“በግርምት አሰላሰልኩ፤ ይኸውም፤ እያንዳንዱ ዋጋ ያለው እና ከባድ ነገር ሁሉ ረጅም መንገድ የሚወስድ እና እሱን ለማግኘት ብዙ ጥረት የሚጠይቅ መሆኑ ነው። ሸሪዓዊ እውቀት ከምንም በላይ የተከበረ ስለሆነ በድካም ፣ እረፍት በመተው፣ ደጋግሞ በማንበብ ፣ እና ተድላዎችን እና ምቾትን በመተው ብቻ የተገኘ ነው።” 📚 صيد الخاطر (ص281)|| t.me/Sadik_Ibnu_Heyru
“በግርምት አሰላሰልኩ፤ ይኸውም፤ እያንዳንዱ ዋጋ ያለው እና ከባድ ነገር ሁሉ ረጅም መንገድ የሚወስድ እና እሱን ለማግኘት ብዙ ጥረት የሚጠይቅ መሆኑ ነው። ሸሪዓዊ እውቀት ከምንም በላይ የተከበረ ስለሆነ በድካም ፣ እረፍት በመተው፣ ደጋግሞ በማንበብ ፣ እና ተድላዎችን እና ምቾትን በመተው ብቻ የተገኘ ነው።” 📚 صيد الخاطر (ص281)|| t.me/Sadik_Ibnu_Heyru
አሁን ባለንበት ዘመን የሲህር፣ የአይንናስ፣ የቡዳና በጅን የመጠቃት ነገር እጅግ አሳሳቢ ጉዳይ ሆኗል። መፍትሄው ቀላል ከመሆኑም ጋር ብዙ እህቶች እየተሰቃዩበት ይገኛል። 👉ይህ ነገር ሰበቡ ምንድ ነው? 👉በምንድ ነው የሚወገደው? 👉ምን ማድረግ አለብን? 👉ከምን መጠንቀቅ ይገባል? የሚሉ ወሳኝ ነጥቦች መዳሰስ የግድ ሆኗል። ይህን ታሳቢ በማድረግ ይህንን አጭርና ብዙ ፋኢዳዎች የያዘን ኪታብ ለመጀመር ወስኛለሁ። አላህ ኢህላሱን ይወፍቀኝ። ኪታቡ በመግዛት ከወዲሁ በእጃችሁ ያዙ። አላህ ካለ በቅርቡ ከሶስት ቀን በኋላ የምንጀምረው ይሆናል።✍ታናሽ ወንድማችሁ ኢብኑ ኸይሩ ቂርአቱ የሚተላለፍበት ቻናል 👇👇👇👇👇👇👇👇👇 http://t.me/Sadik_Ibnu_Heyru http://t.me/Sadik_Ibnu_Heyru ሼር በማድረግ የኸይር ሰበብ ሁኑ
«እውነትን የሚፈልግ በምክር ደስ ይሰኛል፣ ስሕተቱን ሲነገረው ደስ ይለዋል «እንጂ አይከፋም»።"(ሸርሑ ኪታቢ አል – ዑቡዲያህ (252) =
አይኖቿ የሚረካበት እራት ከእናትህ ጋር መመገብ፤ ሱና ከሆነ ሐጅ ይልቅ ለአንተ የተወደደ ነው።"«ሐሠን አልበስሪይ ረሂመሁሏህ» = t.me/Sadik_Ibnu_Heyru
ከአላህ መልእክተኛ ﷺ ጋር ኢሕራም ላይ እያለን በእኛ በኩል ጋላቢዎች ያልፉ ነበር። ወደ እኛ ሲቀርቡ ከእኛ አንደኛችን ጂልባቧን ከጭንቅላቷ ላይ በፊቷ ላይ ጣል አድርጋ ትሸፈን ነበር። ሲያልፍንም እንገልጣለን።”(አቡ ዳዉድ 1833) “
ይህም የሴቷ ፊት መገለጥ በሚያስፈልግበት የኢህራም ሁኔታ ላይ እንዲህ ከተሸፈኑ፣ በሌሎች ጉዳዮች ላይ ደግሞ በይበልጥ ሊሸፈኑ ይገባል።"(ፈታዋ ለጅነቱ አድዳኢማህ (17/256) = t.me/Sadik_Ibnu_Heyru
መውሊድ የሙስሊሞች ኢድ አይደለም።
☞
መውሊድ በዲን ላይ የተጨመረ መጤ በአል ነው።🎙በአቡ አብዲላህ ኢብኑ ኸይሩ = t.me/Sadik_Ibnu_Heyru/13620
የሙሐመድ ባልደረቦች ያልፈፀሙትን ማንኛውም አምልኮት አትፈፅሙ፤ የመጀመሪያው ትውልድ ለሌላኛው ትውልድ አንድም ያስቀረው ዒባዳ የለምና።»المولد النبوي لا يحتاج حديث صحيح ❌️ القائل صوفيّ ما عنده لا حديث صحيح ولا عقل صحيح ولا قلب صحيح.❌ الحمد لله على نعمة السنة والعقل! = t.me/Sadik_Ibnu_Heyru
ﷺ
መውደድ፣ ሱናቸውን መከተል እና የህይወት ታሪካቸውን ማንበብ የእለት ተእለት ተግባር ሊሆን ይገባል እንጂ መሰረት እና ማስረጃ በሌለው በአመት አንድ ቀን ብቻ መሆን የለበትም።t.me/Sadik_Ibnu_Heyru
ኢኽዋኖች ስለመውሊድ ሲወራ ለምን ይከፋቸዋል ?➡️የኢኽዋኖች መሪ ሀሰነል በና ስለመውሊድ ምን አለ? 🎙በአቡ አብዲላህ «ኢብኑ ኸይሩ» = t.me/Sadik_Ibnu_Heyru/13610
መውሊድ ቢድአ ከመሆኑ ጋር በውስጡ የሚፈፀሙ ግልፅ ጥፋቶች!🎙በአቡ አብዲላህ «ኢብኑ ኸይሩ» = t.me/Sadik_Ibnu_Heyru/13609
መውሊድ ቢድአ መሆኑን ከሚያሳዩ መረጃዎች ውስጥ !!🎙በአቡ አብዲላህ « ኢብኑ ኸይሩ» = t.me/Sadik_Ibnu_Heyru/13608
ተጨማሪም ብዙ ነጥቦች ስለ መዉሊድ የተሰጡበት ትምህርት በቻናሉ ያገኛሉ ⇗⇗⇗»
ሰኞና ሀሙስ ስራዎች ወደ አላህ ይቀርባሉ። እኔ ደሞ ስራዬ ፃመኛ ሆኜ (ወደ አላህ) እንዲቀርብልኝ እፈልጋለሁ።📚(ኢማም አህመድ ዘግቦታል)
አሏህ የፈጠረህ እሱን ለመገዛት ነው በህይወትህ አትጫወት!ዱኒያን አሏህ የፈጠራት ላንተው ብሎ ነው! ብዙም አትድከምላት አታምልካትም!
ጀነት ወይም ጀሀነም የወደ ፊት የማይቀሩ ቤቶችህ ናቸው ከወዲሁ ተዘጋጅ።= t.me/Ibnu_Teymya_Ye_Ewket_Maed
አሏህ የፈጠረህ እሱን ለመገዛት ነው በህይወትህ አትጫወት!ዱኒያን አሏህ የፈጠራት ላንተው ብሎ ነው! ብዙም አትድከምላት አታምልካትም!
ጀነት ወይም ጀሀነም የወደ ፊት የማይቀሩ ቤቶችህ ናቸው ከወዲሁ ተዘጋጅ።= t.me/Ibnu_Teymya_Ye_Ewket_Maed
አላህ የወሰነው ውሳኔ ለምን ሆነ ከምል ፍም እሳት እስኪጠፋ ብጨብጥ እመርጣለሁ።ኢብኑ መስኡዱ قال ابن مسعود رضي الله عنه؛ لأَنْ أَعُضَّ على جَمْرَة حتى تَبْرُدَ. أَحَبُّ إليّ من أن أقول لِشيء قد قَضاه الله. لَيْتَه لم يَكُن. 📚أبوداود في الزهد١٢٨
ሙሳ ከኔ የተሻለ ነበር። ፊርዐዉን ደግሞ ካንተ የከፋ ነበር። ሆኖም ግን ሙሳ በየእለቱ ወደ ፊርዐዉን በር በተደጋጋሚ እየሄዱ ኢማንን ያቀርቡለት ነበር።(ፈዋቱል ወፊያት፣1/75) ◥በርካታ ሙስሊሞች በቆጵሮስ ጦር ታፍሰዉ በተወሰዱ ግዜም ለሀገሪቱ ክርስቲያን መሪ የሚደንቅ ረጂም ደብዳቤ ልከዉለታል። ሙስሊሞችን በርህራሃ እንድይዛቸዉና እምነታቸዉን እንዳይቀይር አሳስበዉታል። በጣም የሚደንገዉ ነገር"አልመሲሕ ቀኝ ቁንጭህን በጥፊ ለሚመታህ ግራህን አዙርለት ኩታህን ለወሰደብህ ቀሚስህን ስጠዉ,እያለ ቃል ኪዳን በማፍረስ ወይሞ ደግሞ ያልተዋጓቸዉን ሰዎች እንድሁ ማርከዉ ሊወስዱ ነዉ "እያሉ ዉስጥን የሚሞግት መልዕክት ነዉ የላኩለት። ◢በተታሮች የታፈሱ እስረኞችን ለማስለቀቅ የተታሩን መሪ ቃዛንን ባናገሩ ግዜ ሙስሊሞችን ብቻ ነጥሉ ለመልቀቅ ሲዘጋጂ ክርስቲያኖችና የሁዶችን ጭምር እንድለቅ የጠየቁትን እያወሱ ድንቅ ዲፕሎማሲያዊ ስራ ሰርተዋል። እሱንም በጣም ባማረ መልኩ ነበር ወደ ኢስላም የጠሩት። ◣
ከዚህ በኋላ ንጉሱ ለሙስሊም እስረኞች የነበረዉን አያያዝ ከማሻሻሉም ባለፈ መስጂድ ሰርቶላቸዋል ይባላል
።(መጁሙዑል ፈታዋ፡28/601_630)አልዋፊ ቢል ወፊያት ፡7/13) ◢ጂን ያለባቸዉ ሰዎች ላይ ቁርኣን እየቀሩ ያስለቅቁነበር።በዚህ ረገድ ብዙ የሚደንቁ ነገሮች አሏቸዉ።ዉጪ!ይሄነገር አልፈቅድልሽም ብሎሻል ሰዉ ይልኩ ነበር። የሚደንቀዉ በዚች ብቻ ስንቱ ያንሰራራ ነበር።አንዳንደየ እራሳቸዉ በመገኘት ቁርአን እየቀሩ ጂኖችን ያስወጡ ነበር።
አንዳደየ አመፀኛ ጂን ሲገጥማቸዉ በድብደባ ያስወጡ ነበር።ህመምተኛ ሲነቃ ግን ጭራሺ ህመሙ አይሰማዉም።ጂን በያዛቸዉ ላይ በብዛት የሚቀሩት ይህቺን አንቀፀ ነበር፦ (أَفَحَسِبْتُمْ أَنَّمَا خَلَقْنَاكُمْ عَبَثًا وَأَنَّكُمْ إِلَيْنَا لَا تُرْجَعُونَ) المؤمنون "
የፈጠርናችሁ ለከንቱ እንደሆነና እናንተም ወደኛ እንደማትመለሱ ጠረጠራችሁን ?(አል ሙእሚኑን፡115)
በተጨማሪም በአየተል ኩርሲ፣በቁል አዑዙ ቢረቢል ፈለቅና በቁል አዑዙ ቢረቢ'ንናስ ያክሙ ነበር።[ዛዱል መዓድ:4/68) ✍️ ኢንሻ አላህ ይቀጥላል.... ──────⊹⊱✫⊰⊹────── http://t.me/Sadik_Ibnu_Heyru
ለሰዉ ልጆች በሙሉ የሁለት አለም ስኬት ፣መንገዶችን ማሳያና ለህይወት አስፈላጊ ነገሮችን ሁሉ የሚያብራራ፣ህጉን ለተከተሉ የቂያም ቀን መስካሪ እንደሆነ በርካታ የቁርአን አንቀፆችና ነብያዊ ሐዲሶች ተብራርተዋል። «وَنُنَزِّلُ مِنَ ٱلۡقُرۡءَانِ مَا هُوَ شِفَاۤءࣱ وَرَحۡمَةࣱ لِّلۡمُؤۡمِنِینَ وَلَا یَزِیدُ ٱلظَّـٰلِمِینَ إِلَّا خَسَارࣰا » «
ለአማኞች ፈዉስና እዝነት የሆነን ቁርኣን እናወርዳለን፣በእርሱ በመካድ እራሳቸዉን ለበደሉ ኪሳራን እንጅ ሌላ ምንም አይጨምርላቸዉም።»«አል ኢስራእ 82» •┈┈•┈┈•⊰✿◇✿⊱•┈┈•┈┈• t.me/Sadik_Ibnu_Heyru
አዉጥተዉ ባለበት አስቀመጡት። ኢብኑ ተይሚያ ገቡና እሱኑ አንስተዉ አንዳች ቅሬታ ሳይተነፍሱ እስከሚበቃቸዉ ድረስ በልተዉ ወጡ
።(ፈዋቱል ወፊያት:1/74_75) ◢ግብፀ እያሉ ለእናታቸዉ የፃፉት ደብዳቤ ለወላጂ እናታቸዉ ያላቸዉን አክብሮት ጥልቀት የሚያሳይ ነዉ። እንድህ ይላል፦ ◣ከአሕመድ ኢብኑ ተይሚያ ወደ እድለኛዋ ወላጂ እናቴ። አላህ በፀጋዉ እርካታን ያጎናፀፍት።ድርብርብ ችሎታዉን ይለግሳት። እንድሁም ከምርጥ ሴት ባሮቹና ከአገልጋዮቹ ዉስጥ ያድርጋት።ሰላም በናንተ ላይ ይሁን የአላህ እዝነት በረከቶቹም እንድሁ። ◥እኛ ወደናንተ ያንን ከሱ በስተቀር የሐቅ አምላክ የሌለዉን አላህን እናመሰግነዋለን።እሱ ለምስጋና የተገባ ነዉ። አሱ ለሁሉም ነገር ላይ ቻይ ነዉ። የነብያት መቋጫና የአላህ ፈሪዎች ኢማም በሆኑት ባሪያዉና መልዕክተኛዉ ሙሓመድ ሶለላሁ አለይሂ ወሰለም ላይ እንድሁም በቤተሰቦቻቸዉ ላይ ሶላቱን እንድያወርድ እንጠይቀዋለን ሰላሙንም እንድያሰፍን እንድሁ። ◤ወደናንተ የላኩት ይህ ደብዳቤ ስለ ላቁ የአላህ ፀጋዎች፣ ስለተከበሩ ዉለታዎቹ፣ ስለ ግዙፍ ችሮታዎቹ ነዉ። አላህን በነሱ ላይ እናመሰግነዋለን።ከትሩፍቱ እንድጨምርልም እንጠይቀዋለን። የአላህ ፀጋዎች በበለፀጉ በጨመሩ ቁጥር ለመገመት ያታክታሉ። ◥በአሁኑ ስዓት በዚህ ሀገር መቆየታችን ለአንገብጋቢ ጉዳዮች እንደሆነ ታዉቃላችሁ።ችላ ካልናቸዉ የዱኒያም ጉዳይዎቻችን ይጠፍሉ። ወላሒ ከእናንተ መራቅ የምንመርጥ አይደለንም።ወፎች ቢሸከሙን ወደናንተ በደረስን ነበር።ነገር ግን ሰዉ ሲርቅ ምክንያቱም ከሱጋር ይርቃል። እናንተ ያለዉን ዉስጣ ዉስጥ ብታዉቁት ለአላህ ምስጋና ይገባዉና በዚህ ስዓት ይህንን(መቆየታችንን)እንጂ አትመርጡም። ◤ለአንድ ወር እንኳን በቋሚነት ለመኖር አልቆጠርንም። እንደዉም ለኛም ለእናንተም በየ ቀኑ እስቲኻራ እናደርጋለን።ከመልካሙ እንድገጥመን ዱዓ አድርጉልን። በመልካምና በሰላም ለእኛም፣ለእናንተም፣ለሙስሊሞችም በጎዉን እንድያስመርጠን የላቀዉን አላህን እንለምነዋለን። ◥ከዚህም ጋር አላህ በእርግጥም ከሚታሰበዉና ከሚገመተዉ በላይ የኸይር፣የእዝነት፣ የመቀናትና የበረከት በሮችን ከፍቶልናል። እኛ ሁለየ ለመጓዝ እንዳሰብን የጠራዉንና የላቀዉን አላህን እስቲኻራ እንዳደረን ነዉ። ስለሆነም ለናንተ ቅርብ ከመሆን ይልቅ የሆነን የዱኒያ ነገርን የምናስቀድም መስሎት ማንም ጥርጣሬን እንዳይጠረጥር። ◤ሌላዉ ቀርቶ ከዲን ጉዳይዎች እንኳን ለናንተ ቅርብ ከመሆን የሚያንስ የሆነዉን አናስቀድምም።ነገር ግን ችላ ቢባሉ ግልፀና ጠቅላይ የሆኑ ጉዳቶችን እንዳያስከትሉ የምንሰጋቸዉ ትልልቅ ነገሮች ይዘዉን ነዉ። መቼም በቦታዉ ያለ በሩቅ ያለ የማያየዉን ያያል። ◥ብቻ የምፈልገዉ ከመልካሙ እንድገጥመን ዱዓ ማድረግ ነዉ።
አላህ ያዉቃል፣እኛ አናዉቅም።እሱ ነዉ የሚችለዉ፣እኛ አንችልም።እሱ ሚስጥራትን ሁሉ እጂጉን አዋቂ ነዉ።◤ነብዩ ﷺበእርግጥ እንድህ ብለዋል፦ከሰዉ ልጁ እድለኝነቱ አላህ ካስመረጠዉ(ኢስቲኻራ)ካደረገ በኋላ በሚወሰንለት መዉደዱ ነዉ።
ከሰዉ ልጂ እድለቢስነቱ አላህ አስመርጦ በሚወስንለት መቀየሙ ነዉ። እናም ነጋዴ ተጓዥ ሲሆን ንብረቱ እንዳይጠፍበት ሲሰጋ ግዜ ነገሮች እስከሚስተካከሉ ድረስ መቆየትን ይመርጣል።እኛም ያለንበት እንድሁ ለመግለፀ የሚከብድ ነዉ። ◥ ብልሀትም ሀይልም በአላህ እንጂ የለም።
የአላህ ሰላሙ፣ እዝነቱና በረካዎቹ በናንተም፣ በትልልቁም በትንንሹም እቤት ባለዉ ሁሉ፣በመላዉ ጎረቤት፣ ቤተሰብና ጓደኞች ሁሉ በእያንዳንዱ ላይ በዝቶ ይትረፍረፍ።ምስጋና ለአላማቱ ጌታ ለአላህ ይሁን።አላህ በሙሐመድ፣በቤተሰብቻቸዉና በባልደረቦቻቸዉ ላይ ሶላቱንና ሰላሙን ያዉርድ።(አልፈተዋ 24/48_50) ✍️ይቀጥላል ኢንሻ አላህ ... ──────⊹⊱✫⊰⊹────── https://t.me/Sadik_Ibnu_Heyru
ለሱና ለሰለፍያ ቅናቻ ያላቸው እንዲሁም ከሱና የሚከላከሉ መስለው በሰለፍዮችና ሱንዮች መካከል ጥላቻ የሚዘሩ የሚያበጣብጡ ብዙ ሰዎች አሉ። ልንጠነቀቃቸው ይገባል።قال الشيخ ربيع المدخلي:
فقد تظاهر أناس بالغيرة فكان عملهم سلاحاً يفتك بالدعوة السلفية وبأهلها ويغرس بينهم العداوة والبغضاء، وهذه الأعمال ونتائجها يجب الحذر منها والتحذير منها والدعوة إلى الله بالحكمة والموعظة الحسنة والجدال بالتي هي أحسن.المجموع 4/ 139 = http://t.me/Sadik_Ibnu_Heyru
የሚለውን አትጨምር። በሀዲስ የመጣው ቢስሚላ የሚለው ነው። የዚክር ቃላቶች በቁርአንና ሀዲስ ላይ በመጣው ልክ የተገደበ ነውና። በዛ ላይ መጨመር አይቻልም።http://t.me/Sadik_Ibnu_Heyru
የጫት ሱስ አለ። የሲጋራ እንዲሁም የሽሻ። ከነዚህ የባሰ አንድ ከባድ ሱስ አለ። የቲክቶክ የዩቱብና የፌስቡክ ሱስ። ሱስ በባህሪው ይስባል። እንዳትላቀቅ ያደርጋል። ለትንሽ ጊዜ ካልተወሰደ ወይም ካልተገኘ ይጨንቃል። የሚዲያ ሱሰኞችም ባህሪ እንዲሁ ነው። ባገኙት አጋጣሚ ሁሉ እዛ ላይ ይጣዳሉ። ለአንድ ቀን ከሱ ርቀው መዋል አይችሉም። ገንዘባቸው፣ ጊዜያቸውና አቅላቸው ለማይረባ ነገር መስዋእት ያደርጋሉ። ቁርአን አይቀሩ ቂርአት የላቸው ዚክር ኢባዳ አያደርጉ በቃ አይናቸው እስኪያማቸው እዛ ላይ ያፈጣሉ። እንቅልፋቸው ራሱ ባግባቡ ስለማይተኙ ፋዞ ዝንጉ ተነጫናጭ ሆነው ይውላሉ። ይህ ነገር የጤና እክል ከማስከተሉም ጋር አሄራዊ ኪሳራም አለው። በዛላይ አብዘሀኛው ሰው እዛ ላይ የሚያየው ጤነኛ ነገር አይደለም። ሙዚቃ፣ ፊልም፣ የዘር ወሬ፣ ያምይረባ ዜና፣ የተገላለጡ ሴቶችና ሌሎችም ብዙ ጥፋቶች ይመለከታሉ። ለዛም ነው ድንገት ሰው ሲመጣባቸው ደንግጠው የሚዘጉት። በዚህ ሁሉ አላህ ፊት ተጠያቂ ናቸው። ወጣትነትህ በኢልም በኢባዳ በሀላል ስራ አሳልፈው። በዋዛ ፈዛዛ በቀልድ በጨዋታ አትግደለው። ሀራም ነገር የምታይበት ስልክ፣ ለዛ ብለህ የምትሞላው ረሲድ፣ የምታባክነው ጊዜ በዚህ ሁሉ ነገ አላህ ፊት ቆመህ ትጠየቃለህ። የዛኔ መልስህ ምን ይሁን?= t.me/Sadik_Ibnu_Heyru