማለት ህዝብን ከማሸበር ተግባሩ በአስቸኳይ እንዲቆጠብና ከህዝብ ጋር ነፃ ውይይት እንዲጀምር፣
عرض المزيد ...
212
0
2. ከዚህ በፊት የብልፅግና መንግሥት "ከእንግዲህ አንድም የሚፈናቀል ሰው አይኖርም" ሲል ለህዝብ የገባውን ቃል እንዲያከብርና፣ "እገዛለታለሁ" በሚለው ህገ-መንግሥት አንቀጽ 43 ላይ የተደነገጉትን የህዝብ መብቶች እንዲያከብር፣ 3. በህገመግሥቱ አንቀጽ 43 ተራ ቁጥር 4 ላይ እንደተደነገገው የልማት እንቅስቃሴ ዋና አላማ የዜጎችን እድገትና መሠረታዊ ፍላጎቶች ማሟላት በመኾኑ፤ ህዝብ መንግሥት የሚያቅዳቸውን የልማት ፕሮጀክቶች የማወቅ፣ አስተያየት የመስጠት፣ የመሳተፍ እና የመወያየት መብቱ እንዲጠበቅለት፣ 4. ህዝብን ያላማከለ፣ የህዝብን ይሁንታ ያላገኘና በህዝብ መብት ላይ እየተረማመደ የሚከናወን ፕሮጀክት መጨረሻው ውድቀት፣ የንብረት ውደመት እና የገንዘብ ብክነት እንደሆነ አገዛዙ እንዲገነዘብ እናሳስባለን። ለ. ከቤት ንብረቱ ከአንድ ወር ባነሰ ጊዜ ውስጥ እንደሚፈናቀል ለተነገረው የሽሮሜዳ ፣ የካዛንችስና የፈረንሳይ ነዋሪ የቀረበ ጥሪ፦ 1. ማንኛውም የልማት ፕሮጀክት ህዝብን ያማከለና የህዝብን አመኔታና ተቀባይነት ሳያገኝ መከናወን እንደማይችል ህገ-መንግስቱ ስለሚደነግግ፤ ህገመንግሥታዊ መብትህን ተጠቅመህ በየአካባቢህ በመነጋገርና ኮሚቴዎችን በማቋቋም ህጋዊ ጥያቄዎችህን ፔቲሽን በመፈራረም በጽሑፍ ለሚመለከተው የከተማ አስተዳደር ጽህፈት ቤት እንድታመለክት፣ 2. አገዛዙ የምታቀርበውን ትያቄ አልቀበልም ብሎ ለውይይት የማይጋብዝህ ከሆነ፣ ጥቄዎችህን ወደ ፍርድ ቤት በመውሰድ በህጋዊ ትግሉ እንዲገፋበት እናሳስባለን፡፡ 3. የሚመለከታችሁ አካላት ሁሉ ከአዲስ አበባ ህዝብ ጎን በመቆም ሙያዊ ትብብር እንድታደርጉ ፓርቲያችን ባልደራስ ይጠይቃል፡፡ በጨረሻም መላው የአዲስ አበባ ነዋሪ በኮሪዶር ልማት ስም በርካታ የከተማዉን አካባቢ፤ ሰው አልባ፣ባለቤት አልባ ያደረገው የብልፅግና መንግሥት አሁን ደግሞ ነባር ሰፈሮችኽን አንድ በአንድ በልማት ስም ለማፍረስ እየተጣደፈ ይገኛል። በመኾኑም፤ አሁን የመፍረስ አደጋ ከተጋረጠባቸው የፈረንሳይ፣ የካሳንችስ እንዲኹም የሽሮሜዳ ነዋሪዎች ጎን በመቆም፣ በስልጡን አካኼድ ድምፅህን እንድታሰማ። እንደ ማህበራዊ ሚዲያ ያሉ የህዝብ ድምጽ የሚሰማባቸውን ዘዴዎች በመጠቀም ከተማህን ከመፍረስ አደጋ አንድታደግ ጥሪያችንን እናቀርባለን። የባልደስራ ለእውነተኛ ዲሞክራሲ ፓርቲ የሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ መስከረም 07/ 2017 ዓ.ም አዲስ አበባ/ ኢትዮጵያ
عرض المزيد ...
121
0
1
0
ሞሳድ በሂዝቦላህ የኮሙኒኬሽን መስመር ፔጀር ላይ 5 ሺ አነስተኛ መጠን ያላቸውን ፈንጂዎች እንዲቀበር ማድረጉ ተሰማ የእስራኤል የስለላ ድርጅት ሞሳድ በሊባኖስ ቡድን ሂዝቦላህ ትእዛዝ ማስተላለፊያ የኮሙኒኬሽን መስመር ላይ በታይዋን የተሰሩ 5 ሺ ፔጃሮች ውስጥ አነስተኛ መጠን ያለው ፈንጂ በመትከል  የማክሰኞው ፍንዳታ እንዲሳካ ማድረጉን የሊባኖስ ከፍተኛ የደህንነት ምንጭ ገልጿል። ይህ ሴራ ብዙ ወራትን ያስቆጠረ ነው። ጥቃቱ በሂዝቦላህ ላይ ያነጣጠረ ሲሆን በሊባኖስ የሚገኙ ሆስፒታሎችን እንዲጨናነቅ አድርጓል ። አንዳንድ ተጎጂዎች ለዓይነ ስውርነት ሲዳረጉ ሌሎች ደግሞ የሰውነት አካል መቆረጥ ያስፈልጋቸዋል ።በሊባኖስ እና በሶሪያ ከተከሰቱት ገዳይ ፍንዳታዎች ጋር የተገናኘው የታይዋኑ ፔጀርስ አምራች ጎልድ አፖሎ ፔጀሮቹ የተሰሩት በአውሮፓውያን ባሲ ድርጅት ነው ብሏል። የታይዋኑ ኩባንያ ፔጀሮቹ በሃንጋሪ ዋና ከተማ ቡዳፔስት ላይ መቀመጫውን ላደረገው ባሲ ምርቱን እንዲሰራ ፍቃድ ሰጥቶታል። የሊባኖሱን የሂዝቦላህ ቡድን አባላትን ለመግደል በሺህ የሚቆጠሩ ፈንጂዎች የተመረቱት በታይዋን ኩባንያን ስም በመጠቀም እንደሆነ ከተገለፀ በኋላ የታይዋን ወሳኝ የቴክኖሎጂ ኢንዱስትሪ ተጎትቶ ወደ መካከለኛው ምስራቅ የውጥረት ትኩሳት ውስጥ ገብቷል። ጎልድ አፖሎ የተባለው ድርጅት በሊባኖስ በጅምላ የፈነዳውን ኤአር-924 ሞዴል ፔጄሮችን እንዳመረተ በመግለጽ ባሲ በተባለ የአውሮፓ ኩባንያ በሰጠው የፈቃድ ውል የተሰራ ነው ሲል አስተባብሏል።ተንታኞች ክስተቱ ወደፊት ለደሴቲቷ ግዛት ታይዋን የቴክኖሎጂ ኢንዱስትሪ የማይመቹ ጥያቄዎችን እንደሚያስነሳ ተናግረዋል ። በብሔራዊ የታይዋን ኦሽን ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂ ህግ ፕሮፌሰር የሆኑት ክሪስቲ ቺያንግ "ይህ ክስተት ለኢንዱስትሪው ትልቅ እና ወሳኝ ትምህርት ይሆናል" ብለዋል። የታይዋን የቴክኖሎጂ ኢንዱስትሪ የሃርድዌር አምራቾች ብቻ እንደሆኑ አድርገው ራሳቸውን ያስባሉ። እናም ከፖለቲካ ጋር ምንም ግንኙነት የላቸውም ፤ የራሳቸውን ንግድ ይሠራሉ ነገር ግን ከእንግዲህ በመላው ዓለም እንዲህ ብቻ ላይታመኑ ይችላሉ ብለዋል።የታይዋን ኢኮኖሚ ሚኒስቴር “ወደ ሊባኖስ በቀጥታ ምርቱን የመላክ ሪከርድ የለም” ብሏል። ሚኒስቴሩ በታይዋን ከሚገኙ የመገናኛ ብዙኃን ለተነሱ ጥያቄዎች በሰጠው ምላሽ የጎልድ አፖሎ ኩባንያ እ.ኤ.አ. ከ2022 እስከ 2024 አመት ነሃሴ ወር ድረስ 260,000 ፔጃርን በዋነኛነት ወደ አውሮፓ እና አሜሪካ ልኳል። እነዚህ ምርቶች በመገናኛ ብዙሃን እንደዘገበው የፍንዳታ አቅም የላቸውም" ሲል ሚኒስቴሩ አክሎ ገልጿል። ኩባንያው ከመገናኛ ብዙሃን የተነሱትን ፎቶግራፎች ከገመገመ በኋላ እና ገጾቹ ወደ ውጭ ከተላኩ በኋላ የተሻሻሉ መሆናቸውን በማረጋገጥ ምርቱ የእኛ ስለመሆኑ አጠራጣሪ ነው" ብሏል።ፔጀር የሬዲዮ ዌቭ የሚጠቀም የመገናኛ ዘዴ ነው። ሰዎች መረጃ ሲልኩ የሚተላለፈውም የሬዲዮ ፍሪክዌንሲ በመጠቀም ነው። መልዕክት የተላከለት ሰው መልዕክቱ እንደደረሰው በንዝረት መልዕክት መስጠት የሚችል ሲሆን አጭር የጽሑፍ ወይም የድምፅ መልዕክቶችን ማስተላለፍ ይችላል።እ.አ.አ 1980ዎቹ እንዲሁም 90ዎቹ በስፋት ጥቅም ላይ ይውል የነበረ የግንኙነት መሳሪያ አሁን ላይ በሞባይል ስልክ ቢተካም አሁንም ድረስ በተለያዩ ቦታዎች ጥቅም ላይ ይውላል። በስምኦን ደረጄ
عرض المزيد ...
8 318
11
7 796
3
በሊባኖስ በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎችን ላቆሰለው ፍንዳታ ሄዝቦላህ እስራኤልን ተጠያቂ አደረገ 👉 የሂዝቦላህ አባላት ለመግባባት የሚጠቀሙባቸው በእጅ የሚያዙ ፔጄሮች ላይ ከባድ ፍንዳታ ደርሷል በሊባኖስ ውስጥ የታጠቀው የሂዝቦላህ አባላት ለመግባባት የሚጠቀሙባቸው በእጅ የሚያዙ ፔጄሮች ላይ በደረሰ ፍንዳታ አንድን ሕፃን ጨምሮ ዘጠኝ ሰዎች መሞታቸውን የሀገሪቱ የጤና ሚኒስትር ገልፀዋል። በሊባኖስ የኢራን አምባሳደር ከቆሰሉት ሰዎች መካከል ይገኙበታል። በቤይሩት እና በሌሎች በርካታ ክልሎች በተመሳሳይ ፍንዳታ 2,800 ሰዎች ቆስለዋል። ከቆሰሉት ሰዎች መካከል 200 ያህሉ ክፉኛ ተጎድተዋል። በኢራን የሚደገፈው ሄዝቦላህ በፔጄሮች ፍንዳታ "የተለያዩ የሂዝቦላህ ክፍሎች እና ተቋማት ሰራተኞች የሆኑ ስምንት ተዋጊዎች መሞታቸውን አረጋግጧል። ቡድኑ “ለዚህ የወንጀል ጥቃት” እስራኤልን በመወንጀል “ፍትሃዊ ቅጣት” እንደሚጠብቃት ገልጿል። የእስራኤል ጦር በጉዳዩ ላይ አስተያየት ለመስጠት ፈቃደኛ አልሆነም።ፍንዳታዎቹ ከመከሰታቸው ከሰዓታት በፊት የእስራኤል የፀጥታ ካቢኔ እንዳስታወቀው የተፈናቀሉ ነዋሪዎች በሰላም እንዲመለሱ ለማድረግ በሀገሪቱ ሰሜናዊ ክፍል ላይ የሂዝቦላ ጥቃቶችን ማቆም ይፋዊ የጦርነት ግብ ነው ብሏል። እ.ኤ.አ ኦክቶበር 7 በእስራኤል እና በሃማስ መካከል በጋዛ ጦርነት ከጀመረ ማግስት አንስቶ በእስራኤል-ሊባኖስ ድንበር ላይ በየቀኑ የተኩስ ልውውጥ እየተደረገ ይገኛል። ሂዝቦላህ እንደገለፀው ቡድኑ ለግንኙነት አገልግሎት በስፋት የሚተማመንበት ቁጥራቸው በውል ያልተገለጸ ፔጀርስ ፈንድተዋል። በዋና ከተማዋ ቤሩት እና በሌሎች በርካታ አካባቢዎች የሞባይል ስልኮችን ለመጥለፍ እና ለመከታተል ስጋት በመኖሩ ሂዝቦላህ በነዚህ መሳሪያዎች ላይ ይተማመናል። በስምኦን ደረጄ
عرض المزيد ...
8 489
5
7 991
2
ኤንድሪክ የመጀመሪያ የሻምፒዮንስ ሊግ ጎሉን በአስደናቂ ሁኔታ አስቆጥሯል 😮 ጎሏ 👉
8 385
1
የምሽቱ አስደናቂ ውጤት Bayern Munich beat Dinamo Zagreb 9 (N-I-N-E) goals to 2 (T-W-O) No team has ever scored more in a Champions League game
7 769
0
🇪🇺 በአውሮፓ ቻምፒየንስ ሊግ የመጀመሪያ ሳምንት ጨዋታዎች  ጁቬንትስ 3-1 ፒኤስቪ አይንዶቨን ⚽️ይልዲዝ       ⚽️ሳይባሪ ⚽️ማኬን ⚽️ጎንዛለዝ ያንግ ቦይስ 0-3 አስቶንቪላ ⚽️ቲሌማንስ ⚽️ዋትኪንስ ⚽️ኦናና   ኤስ ሚላን 1-3 ሊቨርፑል ⚽ ፑሊሲች               ⚽ ኮናቴ                                ⚽ ቫንዳይክ                                  ⚽️ስቦዝላይ ባየር ሙኒክ 8-2 ዳይናሞ ዛግሬብ ⚽️⚽️⚽️⚽️ ሀሪ ኬን (ፍ)    ⚽️ፔትጎቪች    ⚽ ጉሬሮ                    ⚽️ኦጊዋራ  ⚽️⚽️ ኦሊሴ ⚽️ ሳኔ ሪያል ማድሪድ 2-1 ስቱትጋርት ⚽️ ምባፔ             ⚽️ኡንዳቭ ⚽️ ሩዲገር ስፖርቲንግ  2-0 ሊል ⚽ ግዮኬሬሽ ⚽️ ዴባስት ~ ካራባኦ ካፕ ማንችስተር ዩናይትድ 7-0 ባርንስሊይ ⚽️⚽️ራሽፎርድ ⚽️አንቶኒ (ፍ) ⚽️⚽️ጋርናቾ ⚽️ኤሪክሰን ጎሎች 👉
عرض المزيد ...
6 392
2
ቶማስ ሙለር በሻምፒዮንስ ሊግ መድረኩ በአንድ ክለብ በ 152 ጨዋታዎች ላይ በመሰለፍ የቀድሞው የባርሴሎና አማካኝ ዣቪን ክብረወሰን ተረክቧል 🫡
6 876
1
31 የሻምፒዮንስ ሊግ ጎሎች የባየርንሙኒኩ አጥቂ ሀሪ ኬን በሻምፒዮንስ ሊጉ 31ግቦችን ማስቆጠር በመቻሉ ፤ በውድድሩ ታሪክ ከእንግሊዝ ቀዳሚውን ስፍራ ይዞ የቆየውን ዋይኒ ሩኒ መብለጥ ችሏል 🤝
6 842
0
ኪሊያን ምባፔ በሪያል ማድሪድ መለዮ የመጀመሪያ የሻምፒዮንስ ሊግ ግቡን አስቆጥሯል 🔥 ጎሉን ለመመልከት 👉
6 635
1
🇪🇺 በአውሮፓ ቻምፒየንስ ሊግ የመጀመሪያ ሳምንት ጨዋታዎች     የጨዋታ አጋማሽ ውጤት  ኤስ ሚላን 1-2 ሊቨርፑል ⚽ ፑሊሲች        ⚽ ኮናቴ                                ⚽ ቫንዳይክ ባየር ሙኒክ 3-0 ዳይናሞ ዛግሬብ    ⚽ ሀሪ ኬን (ፍ)    ⚽ ጉሬሮ    ⚽ ኦሊሴ ሪያል ማድሪድ 0-0 ስቱትጋርት ስፖርቲንግ  1-0 ሊል ⚽ ዮክሬሽ
7 209
1
የቀን ስራ በመስራት የሚተዳደረው ወጣት በለጠ ታመነ የ4 ሚሊዮን ብር እድለኛ ሆነ ወጣት በለጠ ታመነ የድሬዳዋ ነዋሪ ሲሆን በአድማስ ዲጂታል ሎተሪ 1ኛ ዕጣ የ4ሚሊየን ብር ዕድለኛ ሆነዋል ፡፡ ወጣት በለጠ የተገኘውን የቀን ስራ በመስራት ቤተሰቡን የሚመራ ሲሆን በደረሰውም ገንዘብ ቤት እንደሚገዛበት ገልጸዋል ፡፡
8 251
4
ዘመን ባንክ አጠቃላይ ካፒታሉ  ከ12 ቢሊዮን ብር በላይ መድረሱን አስታወቀ 👉በዛሬው ዕለት ለደንበኞቹ የምስጋና እና የሽልማት  መርሃ ግብር አካሂዷል ዘመን ባንክ ከተመሰረተ 16 ዓመት የሞላው ሲሆን በዛሬው ዕለት ደንበኞችን የማመስገን እና   70 ለሚሆኑት ደግሞ የሽልማት  መርሃ ግብር  አካሂዷል። ዘመን ባንክ  ከተለመደው የባንክ አገልግሎት በተለየ መልኩ ዘመናዊ እና በቴክኖሎጂ  በታገዘ መልኩ ለደንበኞቹ ግልጋሎት  እየሰጠ እንደሚገኝ የዘመን ባንክ ዋና ስራ አስፈጻሚ የሆኑት አቶ ደረጄ ዘበነ ለብስራት ሬዲዮ እና ቴሌቪዥን ተናግረዋል። የዲጂታል ባንኪግን አገልግሎት  ለደንበኞቹ ምቹ በሆነ መልኩ   ያቀረበ ሲሆን ከደንበኞቹ ጋር ያለውን ግንኙነት  ለማሳደግ እና አብሮነት ለማጠንከር   እንዲያስችል በዛሬው ዕለት ለደንበኞቹ ምስጋና  አቅርቧል። ዘመን ባንክ ከ16 ዓመታት በፊት ወደ ስራ ሲገባ በ91 ሚሊዮን ብር ካፒታል የጀመረ ሲሆን በአሁን ሰዓት  12 ቢሊዮን 262 ሚሊዮን  ብር ካፒታል መድረስ መቻሉ ተጠቁሟል። ባንኩ  127 የሚደርሱ ቅርንጫፎች በተለያዩ አካባቢዎች  በመክፈት  እየሰራ የሚገኝ ሲሆን  በቅርቡ ካስመረቀው አዲስ ዋና መስሪያ ቤት በተጨማሪ  ሌላ አዲስ መስሪያ ቤት ለመገንባት በሂደት ላይ እንደሚገኝ ብስራት ሬዲዮ  እና ቴሌቪዥን ሰምቷል። በኤደን ሽመልስ
عرض المزيد ...
8 194
8
📱🌼Broz mobile and computer 🌼📱 🍏Original iPHONE, Samsung & Tab  አዳዲስ እንዲሁም ያገለገሉ ስልኮችን በተመጣጣኝ ዋጋ እና ያሎት ስልክ ላይ በመጨመር ከበቂ ዋስትና  እና ጥገና ጋር  እኛው  ጋር  ያገኛሉ ። Telegram Channel ቀድመው ይደውሉ 👇 Contact us ☎️      251911120707      251904818881 📍ቦሌ መድሃኒአለም
7 933
0
በወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን የ2017 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የመማር ማስተማር ሂደት ተጀመረ በወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን የ2017 ዓ.ም የትምህርት ዘመን በተለያዩ ትምህርት ቤቶች በይፍ መጀመሩን የዞኑ ትምህርት መምሪያ ገልጿል። ተማሪዎች በተቀመጠላቸው ቀን ተገኝተው ትምህርታቸውን እየተከታተሉ መሆኑ የተነገረ ሲሆን ወደ ትምህርት ገበታቸው ያልመጡ ተማሪዎች በጊዜው ተገኝተው ትምህርታቸውን እንዲከታተሉ ወላጆች የድርሻቸውን መወጣት እንዳለባቸው መልዕክት ተላልፏል። በ2017 የትምህርት ዘመን 690 በላይ ተማሪዎች በተከዜ አንደኛ እና መካከለኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተቀብለው ለማስተማር በእቅድ መያዙን ያነሱት የትምህርት ቤቱ ርዕሰ መምህር መምህር አላምረው ፈለቀ ከ 590 በላይ ተማሪዎች መመዝገባቸውን ተናግረዋል። አንዳንድ ተማሪዎች ያልተመዘገቡ መኖራቸውን አስረድተው ምዝገባው በቀጣይም ከመማር ማስተማሩ ጎን  ለጎን ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አሳስበዋል።
عرض المزيد ...
7 051
2
آخر تحديث بتاريخ: ١١.٠٧.٢٣
سياسة الخصوصية Telemetrio