ለአመታት ውብ እግር ኳስን መጫወት መገለጫቸው ካደረጉ ክለቦች መካከል ዋነኛው አርሰናል ነው።
አርሰናልን ውብ እግር ኳስ አልተጫወትክም ብሎ መተቸት የሚያስችል ሞራል የትኛውም ክለብ የለውም ። ለእኔ በተለይ የአርሰን ቬንገሩ አርሰናል ለውብ እግር ኳስ ሲባል ዋጋ የከፈለ ቡድን አድርጌ ነው የማየው ።
አሁን በምንም መልኩ አርሰናል ጨዋታዎችን ቢያሸንፍ የውብ እግር ኳስ ባለሟል የመሆናቸውን እውነታ አይቀይረውም ። already አርሰናል ሲባል ወደ ሁሉም አእምሮ የሚመጣው ውብ ጨዋታ የሚል ነው ። ለአመታት ለፍልስፍናው ታማኝ የሆነ ክለብ ውጤት ለማግኘት አንዳንድ ቀን ውብ ኳስ ባይጫወት ትልቅ አጀንዳ ሊሆን አይገባም ።
በትላንቱ ጨዋታ ሲቲ ነጥብ እንዲያገኝ የአርሰናል ችሮታ አስፈልጎት ነበር ጨዋታው ነጥብ ከማግኘት ባሻገር የስነልቦናም ነበር ። ለሲቲ ያስተላልፉት መልእክት ግልፅ ነው
በሜዳህ ጎዶሎ እንኳን ሆኜ አላሸነፍከኝም የሚል ነው ።
ከእንግዲህ በእርግጠኝነት ሲቲ ወደ ኤምሬትስ የሚመጣው ላለመሸነፍ ይሆናል በቅርብ አመታት ሲቲ ከሜዳው ውጪ የሚቸገረው በክሎፕ ሊቨርፑል ብቻ ነበር አሁን አርሰናል ሆኗል ።
ከስፐርስ ቪላ እና ሲቲ ጋር ከሜዳው ውጪ ተጫውቶ ከ9 ነጥብ 7 ነጥብ አሳክቷል አርቴታ ሊደነቅ ሲገባ ተቺወች በዝተዋል ።
ይሄ አሳፋሪ ነገር ነው ለተቺወቹ 🙌
Credit :- Gebre Medhin ከ ሊቨርፑሉ ደጋፊ
@ZENA_ARSENAL
@ZENA_ARSENALعرض المزيد ...