Best analytics service

Add your telegram channel for

  • get advanced analytics
  • get more advertisers
  • find out the gender of subscriber
Ubicación del canal e idioma

audience statistics ኦርቶዶክስ ተዋህዶ - ‌🇴‌🇷‌🇹‌🇭‌🇴‌🇩‌🇴‌🇽 ‌🇹‌🇪‌🇼‌🇦‌🇭‌🇩‌🇴

✞✞✞ በየቀኑ አዳዲስ መንፈሳዊ ፅሁፎች ለማግኘኘት ከፈለጉ ተቀላቀሉን ✞✞✞  @orthodox1  ሁሉም እንዲያነበው share ያርጉ ለማንኛውም መረጃዎች ለመጠየቅ  @drshaye  ማናገር ይችላሉ 🇪🇹 ✝✝ኦርቶዶክስ ለዘላለም ትኑር 🇪🇹 Join Us Today And Lets learn Together ✝✝✝  @orthodox1  
Mostrar más
37 876-22
~4 219
~7
10.21%
Calificación general de Telegram
Globalmente
23 744lugar
de 78 777
182lugar
de 396
En categoría
594lugar
de 2 333

Género de suscriptores

Averigua cuántos suscriptores masculinos y femeninos tienes en el canal.
?%
?%

Idioma de la audiencia

Descubre la distribución de los suscriptores de canales por idioma
Ruso?%Inglés?%Árabe?%
Crecimiento del canal
GráficoTabla
D
W
M
Y
help

La carga de datos está en curso

Duración del usuario en el canal

Descubra cuánto tiempo permanecen los suscriptores en el canal.
Hasta una semana?%Viejos?%Hasta un mes?%
Ganancia de suscriptores
GráficoTabla
D
W
M
Y
help

La carga de datos está en curso

Hourly Audience Growth

    La carga de datos está en curso

    Time
    Growth
    Total
    Events
    Reposts
    Mentions
    Posts
    Since the beginning of the war, more than 2000 civilians have been killed by Russian missiles, according to official data. Help us protect Ukrainians from missiles - provide max military assisstance to Ukraine #Ukraine. #StandWithUkraine
    . መፃጉዕ እና ኒቆዲሞስ 【 ዮሐ ፫ / ዮሐ ፭ 】 ✥ °°°°°°°°°°°°°°°°°°° ✥ የዐቢይ ጾም ሳምንታት ከ፶ ሚሊየን ሕዝብ በላይ ባላቸው ተዋህዶን በሚያምኑ በጽባሓውያኑ ኦርቶዶክሳውያት አብያተ ክርስቲያን ዘንድ [ Eastern Christian churches adhering to Miaphysite Christology; Oriental Orthodox Churches】እኛ ከዘወረደ እስከ ሆሳዕና እንደምንዘክረው ከሆሳዕና በቀር በስያሜ የተለያየት መታሰቢያ ተሠጥቶት ይዘከራል በብዙዎቹ ① ከብካበ ቃና ☞ ② ለምጻሙን ማዳኑ ☞ ③ ሽባውን ማዳኑ ☞ ④የከነናዊቷ ሴት እምነት ልጇን ማዳኑ ☞ ⑤ እኩለ ጾም/ በዓለ መስቀል ☞ ⑥ ደጉ ሳምራዊና ጀርባዋ የጎበጠች ሴት ☞ ⑦ ዘእውሩ ተወልደ ☞ ⑧ ሆሳእና ይታሰቡበታል። በዚህ ውሥጥ በየሳምንታቱ የእነዚህ ታሪኮች መጻፍና መዘከር ምክንያቱ ታሪክ ‘አዋቆች’ ብቻ እንድንሆን አይደለም። ለምሳሌ በቅዱስ መጽሐፍ የቅዱሳን እና የርኩሳን፣ የቡሩካንና የርጉማን ፣ የጻድቃንና የኃጥዓን ታሪክ ሁሉ ተዘግቧል ምክንያቱ ደግሞ በሁለት መንገድ መረዳት ይቻላል። እንድንታነጽና እንድንገሠጽ ፩) የመልካም ሰዎች ታሪክ ⇨ ለጽናት በተስፋ ለመጽናናት “በመጽናትና መጻሕፍት በሚሰጡት መጽናናት ተስፋ ይሆንልን ዘንድ አስቀድሞ የተጻፈው ሁሉ ለትምህርታችን ተጽፎአልና።” 【ሮሜ ፲፭፥፬】 ፪) የአመጸኞች ታሪክ ⇨ ለተግሳጽ “ይህም ሁሉ እንደ ምሳሌ ሆነባቸው፥ እኛንም የዘመናት መጨረሻ የደረሰብንን ሊገሥጸን ተጻፈ።” 【፩ኛ ቆሮ ፲፥፲፩】 በዚሁ መንገድ ሊቃውንትና መና**ፍቃን ፣ የካዱና የጸኑ ፣ በጎ ሠሪዎችና ክፉ አድራጊዎች … ግለሰቦችም ታሪካቸው ተዘግቦ ተነግሯል። ዐላማው እንደቀድሞው ለሁለት ጥቅም ነው ፤ ፩) መልካም አድራጊዎች እንድናውቃቸው ምሳሌና አብነት እንድናደርጋቸው ☞ "ወአእምርዎሙ ለእለ ከመዝ ⇨ እንግዲህ እንደነዚህ ያሉትን እወቁአቸው” 【፩ኛ ቆሮ ፲፮፥፲፰】 ፪) ክፉ አድራጊዎችን ግን እንድናውቅባቸው ለመጠንቀቅ ☞ "ተዓቀቡ አንትሙሂ ወዑቅዎሙ ለከለባት ወዑቁዎሙ ለገበርተ እኪት ⇨ ከውሾች ተጠበቁ፥ ከክፉዎችም ሠራተኞች ተጠበቁ፥ ።” 【ፊል 3፥2】 መፃጉዕና ኒቆዲሞስም በ፫ ክፍል ታሪክ የዚህ መንገድ አስተማሪዎች እንዲሆኑ በዐቢይ ጾም ሰንበታት የሚታሰቡ ግለሰቦች ናቸው ✧ ክፍል 【፩】 በዮሐንስ ወንጌል ምዕራፍ ፫ እና ምዕራፍ ፭ ኒቆዲሞስ ☞ ወሐሎ አሐዱ ብእሲ ዘስሙ ኒቆዲሞስ ወመልአኮሙ ለአይሁድ ወውእቱ መጽአ ኀበ እግዚእ ኢየሱስ ቀዲሞ ሌሊቱ መፃጉዕ ☞ ወሐሎ አሐዱ ብእሲ ዘሠላሳ ወሰመንቱ ክረምቱ እምዘደወየ ወኪያሁ ርእዮ እግዚእ እግዚእ ኢየሱስ ይሰክብ ውስተ ዐራቱ ልዩነት ኒቆዲሞስ ወደ ጌታው የመጣ መፃጉዕ ጌታው ወደ እርሱ የመጣ ኒቆዲሞስ ቀድሞ በሌሊት የሚገሰግሰው ከጌታው እግር ስር ሊማር (ለትምህርት) መፃጉዕ ቀድሞ ወደ መጠመቀቂያው ውኃ ለመውረድ ደጅ የሚጠና ምኞቱ ሊማር (ለምሕረት) ኒቆዲሞስ ምሁረ ኦሪት ፣ ባለ ሥልጣንና ባለሀብት መፃጉዕ ምሁረ ደዌ ፣ ሰው የሌለው ፣ ድኃ (ንብረቱ አልጋው ብቻ) ኒቆዲሞስ ስሙ የተጠቀሰ መፃጉዕ ግን በህመሙ ደረጃ መገለጫው እንጂ በስም ያልተጠቀሰ 【የመፃጉን ስም አልተጠቀሰም መፃጉዕነት የደዌ መጽናት እንጂ ስም አለመሆኑን ልብ ይሏል ፤ ልክ እንደ አልአዛርና ነዌ (ባለጠጋው) 】 ስሙ አለመጠቀሱ ባለመታመኑ ነው፤ የጻድቃን መንገድና የታመኑ ሰዎች ስም መታወቁ በመንግሥቱ እውቅና እንዳላቸው ያስገነዝባልና “ኄር እግዚአብሔር ለእለ ይትኤገስዎ በዕለተ ምንዳቤሆሙ ወያአምሮሙ ለእለ ይፈርህዎ ⇨ እግዚአብሔር መልካም ነው፥ በመከራ ቀንም መሸሸጊያ ነው፤ በእርሱ የሚታመኑትንም ያውቃል።”።【 ናሆም 1፥7】 “እስመ እግዚአብሔር የአምር ፍኖቶሙ ለጻድቃን ወፍኖቶሙሰ ለኃጥኣን ትጠፍእ ⇨ እግዚአብሔር የጻድቃንን መንገድ ያውቃልና፥ የክፉዎች መንገድ ግን ትጠፋለች።” 【 መዝሙር 1፥6】 ✧ ክፍል ፪ በአይሁድ ክስና ውንጀላ ውስጥ ☞ መፃጉዕ ወደ አይሁድ ሔዶ ክርስቶስን ከሰሰ ☞ ለክርስቶስ መገደል ምክንያትም ሆነ በዮሐንስ ወንጌል ምዕራፍ ፭ ከቁጥር ፻፫ ጀምሮ እንደተነገው «ዳሩ ግን በዚያ ስፍራ ሕዝብ ስለ ነበሩ ኢየሱስ ፈቀቅ ብሎ ነበርና የተፈወሰው ሰው ማን እንደ ሆነ አላወቀም። ከዚህ በኋላ ኢየሱስ በመቅደስ አገኘውና፦ እነሆ፥ ድነሃል፤ ከዚህ የሚብስ እንዳይደርስብህ ወደ ፊት ኃጢአት አትሥራ አለው። ሰውዬው ሄዶ ያዳነው ኢየሱስ እንደ ሆነ ለአይሁድ ነገረ። ስለዚህም በሰንበት ይህን ስላደረገ አይሁድ ኢየሱስን ያሳድዱት ነበር ሊገድሉትም ይፈልጉ ነበር። ☞ ኒቆዲሞስ ግን አይሁድ ወደእርሱ በመጡ ጊዜ ጥብቅና የቆመና እንዳይያዝ የሞገተ ሆኑ ተገኝቷል በዮሐንስ ወንጌል ምዕራፍ ፯ ከቁጥር ፶ ጀምሮ « ከእነርሱ አንዱ በሌሊት ቀድሞ ወደ እርሱ መጥቶ የነበረ ኒቆዲሞስ፦ ⁵¹ ሕጋችን አስቀድሞ ከእርሱ ሳይሰማ ምንስ እንዳደረገ ሳያውቅ በሰው ይፈርዳልን? አላቸው።» ✧ ክፍል ፫ መጻጉዕ ፦ ጌታውን በዕለተ ዓርብ በጥፊ መትቶ የመታበት እጁ ሰሎ ቀርቶ ከደዌው የታረቀ ቀድሞ እንዲህ ሲል አስጠንቅቆት ነበር "ናሁኬ ሐየውከ ዑቅ ኢትአብስ ዳግመ እንከ ከመ ዘየአኪ ኢይርከብከ ⇨ ከዚህ በኋላ ኢየሱስ በመቅደስ አገኘውና፦ እነሆ፥ ድነሃል፤ ከዚህ የሚብስ እንዳይደርስብህ ወደ ፊት ኃጢአት አትሥራ አለው።” 【ዮሐ ፭፥፲፬ 】 እርሱ ግን "በዚያ ቆሞ የነበረው ከሎሌዎች አንዱ፦ ለሊቀ ካህናቱ እንዲህ ትመልሳለህን? ብሎ ኢየሱስን በጥፊ መታው።” 【ዮሐ ፲፰፥፳፪】 ኒቆዲሞስ ፦ በከበረና ዋጋው ውድ የሆነ ሽቱ ገዝቶ ለአምላኩ የመግነዝ ሥርዓት ፈጸመ፤ ከስውሩ ደቀመዝሙር ከአርማትያሱ ዮሴፍ ጋር ሆኖ አምላኩን ሥጋ ከመቃብር አውርዶ አካሉን በአዲስ በፍታ ሸፍኖ ወደ አዲስ መቃብር ያኖረ 【 ዮሐ ፲፱፥፴፰ እስከ ፵】 «ከዚህም በኋላ አይሁድን ስለ ፈራ በስውር የኢየሱስ ደቀ መዝሙር የነበረ የአርማትያስ ዮሴፍ የኢየሱስን ሥጋ ሊወስድ ጲላጦስን ለመነ፤ ጲላጦስም ፈቀደለት። ስለዚህም መጥቶ የኢየሱስን ሥጋ ወሰደ። ደግሞም አስቀድሞ በሌሊት ወደ ኢየሱስ መጥቶ የነበረ ኒቆዲሞስ መቶ ንጥር የሚያህል የከርቤና የእሬት ቅልቅል ይዞ መጣ። የኢየሱስንም ሥጋ ወስደው እንደ አይሁድ አገናነዝ ልማድ ከሽቱ ጋር በተልባ እግር ልብስ ከፈኑት።» ኒቆዲሞስ በልሳነ ጽርእ ኒኮዴይሞስ "Νικόδημος" ይባላል በትርጉሙ ኒኮስ (νῖκος) እና ዴይሞስ (δῆμος) አገናኝቶ መዋዔ እም ሕዝቡ ይለዋል ከሕዝቡ ድል ያደረገ "victorious among his people" ይለዋል ቤተክርስቲያናችን ሦስት ጊዜ ትዘክረዋለች ፩) የዕረፍቱን መታሰቢያ ነሐሴ ፩ ቀን ሠይማ ፪) በዐቢይ ጾም ደግሞ የ፯ኛ ሳምንት መጠሪያን ሠጥታ ፫) ለሁልጊዜው ደግሞ የቤተመቅደሱን አጥር ቅጥር እንደመግነዙ በመቁጠር የመግቢያ በሩን አዕማድ ለዮሴፍና ኒቆዲሞስ መታሰቢያ እንዲሆናቸው በማውሳት የቅዱሱን የማታ ሰው የኒቆዲሞስን በረከት በሁላችን ላይ ያሳድርብን! መልእክቱን በድምጽና በምስል ለመከታተልና ለመስማት በተከታዩን ሊንክ ታግዘው ማግኘት ይችላሉ
    Mostrar más ...
    MK TV || ዐውደ ስብከት || መፃጕዕ እና ኒቆዲሞስ || ዲ/ን ዶ/ር ቴዎድሮስ በለጠ
    Subscribe and share https://www.youtube.com/user/EOTCMK?s...... https://www.youtube.com/user/EOTCMK?s...... #MKTV #MahibereKidusan #EOTCMK
    1 776
    11
    ቸሩ ሆይ ናና // የመሠንቆ ዝማሬ በ ዲያቆን ድርሻዬ አከለ
    2 276
    1
    https://youtu.be/6EYyCyH4azs?si=KjEQF1NBsbUGtXnC ቸሩ ሆይ ናና // የመሠንቆ ዝማሬ በ ዲያቆን ድርሻዬ አከለ
    ቸሩ ሆይ ናና ❤️ የመሰንቆ ዝማሬ በ ዲያቆን ድርሻዬ አከለ // ኅብር የበገና ምሽት
    2 175
    4
    #ፈራሁ ቀኑ ከረፈደ ከመሸብኝ መጣሁ ደጃፍህ ላይ ቆምኩኝ እንዳልገባ ፈራሁ በደሌን ሳትመዝን ግቢ ብትለኝም ኃጢያቴ ከበደኝ አላራመደኝም የሰው ዕድሜው እኮ አጭር ነው ጥቂት ነው እንዴት ነው ሳላውቅህ ዘመኔ ያለቀው? ጉብዝናዬን ዓለም ስቃ ተጫውታበት እንዴት ብዬ ልርገጥ ደጅህን በድፍረት? ፈራሁ ልግባ ወይ አልግባ እንዴት ይመዘናል የአንተ ደም በእኔ እንባ ? እኔ ፈራሁ እንጂ አንተ እኮ አታስፈራም መምጣቴ ነው ደስታህ ፍቅርህ አይታማም ሽምቅቅ አለች ነፍሴ መስቀልህን ሳየው በደሌን አሰብኩት ደምህን እያየሁ ፈራሁ ልግባ ወይ አልግባ እንዴት ይመዘናል የአንተ ደም በእኔ እንባ ? በንጽህናህ ፊት እንዴት እቆማለሁ እንደ መላዕክቱ በምን እጋረዳለሁ ራሴን መሸፈኛ ክንፍ የለኝም እኔ ይታያል ኃጢያቴ የበደል ዕርቃኔ ፈራሁ ልግባ ወይ አልግባ እንዴት ይመዘናል የአንተ ደም በእኔ እንባ ? ጠዋት እና ማታ ለመጣው አንድ ነህ አምሽቶ ለገባም እኩል ትከፍላለህ አብርሃም ወይስሐቅ በድንኳንህ ቢያድሩም በአንተ መንግሥት ግን ከወንበዴ አይቀድሙም ፈራሁ ልግባ ወይ አልግባ እንዴት ይመዘናል የአንተ ደም በእኔ እንባ ?
    Mostrar más ...
    ፈራሁ | Ferahu | ዘማሪት በዛወርቅ አስፋው | Bezawork Asfaw | አዲስ መዝሙር New Orthodox Mezmur | 2024
    "ፈራሁ | Ferahu | ዘማሪት በዛወርቅ አስፋው | Bezawork Asfaw | አዲስ መዝሙር New Orthodox Mezmur | 2024 is licensed under a Creative Commons Attribution Share Alike 4.0 International License. Based on a work at https://www.youtube.com/watch?v=KdOwdsGMAfE." Ethiopian Orthodox Tewahedo Song " ፈራሁ | Ferahu | ዘማሪት በዛወርቅ አስፋው | Bezawork Asfaw | አዲስ መዝሙር New Orthodox Mezmur | 2024 " New Ethiopian Orthodox Tewahedo Mezmur 2023 © Wreb Tube is the only Channel that has exclusive rights for all Lyrics produced by Zemarit Bezawork Asfaw #ይህ_ቪዲዮ_በFacebook_ኮፒ_ራይት_የተመዘገበ_ስለሆነ_አካውንትዎ_እንዳይዘጋ_በFacebook_አይልቀቁት:: " ፈራሁ | Ferahu | ዘማሪት በዛወርቅ አስፋው | Bezawork Asfaw | አዲስ መዝሙር New Orthodox Mezmur | 2024 " New Ethiopian Orthodox Tewahedo Mezmur 2023
    5 716
    90
    ╔​✞═•┉✽✥⛪✥✽┉•═✞╗ ❀.  . ╚✞═•┉✽✥⛪✥✽┉•═✞╝          ትናንት ሚያዝያ ፬ የመፈጠራቸው ነገ ሚያዝያ ፭ ደግሞ የዕረፍታቸውን መታሰቢያ ቅድስት ቤተክርስቲያናችን የምትዘክርላቸው አባታችን አዳምና እናታችን ሔዋን በረከታቸው ይደርብርብን። ★ "ሀለዉ አዳም ወብእሲቱ (ሔዋን) እራቃኒሆሙ ወኢይትኃፈሩ ☞ አዳምና ሚስቱ ሁለቱም ዕራቁታቸውን ነበሩ፥ አይተፋፈሩም ነበር።"  【ዘፍ ፪ ፥ ፳፭】 ሁለት ዐይነት እርቃን አለ  የሚያሳፍር እና የማያሳፍር  የማያሳፍረው ራቁትነት ደግሞ የተፈቀደ እና ያለተፈቀደ ሊሆን ይችላል ዛሬ ላይ ትውልዱ ባልተፈቀደ መንገድ መራቆቱን ሳያፍርበት እንደፋሽንም እንደ ክብርም ይቆጥረዋል በቀደመው ታሪክ የቃየል ልጆች ባልተፈቀደ መራቆት አምላካቸውን ሲያሳዝኑ እንደታዩ ቅዱስ ቀሌምንጦስ ገልጧል "ርእዩ አዋልዲሁ ለቃየል በዘይሴኒ ሥነ ራእይ እንዘ የሐውራ ዕራቆን ዘእንበለ ሐፍረት  ☞ የቃየን ሴቶች ልጆች ተውበው እርቃናቸውን በመሆን ሳያፍሩ ሲንቀሳቀሱ እዩዋቸው" 【ቀሌ. ፫፥፵፱】 ታዲያ እንዲህ ባለው መንገድ ነውርን እንደ ክብር መራቆትንም  እንደ መሰልጠን ገላ መግለጥ  እንደፋሽን እያዩ የሚኖሩ መጨረሻቸው ኩነኔ እንደሆነ መጽሐፋችን ይመሰክራል  “መጨረሻቸው ጥፋት ነው፥ ሆዳቸው አምላካቸው ነው፥ ክብራቸው በነውራቸው ነው፥ አሳባቸው ምድራዊ ነው።” 【ፊል ፫፥፲፱ 】        ለሰው ልጅ አካሉን ገልጦና ሰውነቱን አራቁቶ ለመታየት የታወቀ (በቂ) ምክንያት ያስፈልጋል፤ ሠለስቱ ምዕት ለመታከም «የሚተኮስ» «የሚታገም» አካል ቢኖር አልያም ከጸበል ሊነከሩና ሊታጠቡ እንጂ በሌላውስ መንገድ በማንም ፊት እርቃን መታየት ክልክል ነው ብለዋል። "ወዓዲ ተዐቀብ ከመ ኢትትዐረቅ እምልብስከ ቅድመ መኑሂ ዘእንበለ ዳዕሙ ሶበ ይረክበከ ምክንያት ለተዐርቆ።  ☞ ዳግመኛም በማንም ፊት ከልብስህ ራቁትህን እንዳትሆን ተጠበቅ፤ የምትራቆትበት ምክንያት ቢያገኝህ ነው እንጂ" 【 ሃይ አበው ፳፥፲፪ 】 መራቆት አለመዘጋጀት እፍረት ማሳየት የመዘናጋት በበጎ ምግባር ሳይተጉ የመኖር መገለጫ ነው።   “እነሆ፥ እንደ ሌባ ሆኜ እመጣለሁ፤ ራቁቱን እንዳይሄድ እፍረቱንም እንዳያዩ ነቅቶ ልብሱን የሚጠብቅ ብፁዕ ነው።” 【ራእ  ፲፮፥፲፭】         አካልን ራቁቶ  መታየት ቀርቶ  የተራቆተ አካልም ማየት ራሱ   ሲያስነቅፍ ፣ ሲያስቀጣና ሲያስረግም እናያለን በዘፍጥረት መጽሐፍ ምዕራፍ ፱ እንደተገለጸው  በኖኅ ልጅ በካም  ላይ የደረሰው የዚህ ማሳያ ነው " ኖኅም ገበሬ መሆን ጀመረ፥ ወይንም ተከለ። ከወይን ጠጁም ጠጣና ሰከረ፤ በድንኳኑም ውስጥ ዕራቁቱን ሆነ። የከነዓን አባት ካምም የአባቱን ዕራቁትነት አየ፥ ወደ ውጭም ወጥቶ ለሁለቱ ወንድሞቹ ነገራቸው። ሴምና ያፌትም ሸማ ወስደው በጫንቃቸው ላይ አደረጉ፥ የኋሊትም ሄደው የአባታቸውን ዕራቁትነት አለበሱ፤ ፊታቸውም ወደ ኋላ ነበረ፥ የአባታቸውንም ዕራቁትነት አላዩም። ኖኅም ከወይን ጠጁ ስካር ነቃ፥ ታናሹ ልጁ ያደረገበትንም አወቀ። እንዲህም አለ፦ ከነዓን ርጉም ይሁን፤ ለወንድሞቹም የባሪያዎች ባሪያ ይሁን። እንዲህም አለ፦ የሴም አምላክ እግዚአብሔር ይባረክ፥ ከነዓንም ለእነርሱ ባሪያ ይሁን። እግዚአብሔርም ያፌትን ያስፋ፥ በሴምም ድንኳን ይደር፤ ከነዓንም ለእነርሱ ባሪያ ይሁን። " 【ዘፍ ፱፥ ፳ - ፳፯】 እንግዲህ የተራቆተን ማየት በዚህ መጠን የሚያስነቅፍ ከሆነ ተራቁቶ የመታየት ቅጣቱ የከፋ ስለመሆኑ አያጠራጥርም መራቆት የዲያቢሎስ የክብር ልጅ መሆን ነውና ፤ ሰይጣን ማለት በትርጉሙ እሩቅ እም ስብሐተ እግዚአብሔር  【ከእግዚአብሔር ክብር የተራቆተ】ማለት ነውና። የተፈቀደ የማያሳፍርም  ዕርቃን የተባለውና በጥንተ ተፈጥሮ በአዳምና በሴቲቱ ኑሮ የተገለጠው የትኛው ራቁትነት ነው? ① ራቁትነታቸው ከዚህ ዓለም ልብስ ነው አለማፈራቸው ብርሃን ለብሰው ስለነበር ነው ዓለማችን የሚያለብሰን ምድራዊና ቁሳዊ ጊዜአዊና ኃላፊ ትጥቅ ነው መንፈሳዊ ትጥቃችን  ግን ኅልፈትና ውላጤ ከሌለው ሰማያዊ  አባታችን የምንቀበለው ነውና  “የዲያብሎስን ሽንገላ ትቃወሙ ዘንድ እንዲቻላችሁ የእግዚአብሔርን ዕቃ ጦር ሁሉ ልበሱ።”  【ኤፌ ፮፥፲፩】 “እንግዲህ እንደ እግዚአብሔር ምርጦች ቅዱሳን ሆናችሁ የተወደዳችሁም ሆናችሁ፥ ምሕረትን፥ ርኅራኄን፥ ቸርነትን፥ ትህትናን፥ የዋህነትን፥ ትዕግሥትን ልበሱ፤ … በእነዚህም ሁሉ ላይ የፍጻሜ ማሰሪያ የሆነውን ፍቅርን ልበሱት ” 【ቆላ ፫፥፲፪- ፲፬】 የዓለሙ ልብስ ንፍገት ጭካኔ ቅሚያ ትዕቢት ብልጣብልጥነት ችኩልነትና ጸብእን ነው። ይህን ለብሰው የሚዋጉንን  ሥጋውያኑን በሥጋ ጦር ድል መንሳት እንዴት ይቻለናል?  የሳውልን የጦር ዕቃ የታጠቀ ካባ የለበሰና በአመጽ ወደተመላው እግዚአብሔርን ወደተገዳደረው ጎልያድ  በሥጋዊ መሳርያ ውጣ የተባለው  ብላቴናው ዳዊት መታመኛ ትምክህቱ መከታ ጉልበቱ እግዚአብሔር ስለበር በበትርና በኮሮጆው ጠጠር ዘምቶ  አመጸኛውን ሰልፈኛ ሰው ድል ነስቶታል።  “ዳዊትም ሰይፉን በልብሱ ላይ ታጠቀ፥ ገናም አልፈተነውምና መሄድ ሞከረ። ዳዊትም ሳኦልን፦ አልፈተንሁትምና እንዲህ ብዬ መሄድ አልችልም አለው። ዳዊትም አወለቀ።” 【፩ኛ ሳሙ. ፲፯፥ ፴፱】 ② አእምሮ ጠባያቸው ያላደፈ በተፈጥሮ እንደ ሕፃን  ስለነበሩ በዕርቃናቸው አይተፋፈሩም ሕጻናት በንጽሕና እንደ መላእክቱ ናቸው የእነርሱ አእምሮ ጠባይ ማደፍ ስላላገኘው ሊቁም «ንጽሖሙ ለሕፃናት በሥጋሆሙ ወነፍሶሙኒ ዘእንበለ ሕማም» ይላል። በዘመነ ሥጋዌው ክርስቶስ አምላካችንም እንደ ሕፃናት መሆን ለክብረ መንግሥቱ እንደሚያበቃ ነግሮናል “ እውነት እላችኋለሁ፥ ካልተመለሳችሁ እንደ ሕፃናትም ካልሆናችሁ፥ ወደ መንግሥተ ሰማያት ከቶ አትገቡም።” 【ማቴ ፲፰፥፫】 መልሶም እንደነርሱ ላሉቱ ስለምትሠጥነና እነርሱኑ ለመሰሉት ስለምትገባዋ ዘልዓለማዊ ርስት ይህን ደግሟል “ነገር ግን ኢየሱስ፦ ሕፃናትን ተዉአቸው፥ ወደ እኔም ይመጡ ዘንድ አትከልክሉአቸው፤ መንግሥተ ሰማያት እንደነዚህ ላሉ ናትና አለ፤”   【ማቴ ፲፱፥፲፬】  ያለቂም ያለበቀል የሚኖሩ ክፋትንና ተንኮልን አልመው አስበው ሌላው ይጎዳበት ብለው የማይፈጽሙ እንደወረቀት የሠጧቸውን የሚቀበሉ እንደውኃም ቅርጻቸው ያረፉበትን ሥፍራ የሚመስሉ ልጆች ሕጻናትን መስሎ መኖር የሚማሩትን መያዝ በበጎ አርያነት የሚመሩትን መምሰል በእጅጉ ይገባል ፤ “ጌታ ቸር መሆኑን ቀምሳችሁ እንደ ሆነ፥ ለመዳን በእርሱ እንድታድጉ አሁን እንደ ተወለዱ ሕፃናት ተንኰል የሌለበትን የቃልን ወተት ተመኙ።”【፩ኛ ጴጥ ፪፥፪-፫】 እንዲህ ያለው የሕጻናት ንጹሕ አይምሮ መያዝ አያሳፍርም። ③ ከልብሰ ኃጢዓት  ተራቁተው ኃፍረተ ነፍስ ሳይኖርባቸው ይኖሩ ነበር ሰው ኃጢዓትን ለብሶ በደል ደርቦ ከመኖር በንሰሐ ቢራቆት ተኮንና የምታፍር ነፍስ የለችውም፤  ይልቁንም የልብ ንጽሕና ማጣት የሕሊና ሞት እንደሚያመጣበት አውቆ በኃጢዓቱ ምክንያት ያገኘውን ቁስለት የልቡናው ሰንኮፍ በንሰሐ ከከከበረች ነፍሱ ቢያርቅ መንገዱን በጥንቃቄ ቢመራና በፍርሐትና በመንቀጥቀጥ ለአምላኩ ቢገዛ በግራ ከሚቆምና ተኮንነው ከሚያፍሩ በመለየት መክበር ይቻለዋል። “እናንተ ዓለመኞች ሴቶች ሆይ፥ ተጠንቀቁ፤ ተማምናችሁም የምትቀመጡ ሆይ፥ ተንቀጥቀጡ፤ ልብሳችሁን አውልቁ፥ ዕራቁታችሁን ሁኑ፥ ወገባችሁንም በማቅ ታጠቁ።”   【ኢሳ ፴፪፥፲፩】
    Mostrar más ...
    ዲ ን ዶ ር ቴዎድሮስ በለጠ የማያሳፍር ዕራቁትነት ዘፍ 2፥25
    ✝️✝️✝️የእግዚአብሔር ቃል ለሁሉ ይዳረስ ዘንድ በጸሎት ያግዙን✝️✝️✝️አዲሱን የማኅበራችንን የዩቱዩብ ቻናል +++SUBSCRIBE +++ እያደረጋችሁ ትምህርቶችን እና መዝሙሮችን እንዲደርሶት እና ለሌሎች እንዲደርሳቸው ሼር በማድረግም ይተባበሩን:: ከዚህ በፊት የተለቀቁ ትምህርቶችንና ዝማሬዎችን ለማግኘት ከስር የሚገኘውን ሊንክ ይጠቀሙ / @mahiberetsion እግዚአብሔር ያክብርልን
    3 662
    9
    ሸክም የሆነብንን ኃጢዓት አራግፈንና በደላችንን ከላያችን በማስወገድ ራስን አንጽቶ  ልብን አቅንቶ  ሕይወትን መምራት በዙፋኑ ቀኝ ሳያፍሩ ወደመክበር  ያደርሳል። “እንግዲህ እነዚህን የሚያህሉ ምስክሮች እንደ ደመና በዙሪያችን ካሉልን፥ እኛ ደግሞ ሸክምን ሁሉ ቶሎም የሚከበንን ኃጢአት አስወግደን፥ የእምነታችንንም ራስና ፈጻሚውን ኢየሱስን ተመልክተን፥ በፊታችን ያለውን ሩጫ በትዕግሥት እንሩጥ፤ እርሱ ነውርን ንቆ በፊቱም ስላለው ደስታ በመስቀል ታግሦ በእግዚአብሔር ዙፋን ቀኝ ተቀምጦአልና።”【ዕብ ፲፪፥፩-፪】 በማያሳፍር ራቁትነት በፊቱ ለመክበር ያብቃን የአቡነ አዳም የእነ ሔዋን በረከታቸው በሁላችን ይደር! ትምህርቱን  ከታች ባለው "ሊንክ በድምጽ ማግኘት ይችላሉ   
    ዲ ን ዶ ር ቴዎድሮስ በለጠ የማያሳፍር ዕራቁትነት ዘፍ 2፥25
    ✝️✝️✝️የእግዚአብሔር ቃል ለሁሉ ይዳረስ ዘንድ በጸሎት ያግዙን✝️✝️✝️አዲሱን የማኅበራችንን የዩቱዩብ ቻናል +++SUBSCRIBE +++ እያደረጋችሁ ትምህርቶችን እና መዝሙሮችን እንዲደርሶት እና ለሌሎች እንዲደርሳቸው ሼር በማድረግም ይተባበሩን:: ከዚህ በፊት የተለቀቁ ትምህርቶችንና ዝማሬዎችን ለማግኘት ከስር የሚገኘውን ሊንክ ይጠቀሙ / @mahiberetsion እግዚአብሔር ያክብርልን
    4 375
    6
    𝕿𝖊𝖜𝖔𝖉𝖗𝖔𝖘 𝕭𝖊𝖑𝖊𝖙𝖊 𝕸𝖊𝖓𝖌𝖎𝖘𝖙𝖚 Θεόδωρος (תאודור )(تواضروس) Ignatius Theophoros (Ἰγνάτιος Θεοφόρος): ╔​✞═•┉✽✥⛪✥✽┉•═✞╗ ❀.  . ╚✞═•┉✽✥⛪✥✽┉•═✞╝          ትናንት ሚያዝያ ፬ የመፈጠራቸው ነገ ሚያዝያ ፭ ደግሞ የዕረፍታቸውን መታሰቢያ ቅድስት ቤተክርስቲያናችን የምትዘክርላቸው አባታችን አዳምና እናታችን ሔዋን በረከታቸው ይደርብርብን። ★ "ሀለዉ አዳም ወብእሲቱ (ሔዋን) እራቃኒሆሙ ወኢይትኃፈሩ ☞ አዳምና ሚስቱ ሁለቱም ዕራቁታቸውን ነበሩ፥ አይተፋፈሩም ነበር።"  【ዘፍ ፪ ፥ ፳፭】 ሁለት ዐይነት እርቃን አለ  የሚያሳፍር እና የማያሳፍር  የማያሳፍረው ራቁትነት ደግሞ የተፈቀደ እና ያለተፈቀደ ሊሆን ይችላል ዛሬ ላይ ትውልዱ ባልተፈቀደ መንገድ መራቆቱን ሳያፍርበት እንደፋሽንም እንደ ክብርም ይቆጥረዋል በቀደመው ታሪክ የቃየል ልጆች ባልተፈቀደ መራቆት አምላካቸውን ሲያሳዝኑ እንደታዩ ቅዱስ ቀሌምንጦስ ገልጧል "ርእዩ አዋልዲሁ ለቃየል በዘይሴኒ ሥነ ራእይ እንዘ የሐውራ ዕራቆን ዘእንበለ ሐፍረት  ☞ የቃየን ሴቶች ልጆች ተውበው እርቃናቸውን በመሆን ሳያፍሩ ሲንቀሳቀሱ እዩዋቸው" 【ቀሌ. ፫፥፵፱】 ታዲያ እንዲህ ባለው መንገድ ነውርን እንደ ክብር መራቆትንም  እንደ መሰልጠን ገላ መግለጥ  እንደፋሽን እያዩ የሚኖሩ መጨረሻቸው ኩነኔ እንደሆነ መጽሐፋችን ይመሰክራል  “መጨረሻቸው ጥፋት ነው፥ ሆዳቸው አምላካቸው ነው፥ ክብራቸው በነውራቸው ነው፥ አሳባቸው ምድራዊ ነው።” 【ፊል ፫፥፲፱ 】        ለሰው ልጅ አካሉን ገልጦና ሰውነቱን አራቁቶ ለመታየት የታወቀ (በቂ) ምክንያት ያስፈልጋል፤ ሠለስቱ ምዕት ለመታከም «የሚተኮስ» «የሚታገም» አካል ቢኖር አልያም ከጸበል ሊነከሩና ሊታጠቡ እንጂ በሌላውስ መንገድ በማንም ፊት እርቃን መታየት ክልክል ነው ብለዋል። "ወዓዲ ተዐቀብ ከመ ኢትትዐረቅ እምልብስከ ቅድመ መኑሂ ዘእንበለ ዳዕሙ ሶበ ይረክበከ ምክንያት ለተዐርቆ።  ☞ ዳግመኛም በማንም ፊት ከልብስህ ራቁትህን እንዳትሆን ተጠበቅ፤ የምትራቆትበት ምክንያት ቢያገኝህ ነው እንጂ" 【 ሃይ አበው ፳፥፲፪ 】 መራቆት አለመዘጋጀት እፍረት ማሳየት የመዘናጋት በበጎ ምግባር ሳይተጉ የመኖር መገለጫ ነው።   “እነሆ፥ እንደ ሌባ ሆኜ እመጣለሁ፤ ራቁቱን እንዳይሄድ እፍረቱንም እንዳያዩ ነቅቶ ልብሱን የሚጠብቅ ብፁዕ ነው።” 【ራእ  ፲፮፥፲፭】         አካልን ራቁቶ  መታየት ቀርቶ  የተራቆተ አካልም ማየት ራሱ   ሲያስነቅፍ ፣ ሲያስቀጣና ሲያስረግም እናያለን በዘፍጥረት መጽሐፍ ምዕራፍ ፱ እንደተገለጸው  በኖኅ ልጅ በካም  ላይ የደረሰው የዚህ ማሳያ ነው " ኖኅም ገበሬ መሆን ጀመረ፥ ወይንም ተከለ። ከወይን ጠጁም ጠጣና ሰከረ፤ በድንኳኑም ውስጥ ዕራቁቱን ሆነ። የከነዓን አባት ካምም የአባቱን ዕራቁትነት አየ፥ ወደ ውጭም ወጥቶ ለሁለቱ ወንድሞቹ ነገራቸው። ሴምና ያፌትም ሸማ ወስደው በጫንቃቸው ላይ አደረጉ፥ የኋሊትም ሄደው የአባታቸውን ዕራቁትነት አለበሱ፤ ፊታቸውም ወደ ኋላ ነበረ፥ የአባታቸውንም ዕራቁትነት አላዩም። ኖኅም ከወይን ጠጁ ስካር ነቃ፥ ታናሹ ልጁ ያደረገበትንም አወቀ። እንዲህም አለ፦ ከነዓን ርጉም ይሁን፤ ለወንድሞቹም የባሪያዎች ባሪያ ይሁን። እንዲህም አለ፦ የሴም አምላክ እግዚአብሔር ይባረክ፥ ከነዓንም ለእነርሱ ባሪያ ይሁን። እግዚአብሔርም ያፌትን ያስፋ፥ በሴምም ድንኳን ይደር፤ ከነዓንም ለእነርሱ ባሪያ ይሁን። " 【ዘፍ ፱፥ ፳ - ፳፯】 እንግዲህ የተራቆተን ማየት በዚህ መጠን የሚያስነቅፍ ከሆነ ተራቁቶ የመታየት ቅጣቱ የከፋ ስለመሆኑ አያጠራጥርም መራቆት የዲያቢሎስ የክብር ልጅ መሆን ነውና ፤ ሰይጣን ማለት በትርጉሙ እሩቅ እም ስብሐተ እግዚአብሔር  【ከእግዚአብሔር ክብር የተራቆተ】ማለት ነውና። የተፈቀደ የማያሳፍርም  ዕርቃን የተባለውና በጥንተ ተፈጥሮ በአዳምና በሴቲቱ ኑሮ የተገለጠው የትኛው ራቁትነት ነው? ① ራቁትነታቸው ከዚህ ዓለም ልብስ ነው አለማፈራቸው ብርሃን ለብሰው ስለነበር ነው ዓለማችን የሚያለብሰን ምድራዊና ቁሳዊ ጊዜአዊና ኃላፊ ትጥቅ ነው መንፈሳዊ ትጥቃችን  ግን ኅልፈትና ውላጤ ከሌለው ሰማያዊ  አባታችን የምንቀበለው ነውና  “የዲያብሎስን ሽንገላ ትቃወሙ ዘንድ እንዲቻላችሁ የእግዚአብሔርን ዕቃ ጦር ሁሉ ልበሱ።”  【ኤፌ ፮፥፲፩】 “እንግዲህ እንደ እግዚአብሔር ምርጦች ቅዱሳን ሆናችሁ የተወደዳችሁም ሆናችሁ፥ ምሕረትን፥ ርኅራኄን፥ ቸርነትን፥ ትህትናን፥ የዋህነትን፥ ትዕግሥትን ልበሱ፤ … በእነዚህም ሁሉ ላይ የፍጻሜ ማሰሪያ የሆነውን ፍቅርን ልበሱት ” 【ቆላ ፫፥፲፪- ፲፬】 የዓለሙ ልብስ ንፍገት ጭካኔ ቅሚያ ትዕቢት ብልጣብልጥነት ችኩልነትና ጸብእን ነው። ይህን ለብሰው የሚዋጉንን  ሥጋውያኑን በሥጋ ጦር ድል መንሳት እንዴት ይቻለናል?  የሳውልን የጦር ዕቃ የታጠቀ ካባ የለበሰና በአመጽ ወደተመላው እግዚአብሔርን ወደተገዳደረው ጎልያድ  በሥጋዊ መሳርያ ውጣ የተባለው  ብላቴናው ዳዊት መታመኛ ትምክህቱ መከታ ጉልበቱ እግዚአብሔር ስለበር በበትርና በኮሮጆው ጠጠር ዘምቶ  አመጸኛውን ሰልፈኛ ሰው ድል ነስቶታል።  “ዳዊትም ሰይፉን በልብሱ ላይ ታጠቀ፥ ገናም አልፈተነውምና መሄድ ሞከረ። ዳዊትም ሳኦልን፦ አልፈተንሁትምና እንዲህ ብዬ መሄድ አልችልም አለው። ዳዊትም አወለቀ።” 【፩ኛ ሳሙ. ፲፯፥ ፴፱】 ② አእምሮ ጠባያቸው ያላደፈ በተፈጥሮ እንደ ሕፃን  ስለነበሩ በዕርቃናቸው አይተፋፈሩም ሕጻናት በንጽሕና እንደ መላእክቱ ናቸው የእነርሱ አእምሮ ጠባይ ማደፍ ስላላገኘው ሊቁም «ንጽሖሙ ለሕፃናት በሥጋሆሙ ወነፍሶሙኒ ዘእንበለ ሕማም» ይላል። በዘመነ ሥጋዌው ክርስቶስ አምላካችንም እንደ ሕፃናት መሆን ለክብረ መንግሥቱ እንደሚያበቃ ነግሮናል “ እውነት እላችኋለሁ፥ ካልተመለሳችሁ እንደ ሕፃናትም ካልሆናችሁ፥ ወደ መንግሥተ ሰማያት ከቶ አትገቡም።” 【ማቴ ፲፰፥፫】 መልሶም እንደነርሱ ላሉቱ ስለምትሠጥነና እነርሱኑ ለመሰሉት ስለምትገባዋ ዘልዓለማዊ ርስት ይህን ደግሟል “ነገር ግን ኢየሱስ፦ ሕፃናትን ተዉአቸው፥ ወደ እኔም ይመጡ ዘንድ አትከልክሉአቸው፤ መንግሥተ ሰማያት እንደነዚህ ላሉ ናትና አለ፤”   【ማቴ ፲፱፥፲፬】  ያለቂም ያለበቀል የሚኖሩ ክፋትንና ተንኮልን አልመው አስበው ሌላው ይጎዳበት ብለው የማይፈጽሙ እንደወረቀት የሠጧቸውን የሚቀበሉ እንደውኃም ቅርጻቸው ያረፉበትን ሥፍራ የሚመስሉ ልጆች ሕጻናትን መስሎ መኖር የሚማሩትን መያዝ በበጎ አርያነት የሚመሩትን መምሰል በእጅጉ ይገባል ፤ “ጌታ ቸር መሆኑን ቀምሳችሁ እንደ ሆነ፥ ለመዳን በእርሱ እንድታድጉ አሁን እንደ ተወለዱ ሕፃናት ተንኰል የሌለበትን የቃልን ወተት ተመኙ።”【፩ኛ ጴጥ ፪፥፪-፫】 እንዲህ ያለው የሕጻናት ንጹሕ አይምሮ መያዝ አያሳፍርም። ③ ከልብሰ ኃጢዓት  ተራቁተው ኃፍረተ ነፍስ ሳይኖርባቸው ይኖሩ ነበር ሰው ኃጢዓትን ለብሶ በደል ደርቦ ከመኖር በንሰሐ ቢራቆት ተኮንና የምታፍር ነፍስ የለችውም፤  ይልቁንም የልብ ንጽሕና ማጣት የሕሊና ሞት እንደሚያመጣበት አውቆ በኃጢዓቱ ምክንያት ያገኘውን ቁስለት የልቡናው ሰንኮፍ በንሰሐ ከከከበረች ነፍሱ ቢያርቅ መንገዱን በጥንቃቄ ቢመራና በፍርሐትና በመንቀጥቀጥ ለአምላኩ ቢገዛ በግራ ከሚቆምና ተኮንነው ከሚያፍሩ በመለየት መክበር ይቻለዋል።
    Mostrar más ...
    ዲ ን ዶ ር ቴዎድሮስ በለጠ የማያሳፍር ዕራቁትነት ዘፍ 2፥25
    ✝️✝️✝️የእግዚአብሔር ቃል ለሁሉ ይዳረስ ዘንድ በጸሎት ያግዙን✝️✝️✝️አዲሱን የማኅበራችንን የዩቱዩብ ቻናል +++SUBSCRIBE +++ እያደረጋችሁ ትምህርቶችን እና መዝሙሮችን እንዲደርሶት እና ለሌሎች እንዲደርሳቸው ሼር በማድረግም ይተባበሩን:: ከዚህ በፊት የተለቀቁ ትምህርቶችንና ዝማሬዎችን ለማግኘት ከስር የሚገኘውን ሊንክ ይጠቀሙ / @mahiberetsion እግዚአብሔር ያክብርልን
    1
    0
    “እናንተ ዓለመኞች ሴቶች ሆይ፥ ተጠንቀቁ፤ ተማምናችሁም የምትቀመጡ ሆይ፥ ተንቀጥቀጡ፤ ልብሳችሁን አውልቁ፥ ዕራቁታችሁን ሁኑ፥ ወገባችሁንም በማቅ ታጠቁ።”   【ኢሳ ፴፪፥፲፩】 ሸክም የሆነብንን ኃጢዓት አራግፈንና በደላችንን ከላያችን በማስወገድ ራስን አንጽቶ  ልብን አቅንቶ  ሕይወትን መምራት በዙፋኑ ቀኝ ሳያፍሩ ወደመክበር  ያደርሳል። “እንግዲህ እነዚህን የሚያህሉ ምስክሮች እንደ ደመና በዙሪያችን ካሉልን፥ እኛ ደግሞ ሸክምን ሁሉ ቶሎም የሚከበንን ኃጢአት አስወግደን፥ የእምነታችንንም ራስና ፈጻሚውን ኢየሱስን ተመልክተን፥ በፊታችን ያለውን ሩጫ በትዕግሥት እንሩጥ፤ እርሱ ነውርን ንቆ በፊቱም ስላለው ደስታ በመስቀል ታግሦ በእግዚአብሔር ዙፋን ቀኝ ተቀምጦአልና።”【ዕብ ፲፪፥፩-፪】 በማያሳፍር ራቁትነት በፊቱ ለመክበር ያብቃን የአቡነ አዳም የእነ ሔዋን በረከታቸው በሁላችን ይደር! ትምህርቱን  ከታች ባለው "ሊንክ በድምጽ ማግኘት ይችላሉ   
    Mostrar más ...
    ዲ ን ዶ ር ቴዎድሮስ በለጠ የማያሳፍር ዕራቁትነት ዘፍ 2፥25
    ✝️✝️✝️የእግዚአብሔር ቃል ለሁሉ ይዳረስ ዘንድ በጸሎት ያግዙን✝️✝️✝️አዲሱን የማኅበራችንን የዩቱዩብ ቻናል +++SUBSCRIBE +++ እያደረጋችሁ ትምህርቶችን እና መዝሙሮችን እንዲደርሶት እና ለሌሎች እንዲደርሳቸው ሼር በማድረግም ይተባበሩን:: ከዚህ በፊት የተለቀቁ ትምህርቶችንና ዝማሬዎችን ለማግኘት ከስር የሚገኘውን ሊንክ ይጠቀሙ / @mahiberetsion እግዚአብሔር ያክብርልን
    1
    0
    የበገና መዝሙር ዲ/ን አቤል ተስፋዬ ላንዴ እስከወዲያኛዉ
    የበገና መዝሙር ዲ/ን አቤል ተስፋዬ ላንዴ እስከወዲያኛዉ
    🍁 ላንዴ እስከወዲያኛው ያንን ሰው ባ’ረገኝ  ፣ ያቺንም ሴት በሆንኩ ላልወጣ ገብቼ ፡ ላልመለስ በሔድኩ ~~~~~~~~~~~~~~~ ምነው እሱን በሆንኩ ያን የቀኝ ወንበዴ ብመስለው ላ’ንድቀን : ባየው መንገዴ ለመስረቅ አይደለም ንብረት ለመቀማት አልያም ለመዝረፍ ሕይወትን ለማጥፋት በዚያ መንገድማ ከሱስ ብበልጥ እንጂ መች ከእርሱ አንስና እኔን ታውቀኝ የለ …  የወንበዴ አለቃ ያ’ጢኣተኞች ዋና ያ … ጸጸት ያዘለ በዚያች የጭንቅ ሠዓት «አስበኝ» እያለ ከመስቀልህ ጥላ ከሥር ስለዋለ ካ’ዳም ቀድሞ ገባ ምሕረት ተቀበለ እኔም እንደ ጥጦስ : ማታዬ እንዲያምር ብትለኝ ምን አለ? … «ከገነት ተጠለል: ዛሬን ከእኔ እደር» 🍁 ላንዴ እስከወዲያኛው ያንን ሰው ባ’ረገኝ  ፣ ያቺንም ሴት በሆንኩ ላልወጣ ገብቼ ፡ ላልመለስ በሔድኩ : ዛሬን ከእኔ እደር» ደ’ሞ ይህን ተመኘሁ ለንጊኖስን በሆንኩ ያቺን ዕለተ ዓርብ : ቀራንዮ በዋልኩ ለአመጽ አይደለም : ከከአይሁድ ለማበር አልያም ለመውጋት : ያንተን ጎን በጦር በዚያ መንገድማ አንተን ለማሳመም:  ማን እኔን መሰለ ስንቴ እንዳቆሰልኩህ …  ስንቴ እንደወጋሁህ : እኔን ታወቀኝ የለ! ያ …የጲላጦስ ጭፍራ በመስቀል ላይ ሳለህ በሞት በመከራ በጦሩ ቢወጋህ ሳያዝን ሳይራራ  ከቀኝ ጎን አፍስሰህ  ውኃው ከደም ጋራ በፍቅርህ ስታስረው  ዐይኑን ስታበራ ትዕግስትህን ጎትቶት   ባንተ እንደ ተጠራ ምናለ እንደው ’ኔንም … ላንተ ብቻ እንዲያድር : ልቤን ብታበራ 🍁 ላንዴ እስከወዲያኛው ያንን ሰው ባ’ረገኝ  ፣ ያቺንም ሴት በሆንኩ ላልወጣ ገብቼ ፡ ላልመለስ በሔድኩ ሰው ባ’ረገኝ  ፣ ያቺንም ምነው በመሰልኳት የቺን አመንዝራ እንደርሷ ላንድ ቀን : ከፊትህ ብጠራ ለዝሙት አይደለም ነፍሴን ለማሳደፍ አልያም ለመርከስ መቅደስክን ለማጉደፍ በዚያ መንገድማ ነውርን በመሸከም : መች ከእርሷ አንሳለሁ ሕግህን በማፍረስ … እኔን ታውቀኝ የለ : ምን እነግርሃለው ያቺን … ድኩም ዘማ በኃጢአቷ ቆስላ በበደሏ ታ’ማ ዓለም ተሰብስቦ ሕይወቷን ሊቀማ እንዲወግሯት ሳትፈርድ ቸርነትህ ቀድማ መሬቱን ስትጭር ድምጽህ ሳይሰማ ነውሯን እንደቀበርክ በከሳሽ ፊት ቆማ ዳግም አትበድዪ : በፍቅር ሂጂ እንዳልካት እንደው የኔንም ነፍስ … ምናለ መልሰህ: እንዲያ በማረካት 🍁 ላንዴ እስከወዲያኛው ያንን ሰው ባ’ረገኝ  ፣ ያቺንም ሴት በሆንኩ ላልወጣ ገብቼ ፡ ላልመለስ በሔድኩ ባ’ረገኝ  ፣ ያቺንም ሴት ✍️๏ በአግናጥዮስ  🖊 ሕዳር ካህናተ ሰማይ ፳፻፲፫ ዓ.ም ተፃፈ ☞ ከምድር ጌጥ ታላቋ ደብረ ሊባኖስ
    6 073
    42
    🌾 አንተን ማሳዘኔ በደሌ ቢበዛ ባታገኝም ከእኔ የጽድቅ መዓዛ 🌾 በምሕረትህ ብዛት አንተ ይቅር በለኝ ሥራዬን አትይ እኔ ደካማ ነኝ። 🌾 ዘወትር አለቅሳለሁ ድካሜን አውቄ መኖሬ ሲሰማኝ ከቃልህ ርቄ 🌾 በመንገድህ ምራኝ ፊትህን እንዳይ ስለ እናት ብለህ ከኔ አትለይ በዘማሪት ፋሲካ ድንቁ

    file

    4 837
    5
    የመልአከ ፀሐይ ቀሲስ መኮንን ደስታ ሥርዓተ ቀብርን በማስመልከት የተሰጠ መግለጫ መልአከ ፀሐይ ቀሲስ መኮንን ደስታ ባጋጠማቸው ህመም ምክንያት የህክምና ክትትል ሲደረግላቸው ቆይቶ ከዚህ ዓለም ድካም አርፈዋል። የመልአከ ፀሐይ ቀሲስ መኮንን ደስታ ክቡር አስከሬንም ከሀገረ አሜሪካ ወደ ትውልድ ሀገራቸው ኢትዮጵያ ገብቶ ስርዓተ ቀብራቸው እሁድ መጋቢት 15/2016 ዓ.ም በፈረንሳይ ለጋሲዮን በሚገኘው ገነተ ኢየሱ ቤ/ክ ከ4- 6 ሰዓት ይፈፀማል:: ይህንንም በማስመልከት ለመልዐከ ፀሐይ ቀሲስ መኮንን ደስታ መታሰቢያ ለማስቀመጥ ጊዜያዊ ኮሚቴ ተቃቁሞ እንቅስቃሴ ተጀምራል:: በዚህም መሰረት ይህንን የተቀደሰ አላማ ለመደገፍ የምትፈልጉ ከዚህ በታች በተጠቀሱት አካውንቶች ገቢ እንድታደርጉ እንጠይቃለን:: 1000614508497 ንግድ ባንክ 179465639 አቢሲኒያ ባንክ መልአከብርሃንሙላት ክበቤ መልአከብርሃን ቄሰ ገበዝ ተቋመ ማህቶት መምህር በላይ ወርቁ የመልዐከ ጸሐይ ቀሲስ መኮንን ደስታ የቀብር አስፈጻሚ አብይ ኮሚቴ
    Mostrar más ...
    4 882
    3
    ምግብ ልብስና ቤታችን የምኞታችን ማረፊያ፣ መድኃኔዓለም መድኃኒት ምግብ ልብስና ቤታችን፣ የኑሯችንም መሠረት ⇌⇋♧ ⇌⇋♧ ⇌⇋♧ ⇌⇋♧ ⇌⇋ ትጉህ ኖላዊ  ነው ፤  ነቅቶ የሚጠብቅ ከተራራው ወርዶ፣  ከበለስ ለበላች – ላንዷ የሚጨነቅ ከአውሬ እየታደገ ፤ እንዳንመስል ዓለሙን በመስቀል መንበር ላይ፣  አዘጋችቶ ሰጠን – ሥጋውና ደሙን  መድኃኒታችን መድኃኔዓለም   የማያልቀው ምግብ ለተራበው ዓለም  ⇌⇋♧ ⇌⇋♧ ⇌⇋♧ ⇌⇋♧ ⇌⇋ ጸጋችን ተገ’ፎ ፣ ተራቁተን ብንርቅ በቁም ሞትን ለብሰን ፣ በለስ አገልድመን –በኃጢዓት ብንደርቅ በልጅነት ሥልጣን ከክብር ሊመልሰን ከሸማኔ ጎድጓድ ፣ ከድንግል ተገኝቶ – ራሱን አለበሰን መድኃኒታችን መድኃኔዓለም የማያረጀው ልብስ ለታረዘው ዓለም  ⇌⇋♧ ⇌⇋♧ ⇌⇋♧ ⇌⇋♧ ⇌⇋ ከንቱ ቃል በመስማት ፣ ማረፊያ ስናጣ  ከገነት ተሰ’ደን ፣  ከሰማዩ መንግሥት–ወደ ምድር  ብንመጣ ተድላና ርስት ሆኖ የምንወርሰው ሀገር መንግስተ ሰማያት፣ ወንጌልና ተስፋ –እርሱ ነው እግዚአብሔር። መድኃኒታችን መድኃኔዓለም የማይፈርስ ጽኑ  ቤት  ለፈላሲው ዓለም  ⇌⇋♧ ⇌⇋♧ ⇌⇋♧ ⇌⇋♧ ⇌⇋ ⇌⇋♧ ⇌⇋♧ ⇌⇋♧ ⇌⇋♧ ⇌⇋
    Mostrar más ...
    የሕግ ፍፃሜ 🔴  "መድኃኒታችን" ዲ ዘለዓለም ታከለ (ዘጎላ) || New EP Yiheg Fetsame |  Medhanitachen l D Zelalem Takele
    #like #share #subscribe መድኃኒታችን የምኞታችን ማረፊያ፣ መድኃኔዓለም መድኃኒት ምግብ ልብስና ቤታችን፣ የኑሯችንም መሠረት ትጉህ ኖላዊ  ነው ፤  ነቅቶ የሚጠብቅ ከተራራው ወርዶ፣  ከበለስ ለበላች – ላንዷ የሚጨነቅ ከአውሬ እየታደገ ፤ እንዳንመስል ዓለሙን በመስቀል መንበር ላይ፣  አዘጋችቶ ሰጠን – ሥጋውና ደሙን  መድኃኒታችን መድኃኔዓለም የማያልቀው ምግብ ለተራበው ዓለም  ጸጋችን ተገ’ፎ ፣ ተራቁተን ብንርቅ በቁም ሞትን ለብሰን ፣ በለስ አገልድመን –በኃጢዓት ብንደርቅ በልጅነት ሥልጣን ከክብር ሊመልሰን ከሸማኔ ጎድጓድ ፣ ከድንግል ተገኝቶ – ራሱን አለበሰን መድኃኒታችን መድኃኔዓለም የማያረጀው ልብስ ለታረዘው ዓለም  ከንቱ ቃል በመስማት ፣ ማረፊያ ስናጣ  ከገነት ተሰ’ደን ፣  ከሰማዩ መንግሥት–ወደ ምድር  ብንመጣ ተድላና ርስት ሆኖ የምንወርሰው ሀገር መንግስተ ሰማያት፣ ወንጌልና ተስፋ –እርሱ ነው እግዚአብሔር። መድኃኒታችን መድኃኔዓለም የማይፈርስ ጽኑ  ቤት  ለፈላሲው ዓለም  ግጥም መጋቤ ሐዲስ ቴዎድሮስ በለጠ (ዶ/ር) ዜማ  ዘ. ዘውዱ ጌታቸው ክራር ዘ. ዘውዱ ጌታቸው መሰንቆ እንዳልካቸው አዱኛ ዋሽንት ኤልያስ ፈቃዱ ድምጽ አጃቢ ዘማሪት መቅደስ ማርዬ ድምጽ ቅጂ ሚክሲንግና ማስተሪንግ ዘጎላ ሬከርድስ
    5 730
    19
    የሕግ ፍፃሜ 🔴  "መድኃኒታችን" ዲ ዘለዓለም ታከለ (ዘጎላ) || New EP Yiheg Fetsame |  Medhan...
    የሕግ ፍፃሜ 🔴  "መድኃኒታችን" ዲ ዘለዓለም ታከለ (ዘጎላ) || New EP Yiheg Fetsame |  Medhanitachen l D Zelalem Takele
    #like #share #subscribe መድኃኒታችን የምኞታችን ማረፊያ፣ መድኃኔዓለም መድኃኒት ምግብ ልብስና ቤታችን፣ የኑሯችንም መሠረት ትጉህ ኖላዊ  ነው ፤  ነቅቶ የሚጠብቅ ከተራራው ወርዶ፣  ከበለስ ለበላች – ላንዷ የሚጨነቅ ከአውሬ እየታደገ ፤ እንዳንመስል ዓለሙን በመስቀል መንበር ላይ፣  አዘጋችቶ ሰጠን – ሥጋውና ደሙን  መድኃኒታችን መድኃኔዓለም የማያልቀው ምግብ ለተራበው ዓለም  ጸጋችን ተገ’ፎ ፣ ተራቁተን ብንርቅ በቁም ሞትን ለብሰን ፣ በለስ አገልድመን –በኃጢዓት ብንደርቅ በልጅነት ሥልጣን ከክብር ሊመልሰን ከሸማኔ ጎድጓድ ፣ ከድንግል ተገኝቶ – ራሱን አለበሰን መድኃኒታችን መድኃኔዓለም የማያረጀው ልብስ ለታረዘው ዓለም  ከንቱ ቃል በመስማት ፣ ማረፊያ ስናጣ  ከገነት ተሰ’ደን ፣  ከሰማዩ መንግሥት–ወደ ምድር  ብንመጣ ተድላና ርስት ሆኖ የምንወርሰው ሀገር መንግስተ ሰማያት፣ ወንጌልና ተስፋ –እርሱ ነው እግዚአብሔር። መድኃኒታችን መድኃኔዓለም የማይፈርስ ጽኑ  ቤት  ለፈላሲው ዓለም  ግጥም መጋቤ ሐዲስ ቴዎድሮስ በለጠ (ዶ/ር) ዜማ  ዘ. ዘውዱ ጌታቸው ክራር ዘ. ዘውዱ ጌታቸው መሰንቆ እንዳልካቸው አዱኛ ዋሽንት ኤልያስ ፈቃዱ ድምጽ አጃቢ ዘማሪት መቅደስ ማርዬ ድምጽ ቅጂ ሚክሲንግና ማስተሪንግ ዘጎላ ሬከርድስ
    13
    0
    4 734
    8
    6 596
    13
    ✝️ኑ! ቸርነትን እናድርግ ✝️ መጋቢት 15 ቀን 2016 ዓ.ም በሚሊኒየም አዳራሽ፣ +++ ገቢው በሀገራችን በተለያዩ አካባቢዎች ባጋጠመው ማኅበራዊ ቀውስና ድርቅ የተጎዱ ወገኖቻችንን፣ ገዳማትና አብነት ት/ቤቶች ለመደገፍ የሚውል። የመግቢያ ትኬቱን፡- 1. በማኅበረ ቅዱሳን ሕንጻ 4ኛ ወለል (ቤተ አብርሃም) 2. በወረዳ ማእከላት ጽ/ቤቶች 3. በማኅበረ ቅዱሳን ንዋያተ ቅድሳት መሸጫ ሱቆች 4. በማኅበረ ቅዱሳን ሕንጻ የዕለት ገንዘብ መሰብሰቢያዎች 5. በአሐዱ ባንክ ሁሉም ቅርንጫፎች 6. በሰ/ት/ቤት ጽ/ቤቶች ለበለጠ መረጃ • 09 44 71 82 82 • 09 42 40 76 60 ማኅበረ ቅዱሳን
    3 963
    3
    «ወኢትምጻእ ቅድመ እግዚአብሔር አምላክከ ዕራቀከ» በአምላክህ በእግዚአብሔር ፊት ራቁትህን አትምጣ 【ዘዳ ፲፮፥፲፮】 በዚህ መጻሕፍት ይተባበሩበታል ✧ "ወኢታስተርኢ ቅድሜየ ዕራቀከ ☞ በፊቴም አንድ ሰው ባዶ እጁን አይታይ" 【ዘጸ ፴፬፥፳】 ✧ "ወኢትትረአይ በቅድሜየ ዕራቀከ ☞ በፊቴም ባዶ እጃችሁን አትታዩ። 【ዘጸ ፳፫ ፥፲፭ / ፳፬፥፲፩】 ✧ ሲራክም "ኢትባእ ቅድመ እግዚአብሔር ዕራቀከ ☞ ወደ እግዚአብሔር ማደሪያ ባዶህን አትግባ" 【ሲራ ፴፪፥፮】 በቅድሜየ ወይም በፊቴ ማለቱ ለእግዚአብሔርስ ሁሉ ቅድሙ ወይም ፊቱ ነው፤ በሁሉ ያለና ከፊቱ የሚሸሸግ የሌለ ሆኖ ሳለ መገለጫ መክበሪያውን ሲያይ ፊቴ ይላል። ☞ በዘመነ ብሉይ በደብተራ ኦሪትና በቤተ መቅደስ በረድኤት ያድር ነበርና ☞ ዛሬም በዘመነ ሐዲስ በሥጋውና ደሙ በቤተክርስቲያን ይገለጽባታልና ከሁሉ አብልጦ ማደርያ ቤቱን ቅድሜየ አላት። ይህን ራሱ ሙሴ ሲገልጠው «ቅድመ እግዚአብሔር ፥ ውስተ መካን ዘኀርየ እግዚአብሔር አምላክከ ☞ በእግዚአብሔር ፊት ፥ እርሱ አምላክህ በመረጠው ስፍራ» ሲል አስረድቷል፤ ለሰው አካሉን ገልጦና ሰውነቱን አራቁቶ ለመታየት የታወቀ (በቂ) ምክንያት ያስፈልጋል፤ ሠለስቱ ምዕት ለመታከም «የሚተኮስ» «የሚታገም» አካል ቢኖር አልያም ከጸበል ሊነከሩና ሊታጠቡ እንጂ በሌላውስ መንገድ በማንም ፊት እርቃን መታየት ክልክል ነው ብለዋል። "ወዓዲ ተዐቀብ ከመ ኢትትዐረቅ እምልብስከ ቅድመ መኑሂ ዘእንበለ ዳዕሙ ሶበ ይረክበከ ምክንያት ለተዐርቆ። ☞ ዳግመኛም በማንም ፊት ከልብስህ ራቁትህን እንዳትሆን ተጠበቅ፤ የምትራቆትበት ምክንያት ቢያገኝህ ነው እንጂ" 【ሃይ አበው ፳፥፲፪】 ራቁትነት በውጭ ያለ (አፍኣዊ) ገላን መክደኛ ነውርን መሸፈኛ ከሆነው ጨርቅ ከመራቆት በላይ በሦስት መንገድ ውሳጣዊ እርቃንን የሚያስረዱ ሦስት መንገዶችን እናስቀምጥ ፩ኛ] ራቁት የሚለው በኃጢዓት መመላለስን በበደል መጽናትን ነው። ያንን በንሰሐ ሳያጠሩ በእግዚአብሔር ፊት መቆም የሚገባ አይደለምና። በኃጢዓት ከመውደቃቸው አስቀድሞ የማይተፋፈሩ የነበሩ አዳምና ሴቲቱ ከሕግ ሲወጡ ራቁትነትን አወቁ፤ “የሁለቱም ዓይኖች ተከፈቱ፥ እነርሱም ዕራቁታቸውን እንደ ሆኑ አወቁ፤ የበለስንም ቅጠሎች ሰፍተው ለእነርሱ ለራሳቸው ግልድም አደረጉ።” 【ዘፍ ፫፥፯】 ቅዱስ ዳዊት ይህን ድርጊት «እንሰሳትን መምሰል» ብሎታል 【መዝ ፵፰፥፲፪/፳】 አባ ጊዮርጊስም በመጽሐፈ ምሥጢር እርቃን ከመቅረት በላይ እንሰሳትን መምሰል ወዴት አለ? ብሏል “ምንት ውእቱ ተመስሎ እንስሳ ዘእንበለ ተከሥቶ ዕርቃኑ ማእከለ ዕፀዊሃ ለገነት ሶበ ነፍጸ አጽፈ ብርሃን ዘላዕሌሁ ኀደጎ አጽፈ ብርሃን ⇨ በገነት ዛፎች መካከል ዕርቃኑን ሆኖ ከመተየት በስተቀር እንስሳን መምሰል ምንድ ነው? የብርሃን ልብስ ከበላዩ ላይ በተገፈፈ ጊዜ የብርሃን መጐናጸፊየው ተለየው” ክዶ ከአምላኩ ተለይቶ የነበረው ቅዱስ ጴጥሮስ ጌታው በፊቱ በቆመ ሠዓት ለጊዜ እርቃኑን በልብስ ደብቆ ከባህር ጠልቆ መታየቱ ነውን በንሰሐ አርቆ ሥጋን በቅጣት አስጨንቆ ድኅነት እንደሚገኝ ማሳያ ነው። “ኢየሱስ ይወደው የነበረውም ደቀ መዝሙር ጴጥሮስን፦ ጌታ እኮ ነው አለው። ስለዚህ ስምዖን ጴጥሮስ ጌታ መሆኑን በሰማ ጊዜ ዕራቁቱን ነበረና ልብሱን ታጥቆ ወደ ባሕር ራሱን ጣለ።” 【ዮሐ ፳፩፥፯】 እንደ ወርቅ የተፈተነ ቃሉን በመያዝ ፣ እንደ ነጭ ልብስ የከበረውን ጸጋ ልጅነት ለማጽናት… ከፊቱ ቀርቦ መያዝ ይገባል “ባለ ጠጋ እንድትሆን በእሳት የነጠረውን ወርቅ፥ ተጐናጽፈህም የራቁትነትህ ኃፍረት እንዳይገለጥ ነጭ ልብስን፥ እንድታይም ዓይኖችህን የምትኳለውን ኵል ከእኔ ትገዛ ዘንድ እመክርሃለሁ።” 【ራእ ፫፥፲፰】 ፪ኛ) ራቁት ማለት ራስን መግለጥ ተርእዮን መሻት እግዚአብሔርን መርሳት አምላከቅዱሳንን ማስረሳት ማለት ነው። ራስን ለመስበክና ስለራስ ለማውራት እግዚአብሔር ፊት መቆም ተገቢ አይደለም። በሰማይ ያሉ አገልጋዮቹ ከመንበሩ ፊት የቆሙ መላእክቱ ፊት እግራቸውን መሸፈናቸው ለዚህ መማርያ ይሆነናል “ሱራፌልም ከእርሱ በላይ ቆመው ነበር፥ ለእያንዳንዱም ስድስት ክንፍ ነበረው፤ በሁለት ክንፍ ፊቱን ይሸፍን ነበር፥ በሁለቱም ክንፍ እግሮቹን ይሸፍን ነበር፥ በሁለቱም ክንፍ ይበር ነበር።” 【ኢሳ ፮፥፪】 ራሱን ሲሰብክ ለዋለው "ኢየሱስን ልናይ እንወዳለን ብለው ለመኑት” (ዮሐ 12፥2) የሚል መልእክት ልከው ኋላ ተመልሶ ራሱን ሰውሮ ክብረ ክርስቶስን ቢሰብክላቸው “ጌታን ባዩ ጊዜ ደስ አላቸው።” (ዮሐ20፥20) ብለው አመስግነውታል። ፫ኛ) ራቁት ማለት ባዶ እጅ ምንም ሳይዙ መምጣት ማለት ነው፤ መባዕ፣ ስእለት ፣ ምጽዋት ፣ ዐሥራት፣ በኩራት፣ ቀዳምያት እና መስዋእት ሳይይዙ ወደመቅደሱ መመረጣት የሚገባ አይደለምና። “ስጡ ይሰጣችሁማል፤ በምትሰፍሩበት መስፈሪያ ተመልሶ ይሰፈርላችኋልና፥ የተጨቈነና የተነቀነቀ የተትረፈረፈም መልካም መስፈሪያ በእቅፋችሁ ይሰጣችኋል።” 【ሉቃ ፮፥፴፰】 የእግዚአብሔር መልስ መስፈርተ ሠናየ ☞ Good measure ንሕኑሕ ☞ pressed down/deeper ምሉዕ ☞ shaken together ሕዝዙኅ ☞ Running over በስብከት መልእክቱን በተከታዩ አስፈንጣሪ ያድምጡ
    Mostrar más ...
    ዲ ን ዶ ር ቴዎድሮስ በለጠ በእግዚአብሔር ፊት ዕራቁትህን አትምጣ ዘዳ16፥16
    ✝️✝️✝️የእግዚአብሔር ቃል ለሁሉ ይዳረስ ዘንድ በጸሎት ያግዙን✝️✝️✝️አዲሱን የማኅበራችንን የዩቱዩብ ቻናል +++SUBSCRIBE +++ እያደረጋችሁ ትምህርቶችን እና መዝሙሮችን እንዲደርሶት እና ለሌሎች እንዲደርሳቸው ሼር በማድረግም ይተባበሩን:: ከዚህ በፊት የተለቀቁ ትምህርቶችንና ዝማሬዎችን ለማግኘት ከስር የሚገኘውን ሊንክ ይጠቀሙ https://www.youtube.com/channel/UCol_BHX6I-EjDdHv2Mbfsdw/videos እግዚአብሔር ያክብርልን
    4 127
    26
    እግዚአብሔርን መውደድ የእ’ሱ የሆነውን ሁሉ በመውደድ ይገለጣል! ይልቁንም የእርሱ ከሆነው ሁሉ  እርሱ የወደደውንና የሞተለትን ክቡር የሰው ልጅ መውደድ እርሱን ወደ መውደድ ያደርሳል! ሰውን መግፋት እግዚአብሔርን መርሳት ነው። አበው «ተዘክሮተ እግዚአብሔር እና ተዛውኦተ አኃው ካለው ሰው በላይ እግዚአብሔርን ከቶ ማን ይመስለዋል?»  ይላሉ! ለዐቢይ ጾም ዐቢይ ትዕዛዝ የሚያስተምር ዐበይት ሕግጋቱን የሚናገር ዝማሬ እነሆ "የሕግ ፍጻሜ" ዲያቆን ዘለዓለም ታከለ (ዘጎላ)  ዝማሬ መላእክት ያሰማልን 🙏 ከፍቅረ ቢጽ ጋራ ፍቅረ እግዚአብሔር አጽና ኦሪትና ወንጌል በሁለቱ ትዕዛዛት ተሰቅለዋልና በባልንጀራህ ላይ በከንቱ አትቆጣ የእግዚአብሔር ሰላም ከቤትህ እንዳይወጣ አድመኝነት ቁጣ ጠብና ክርክር ፀሐይዋ ሳትገባ ትተህ በፍቅር ኑር አዝ (ከፍቅረ ቢጽ ጋራ) ወደሴቲቱ አይቶ ልቡ ‘ሚያመነዝር ምኞቱ ኃጢዓት ወልዳ ከሞት ጋር የሚኖር ያለዝሙት ምክንያት ሚስቱን የሚፈታ ከሰማዩ መንግሥት የለው እድል ፈንታ አዝ (ከፍቅረ ቢጽ ጋራ) እውነት ከሆነ  አዎን ፡  ካልሆነ አይደለም በል በሰማይም በምድር  ፡ ፈጽሞ አትማል ክፉውን በክፉ ፡  ተቃውመህ አትመልስ መልካም የሆነውን በሰው ሁሉ ፊት ያዝ አዝ (ከፍቅረ ቢጽ ጋራ) እግዚአብሔርን መምሰል ራስህን አስለምድ ላሳዳጆች ጸልይ ጠላትህን ውደድ የሚረግሙህንም መርቅ እንጂ አትርገም ይህ ነው ሕገ ወንጌል  ፡ ልዝብ ቀሊል ሸክም አዝ (ከፍቅረ ቢጽ ጋራ)
    Mostrar más ...
    የሕግ ፍፃሜ 🔴  "ሕግጋተ ወንጌል" ዲ ዘለዓለም ታከለ (ዘጎላ) || New EP Yiheg Fetsame |  Hegegate wongel D Zelalem Takele
    #like #share #subscribe ሕግጋተ ወንጌል ከፍቅረ ቢጽ ጋራ ፍቅረ እግዚአብሔር አጽና ኦሪትና ወንጌል በሁለቱ ትዕዛዛት ተሰቅለዋልና በባልንጀራህ ላይ በከንቱ አትቆጣ የእግዚአብሔር ሰላም ከቤትህ እንዳይወጣ አድመኝነት ቁጣ ጠብና ክርክር ፀሐይዋ ሳትገባ ትተህ በፍቅር ኑር ወደሴቲቱ አይቶ ልቡ ‘ሚያመነዝር ምኞቱ ኃጢዓት ወልዳ ከሞት ጋር የሚኖር ያለዝሙት ምክንያት ሚስቱን የሚፈታ ከሰማዩ መንግሥት የለው እድል ፈንታ እውነት ከሆነ  አዎን ፡  ካልሆነ አይደለም በል በሰማይም በምድር  ፡ ፈጽሞ አትማል ክፉውን በክፉ ፡  ተቃውመህ አትመልስ መልካም የሆነውን በሰው ሁሉ ፊት ያዝ እግዚአብሔርን መምሰል ራስህን አስለምድ ላሳዳጆች ጸልይ ጠላትህን ውደድ የሚረግሙህንም መርቅ እንጂ አትርገም ይህ ነው ሕገ ወንጌል  ፡ ልዝብ ቀሊል ሸክም ግጥም መጋቤ ሐዲስ ቴዎድሮስ በለጠ (ዶ/ር) ዜማ ዘ. ዘውዱ ጌታቸው ክራር ዘ. ዘውዱ ጌታቸው መሰንቆ እንዳልካቸው አዱኛ ዋሽንት ኤልያስ ፈቃዱ ድምጽ ቅጂ ሚክሲንግና ማስተሪንግ ዘጎላ ሬከርድስ
    4 512
    10
    እግዚአብሔርን መውደድ የእ’ሱ የሆነውን ሁሉ በመውደድ ይገለጣል! ይልቁንም የእርሱ ከሆነው ሁሉ እርሱ የወደደውንና የሞተለትን ክቡር የሰው ልጅ መውደድ እርሱን ወደ መውደድ ያደርሳል! ሰውን መግፋት እግዚአብሔርን መርሳት ነው። አበው «ተዘክሮተ እግዚአብሔር እና ተዛውኦተ አኃው ካለው ሰው በላይ እግዚአብሔርን ከቶ ማን ይመስለዋል?» ይላሉ! ለዐቢይ ጾም ዐቢይ ትዕዛዝ የሚያስተምር ዐበይት ሕግጋቱን የሚናገር ዝማሬ እነሆ "የሕግ ፍጻሜ" ዲያቆን ዘለዓለም ታከለ (ዘጎላ) ዝማሬ መላእክት ያሰማልን 🙏 ከፍቅረ ቢጽ ጋራ ፍቅረ እግዚአብሔር አጽና ኦሪትና ወንጌል በሁለቱ ትዕዛዛት ተሰቅለዋልና በባልንጀራህ ላይ በከንቱ አትቆጣ የእግዚአብሔር ሰላም ከቤትህ እንዳይወጣ አድመኝነት ቁጣ ጠብና ክርክር ፀሐይዋ ሳትገባ ትተህ በፍቅር ኑር አዝ (ከፍቅረ ቢጽ ጋራ) ወደሴቲቱ አይቶ ልቡ ‘ሚያመነዝር ምኞቱ ኃጢዓት ወልዳ ከሞት ጋር የሚኖር ያለዝሙት ምክንያት ሚስቱን የሚፈታ ከሰማዩ መንግሥት የለው እድል ፈንታ አዝ (ከፍቅረ ቢጽ ጋራ) እውነት ከሆነ አዎን ፡ ካልሆነ አይደለም በል በሰማይም በምድር ፡ ፈጽሞ አትማል ክፉውን በክፉ ፡ ተቃውመህ አትመልስ መልካም የሆነውን በሰው ሁሉ ፊት ያዝ አዝ (ከፍቅረ ቢጽ ጋራ) እግዚአብሔርን መምሰል ራስህን አስለምድ ላሳዳጆች ጸልይ ጠላትህን ውደድ የሚረግሙህንም መርቅ እንጂ አትርገም ይህ ነው ሕገ ወንጌል ፡ ልዝብ ቀሊል ሸክም አዝ (ከፍቅረ ቢጽ ጋራ)
    Mostrar más ...
    49
    0
    ✧ ቃለ እግዚአብሔር ዘይትኀባእ በግእዘ ሕጻናት ✧ 【በሕጻናት ባህሪ የተሰወረ የእግዚአብሔር ቃል】 ሰው ምኞቱን በተስፋ እየጠበቀ ፣ ነገውን በእቅድ እየናፈቀ … ገና ብላቴና ሳለ «ወደፊት ሳድግ እንዲህ ብሆን» ይላል ። ያ በምናባችን የሳልነው ነገ በከንቱ አልፎ የምንቆጭበት ትናንት እየሆነብን እናዝናለን። የዚህች ሕጻን ንግግር ግን ወደኋላ ልጅ ሳለን እንዲህ ሆነን ቢሆን ኖሮ ያስብለናል። በዚህ መንገድ የቀረጻችሁ ቤተሰቦች ብድር ይግባችሁ! ልጃችሁን ባልተለወጠ አንደበት በተመጠነ እድገት በቤቱ ያሰንብትላችሁ🙏
    ለመጠየቅ ፈራሁ!! እጹብ ድንቅ ልጆች የሃረገወይን #etsubdinklijoch #comedianeshetu #ethiopia
    የወጌሻ ዩትዩብ ስልጠና | እስታንዳፕ ኮሜዲ | የእየሩሳሌም ጉዞ እና እጹብ ድንቅ ልጆች ጠቁሞ ለመመዝገብ ከታች ይምረጡ 👇 https://tally.so/r/3ldYl5 ውድ የዶንኪትዩብ ቤተሰቦቻችን የእጹብ ድንቅ ልጆች ፕሮግራማችንን በድጋሜ እነሆ!!! የዛሬ ፕሮግራም እንግዳችን ህጻን ሃረገወይን ቀለሙ ትባላለች እድሜዋ 4 ሲሆን የመጣችው ከቡሬ ነው።ሃረገወይን በቤተክርስቲያን ትምህርቶች ታንጻ ያደገች ልጅ ናት ። እጅን በአፍ የሚያስጭን ተሰጦ ያላት እንዲሁም የሊቀሊቃውንት አባ ገብረኪዳንን ትምህርቶችን በቃሏ ሸምድዳለች ከእነሱም መካከል በዚህ ቪዲዮ ታቀርባለች። የምትሰራቸውን ቪዲዮዎች ሚሊዮኖች በቲክቶክ ተመልክተዋል! ከ800ኪ.ሜ ርቀት በብራና የተጻፈ ደብዳቤ ይዛ መጥታለች ደብዳቤው ላይ ምን ተጽፎ ይሁን? አብረን እንመልከት! Welcome to DonkeyTube, the home of inspiring esub dinklijoch children's programs! In today's episode, we have a very special guest joining us - the adorable 4-year-old Hargeweyn kelemu from Bure. Hargeweyn has captured the hearts of millions with her incredible talents and unique gift. Hargewein's journey began when a video of her went viral on TikTok, captivating viewers from all around the world. But there's more to this little superstar than meets the eye. Hargewein possesses a remarkable ability - she has a hand to mouth gift, which she will share with us today. But that's not all! Hargewein's story takes an even more extraordinary turn. She recently received a letter written on parchment, all the way from a distant location 800 km away. Join us as we explore the contents of this mysterious letter together. What should be written on the letter? Let's see together!
    6 061
    9
    በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ፩ አምላክ   የህንጻ ቤተክርስቲያን ምርቃት ጥሪ ፡፡፡፡፡፡፡፡፡።።።።።።።።።፡፡።።።።።።።።። ኑ" የእግዚአብሔርንም ሥራ አዩ                           (መዝ66÷5) በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ/በአ/አ/ሀ/ስ/በን/ስ/ላ/ክ/ከተማ ቤ/ክ/የምስራቀ ፀሐይ ለቡ መርጡለ አርሴማ ገዳም ቀደም ሲል  ክቡር መልአከ ጽዮን  ቆሞስ አባ እስጢፋኖስ ይርጋ ወደዚህ ደብር በዋና አስተዳዳሪነት ተመድበው በመጡበት ሰዓት በሚያደርጉት የጉብኝት ወቅት ቦታው መሀል ከተማ ተቀምጦ እንዴት የቅድስት አርሴማ ጽላት ቆርቆሮ በቆርቆሮ በሆነ መቃኞ ውስጥ ይቀመጣል በማለት መንፈሳዊ ቁጭት አድሮባቸው  የአካባቢው ምዕመናንም ህንጻ ቤ/ክ እንዲሰራ ፍላጎት ስላላቸው  ዋና አስተዳዳሪው ሳይውሉ ሳያድሩ ልዩ ትኩረት በመስጠት ብዙ ውጣ ውረዶችን አልፈው እግዚአብሔርን ይዘው የንስሐ ልጆቻቸው የሆኑትን አክሊለ ስማዕትና ወለተ ሐና የተባሉ  እግዚአብሔር የመረጣቸው ባልና ሚስቶች የቅድስት አርሴማን ህንጻ  ቤተክርስቲያን እንዲሰሩ  በማሳመን በራሳቸው ወጪ ብቻ  ውሃ አንኳን ከቤተክርስቲያን ሳይጠቀሙ በገንዘብ እየገዙ ማንም ሳይጨመር  በደብሩ ዋና አስተዳዳሪ ክቡር መልአከ ጽዮን ቆሞስ አባ እስጢፋኖስ ይርጋ የየዕለት ክትትል በ1 ዓመት ከ4 ወር ህንጻ ቤተክርስቲያኑ በፈቃደ እግዚአብሔር እጀግ  ዘመኑን በዋጀና ባማረ ሁኔታ ተሠርቶ ተጠናቆ የካቲት 9 ቀን2016 ዓ/ም እና የካቲት 10 ቀን 2016 ዓ/ም .ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ለቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት .ብፁዕ አቡነ አብርሃም የጠቅላይ ቤተክህነት ጠቅላይ ዋና ስራአስኪያጅ እና የባህር ዳር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ .ብፁዕ አቡነ ሄኖክ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና የተዋህዶ ሚዲያ ማዕከል የበላይ ጠባቂ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት የጠቅላይ ቤተክህነትና የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የየመምሪያ ኃላፊዎች በተገኙበት እጅግ ባማረና በደመቀ ሁኔታ  የህንጻ ቤተክርስቲያኑ ምርቃት ይከናወናል ። :::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::     በመሆኑም አርስዎም በዕለቱ ተገኝተው የበረከቱ ተሳታፊ እንዲሆኑ  እና ላልሰሙት ያሰሙ ዘንድ በሰማዕቷ ቅድስት አርሴማ ሰም መንፈሳዊ ጥሪአችንን እናስተላልፋለን ።                            የደብሩ ሰ/ጉ/አ/ጽ/ቤት Mewi Events Our passion is your perfect event. For Bookings ☎️ 0979338787                                  0910611517
    Mostrar más ...
    4 043
    8
    4 443
    7
    ✧ THE ENCOMIUM OE BISHOP ABBA THEODOTUS [THE MARTYRDOM AND MIRACLES OF SAINT GEORGE OF CAPPADOCIA. THE COPTIC TEXTS EDITED WITH AN ENGLISH TRANSLATION ERNEST A. WALLIS BUDGE, M. A] Pp. 307 ✧ The Passion of St. George Translated by E. A. W Budge Written by Abba Theodotus, Bishop of Ancyra in Glaatia in 431 AD. Pp. 18 በተራራው ላይ ጥር ፲፰ ቀን ስለተደረው ገቢረ ተአምራት ገድሉ በተጨማሪነት ከላይ በርእስነት ያነሳነውን ቃል በሰማዕቱ ሕይወት ውሥጥ እያየ እንዲህ ይነግረናል ☞ ወጸውኦ እግዚእነ ኢየሱስ ክርስቶስ ለማር ሰማዕት ቅዱስ ጊዮርጊስ በቃሉ አምላካዊ … ወሶቤሐ ተንስአ ከመ መርዓዊ ዘይወጽእ እምጽርሑ እንዘ አልቦ ሕማም ለግሙራ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ሰማዕቱን ቅዱስ ጊዮርጊስን በአምላካዊ ቃሉ ጠራውና "የመረጥኩህ ወዳጄ ጊዮርጊስ ሆይ አሁን ከእንቅልፍህ ተነሥ አትፍራ፡፡ የማዝህ በመከራህ ሁሉ ከአንተ ጋር ያለሁት አምላክህ እኔ ክርስቶስ ነኝ" አለው፡፡ ያን ጊዜም ቅዱስ ጊዮርጊስ ሙሽራ ከጫጉላው እንደሚወጣ ምንም ሕማም ሳያገኘው ተነሣ፡፡ ደብረ አሱርዮን የክርስቶስ ሙሽራ ሰማዕተ ጽድቅ ቅዱስ ጊዮርጊስን ለመጨረሻው መከራ ለሦስተኛው ሞት የወለደች የሰርግ አዳራሹ ናት። የቀደሙቱ በፈተና ሲጨነቁ በጸሎታቸው እንዲህ የምትል የልብ ለልብ ተማጽኖ ለሰማዕቱ ያደርሳሉ። «ተማኅጸንኩ በዝርወተ አጽምከ በደብረ ይድራስ በድው በአምሳለ ጸበል ወሐመድ በእደ ሠገራት እደው ጊዮርጊስ ኄር ጊዮርጊስ አፈው ምርሐኒ ለፍቁርከ እምፆታ ፈቃድ ምንትው በኀበ አስተርአየ ወፈቀደ መለኮት ሕያው» በግጥም ወደኛው ስንመልሰው ይኽን ሐሳብ ይዟል በአጥንቶችህ ተማጽኛለሁ በተራራው የይድራስ አጸድ በጠባቂዎች እጅ በተበተነው እንደ ትቢያና እንደ አመድ ቸር የምትባል ጊዮርጊስ ምግባርህም የሚያውድ ወዳጅህን አንተው ምራኝ ከሥጋ ፈቃድ መንታ መንገድ በሚገለጥበት ጎዳና ሕያው የመለኮት ፈቃድ 🙏አሜን 🙏 መልካም በዓል ✍️ በቴዎድሮስ በለጠ ጥር ዝርወተ አጽሙ ለቅዱስ ጊዮርጊስ ፳፻፲፮ ዓ.ም. [📍ከደብረ ወርቅ አትርፎ ቅዱስ ጊዮርጊስ]
    Mostrar más ...
    5 305
    7
    ውእቱሰ ከመ መርዓዊ ዘይወጽእ እምጽርሑ አርሱም ከእልፍኙ እንደሚወጣ ሙሽራ ነው °°°°°°°°°°[መዝሙር ፲፰(፲፱)፥ ፭ ]°°°°°°°° ቅዱስ ዳዊት ነገሩን የሚያነሳው "ወውስተ ፀሐይ ሴመ ጽላሎቶ ☞ በፀሐይ ክበብ ውሥጥ ጸዳሉን አደረገ (በእነርሱም ውስጥ የፀሐይን ድንኳን አደረገ)" በማለት ነው። መልሶም ያ ፀሓይ ከጫጉላ የወጣ ሙሽራን ይመስላል [ውእቱሰ ከመ መርዓዊ ዘይወጽእ እምጽርሑ] በማለት ፀሐዩን በሙሽራ እየመሰለ በማሕጸነ ድንግል የተደረገውን ድንቅ ምሥጢረ ሥጋዌና ነገረ ተዋህዶ ወደእኛ እያቀረበ የበተስፋ ይተነብያ አራቅቆ ይተነትናል። መተርጉማኑ ምሳሌስ ከተመሰለለት ነገር ቢያንስ እንጂ እንደምን ይበልጥ ብለው (ምሳሌ ዘየሐጽጽ ባለው) መምሰልስ ሙሽራው ነው ፀሐይን የሚመስለው እንጂ እንዴት ፀሐይ ሙሽራን ይመስላል ይላል ? ብለው ወደዘመኑ ተመልሰው ራሱን ዳዊትን ይጠይቁታል! ይመልስላቸዋል እንዲህ ብለው ይታረቁታል «መመሳሰል የጋራ ነው ብሎ እንዲህ አለ» ፤ ከዚህ አለፍ ብለው ደግሞ ሙሽራውን የፀሐይ ፈጣሪ መርዓዊ ሰማያዊ ክርስቶስ ሆኖ ፀሐይም ራሱ ፀሐየ ጽድቅ አማኑኤል ብለው አንዱን በአንዱ እያወዳጁ ምሥጢሩን በነገረ ምሳሌ ያስማሙታል። ቅዱሱ ነቢይ የትንቢቱ ማረፊያ የሚያደርገው በፀሐይነቱ ውሳጣዊ ዓይናችን ብሩህ ያደረገልንንና የሕሊናችንን ጨለማ አርቆ ከእርሱ በሚገኝ እውቀት ያከበረንን እውነተኛ ብርሃን ቅዱሳኑን በጸጋ ብርሃን ያሰኛቸውን አምላካችን ክርስቶስን ነው እንደሙሽራ ከጫጉላ ቤቱ ከሰርግ አዳራሹ የወጣ ያለው ። ክርስቶስ ፀሐይ °°°°°°🌞°°°°°° እርሱ ፀሐየ ጽድቅ ክርስቶስ ምሥራቅና ጽባህ ከተባለች እናቱ ድንግል ሲወጣ ከቆጥ ተሰቅሎ ከማገር ተንጠልጥሎ ያለ ሁሉ እንደሚገለጥ በእርሱም ፊት አንዳች የማይሠወር ፀሐይ [አልቦ ዘይትኀባእ እምላኅቡ] የተባለ፤ እርሱ ፀሐየ ዘጽድቅ ክርስቶስ በዙፋኑ ከተቀመጠ ንጉሥ አንስቶ በአደባባይ እስከወደቀ ጽኑስ ሁሉ ሊያየው የሚመኝ የሚረባ የሚጠቅም በመንገዱም ለመሮጥ ደስ የሚሰኝ አርበኛ ፀሐይ [ይትፌሳሕ ከመ ይርባሕ ዘይሜርድ ፎኖቶ] የተባለ፤ እርሱ ፀሐየ ዘጽድቅ ክርስቶስ ከባህሪው በሚገኘው ብርሃን የምድርን ጨለማ ያራቀ በጽድቁ ኃጢኣትን በእውቀቱ ድንቁርናን በንጽሕናው ርኩስን ያስወገደ ፀሐይ [ንጹሕ ወይሜይጣ ለነፍስ] የተባለ፤ የከበረች ቤተክርስቲያንን ለራሱ ሙሽሪት ያደረገና እንደሰርግ ቤት (ጫጉላ) የእናቱ ድንግል ማርያምን ማሕጸን ንጽሕት አዳራሽ አድርጎ ሥጋችንን ነስቶ የተዋሐደን የማይጠልቅ ፀሐይ የተባለው ሙሽራው ክርስቶስ በቅዱሳኑ ላይ አድሮባቸው የሚኖርና የዓለም ብርሃን ያደረጋቸው ☀️ጊዮርጊስ ጸሐይ☀️ ፀሐይን የሚገልጥ ፀሐይ ጊዮርጊስ ፀሐየ ልዳ ፀሐይም ቁምነገር ሁኖ ቅዱሳንን በዚህ መመሰላችን የሚነደው መብዛዙ ያሳዝናል፤ እንኳን በምግባር በሃይማኖት የተገለጠ ቅድስና ብቻውን የሰውነት ተፈጥሮ ከፀሐይ የላቀ ነበር። መጽሐፍ እንዲህ ይላል "ከፀሐይ የሚነጻ ምን አለ? እርሱስ እንኳ ያልፋል፤ እንዲህ መሆን ሳለ ደማዊና ስጋዊ (ሰው) ክፉ ነገር ያስባል" 【ሲራ ፲፯፥፴፩】 ፀሐይ ይደንቃችኋል? ቅድስናን የባህሪ ገንዘቡ ያደረገ የበጎ ሥጦታና ፍጹም በረከት ምንጭ የተለዩ ፣ የከበሩ ፣ የነጹና የጸኑ ቅዱሳኑን መርጦ በፀጋው ቅድስና ከፍ የሚያደርግ አምላካችን ክርስቶስ ፦ በኑሯቸው እርሱን የመሰሉት በሕይወታቸው የተገለጠ ቅዱሳንን አድሮባቸው ሲኖር ክብራቸው ከፀሓይ እጥፍ ድርብ (Resplendently) የሚያበራ እንደሆነ በወንጌል ነግሮናል! “በዚያን ጊዜ ጻድቃን በአባታቸው መንግሥት እንደ ፀሐይ ይበራሉ።” 【ማቴ ፲፫፥፵፫】 ሊያውም በሃይማኖታቸው ጽናትና በምግባራቸው ተጋድሎ የጽድቃቸው መገለጫ የሆነው ብርሃን ጉድለት ሳይኖርበት የሚጨምር እንደሆነ ጠቢቡ ሰሎሞን ይመሰክራል “የጻድቃን መንገድ ግን እንደ ንጋት ብርሃን ነው፥ ሙሉ ቀን እስኪሆንም ድረስ እየተጨመረ ይበራል።” 【ምሳ ፬፥፲፰】 በልዳ ምሥራቅነነት ለክርስትናው አርበኝነት ሲወጣና ሲያበራ የታየው ቅዱስ ጊዮርጊስ የልዳው ፀሐይ ነው! 🌟 ጊዮርጊስ ኮከብ 🌟 ወደ ኮከብ የሚመራ ኮከብ ጊዮርጊስ ኮከበ ፋርስ መክብበ ሰማዕታት ኮከበ ክብር ወመስተጋድል ቅዱሱ መንፈሳዊ አርበኛ ጊዮርጊስ ጨለማ በነገሠበት ሥቃይና መከራ በሠለጠነበት ምድራችን በሃይማኖቱ ጽናት በተጋድሎውም ትጋት በላይኛው ሰማይ በከበረች ነፍሱ እንደ ኮከብ ብሩህ ነው። "ወለነፍሰ ጻድቃንሰ ከመ ከዋክብት ብሩሃት በመልዕልተ ሰማያት" 【፩መቃ ፴፮፥፵】 በተለይም ደግሞ በዛሬዋ ኢራን የቀድሞዋ ፋርስ (persia) ለብዙዎች ከስሑታን ፍኖት መመለስና በእውነተኛው ሃይማኖት መጽናት አብነት ሆኖ በማለፉ ኮከበ ፋርስ ተብሏል። “ብዙ ሰዎችንም ወደ ጽድቅ የሚመልሱ እንደ ከዋክብት ለዘላለም ይደምቃሉ።”【ዳንኤል ፲፪፥፫】 ክርስቶስ ያደመቃቸው ከዋክብት ከእርሱ የተገኙ የእርሱ ስለሆኑ መርተው ወደ እርሱ ያደርሳሉ በዚኽች ጥንት ምሥራቃዊት (ጽባሓዊቷ) ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያናችን በኩል ያየነው ይህ ፍጡነ ረድኤት ኮከብ እንደ ሰብአ ሰገል ፈጥኖ እየመራ እንድንገዛለት ያደርገናል። "ርኢነ ኮከበ ዚአሁ በምሥራቅ ወመጻእነ ከመ ንስግድ ሎቱ ☞ የእርሱን ኮከብ በምሥራቅ ዐይተን ልንሰግድለት መጥተናል" 【ማቴ. ፪፥፪】 ደብረ ይድራስ ጽርሐ መርዓሁ ለጊዮርጊስ ጊዮርጊስ የክርስቲስ ሙሽራ እልፍኙ የይድራስ ተራራ °°°🏔°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°⛰️°°° ይድራስ የሚለው ቃል ምድረ በዳ ማለት እንደሆነ የገድለ ቅዱስ ጊዮርጊስ ጸሐፊ የእንቆራው ኤጲስ ቆጶስ ቅዱስ ቴዎዶጦስ (Saint Theodotus of Ancyra) ይነግረናል። ☞ ወአዲ አዘዘ ይንሥኡ እምድር ከመ ይጹሩ ሐመደ ሥጋሁ ለቅዱስ ወይሰድዎ በከበሮ ወያዕርግዎ ኀበ ደብር ልዑል ዘስሙ ይድራስ ዘውእቱ መካነ በድው ብሂል ወይዘርዉ በነፋስ መልዕልተ ደብር ከመ ኢይርከብዎ ክርስቲያን ሐመደ ሥጋሁ ወወዓልትሂ ዘረዉ ሐመደ ሥጋሁ ውስተ ደብር ወተመይጡ ዳግመኛም የቅዱሱን የሥጋውን አመድ አፍሰው በመውሰድ በቀፎ አድርገው ትርጓሜው ምድረ በዳ የሆነ ስሙ ይድራስ ተብሎ ወደ ሚጠራ ታላቅ ተራራ ላይ ክርስቲያኖች የሥጋውን አመድ እዳያገኙት በነፋስ እንዲያዘሩት አዘዘ፤ ጭፍሮቹም የሥጋውን አመድ በተራራ ላይ በትነው ተመለሱ። የተራራውን ትክክለኛ መጠሪያ ስም በሚመለከት በገላትያ ላለችው እንቆራ ኤጲስ ቆጶስ የነበረው ብፁዕ ቴዎዶጦስ [The blessed Abba Theodotus, Bishop of Ancyra in Galatija] የእውነት ፀሐይ የንጋት ኮከብ (The sun of the truth☀️, the star of the morning🌟) እያለ ጠርቶ ያከብረውና በዱድያኖስ በኩል ከደረሰበት ጸዋትወ መከራ አንዱ ሥጋውን አቃጥለው አመድ አድርገው ከፍ ወዳለ ተራራ ይዘውት እንደወጡና በዚያም እንደበተኑት አመልክቶ የተራራውንም ስም ደብረ አሱርዮን ብሎ አስቀምጧል። Then Dadianus made them take his ashes up to a high mountain called Asurion, and they scattered them on the mountain to the winds. ለበለጠ መረጃ ተከታዮቹን የውጪ ምንጮች ከገድለ ቅዱስ ጊዮርጊስ ጋር ለተጨማሪ ማስረጃ ያገናዝቡ
    Mostrar más ...
    3 782
    8
    2 980
    3
    "ወቀዊሞ ማዕከለ ሕያዋን ወሙታን ከተረ መዓተ" 【መጽሐፈ ጥበብ ምዕራፍ ፲፰ ቁጥር ፳፫】 °✞°°°°°°°°°°°°°°°✥°°°°°°°°°°°°°°°°†°() «አሁንስ አበዛችሁት!» ይላሉ ዳታንና አቤሮን እንዲሁም ሐሳባቸውን የገዙ ቆሬና ልጆቹ【ዘኁ. ፲፮፥፫】 የዛሬዎቹን ‘ሁላችን የሀዲስ ኪዳን ካህናት ነን’ ባዮቹን መስለውና በሙሴ ፊት በመቆም ‘አሮንን ብቻ ማን ካህን አደረገው እኛስ ካህን ለመሆን ምን ያንሰናል?’ እያሉ ጨምረው እንዲህ ይላሉ «ማኅበሩ ሁላቸውም እያንዳንዳቸው ቅዱሳን ናቸው» ወይ መመሳሰል እንዴት ይደንቃል! ራሳችሁን ቅዱሳን ቅዱሳን እያላችሁ የምትጠራሩና የምትንጠራሩ ደቂቀ ዳታን ውሉደ አቤሮን ኧረ አድቡ። በእግዚአብሔር ምርጫ ላይ አፍ የሚከፍቱትን መሬት ተከፍታ ውጣቸዋለች እኮ! ዛሬ በውሥጥ በውጪ የቸገረ ነገር የሆነው እንዲህ ዐይነቱ ግብረ ዕቡያን ነው። ⇄ በውሥጥ «አሁንስ እጅግ አበዛችሁት!» እያሉ ከመንበረ ፓትርያርክ ውጪ <መንበረ ሃሮ ዘኦሮሚያ> እና <መንበረ አክሱም ዘትግራይ> እያሉ ራሳቸውን በየሰፈራቸው የቀባቡና የተቀባቡ በሥልጣነ መለኮት ላይ የተሳለቁ የጥምቀት ማግሥት ጉዶች አየን። ⇆ በውጭ ክርስቲያን ነን የሚሉ ደፍረው ራሳቸውን ቅዱስ እያሉ የጠሩ ባለክህነት ለመሆንስ ማን ከልክሎን ብለው በዘፈቀደ የሚሿሿሙ! ውጤቱ ምን ነበር? ሙሴ ለቆሬ ልጆች «እጅግ ያበዛችሁትስ እናንተ ናችሁ» 【ዘኁ ፲፮፥፯】እኛ አልከለከልናችሁ ተፈቀደልን ካላችሁ በሉ ከእግዚአብሔር ጠይቃችሁ አግኙት አላቸው ፤ እነ ሙሴ እነ አሮነን ተሰበሰቡ በጉዳዩ ወደ እግዚአብሔር አመለከቱ ከዚያ ጠሯቸው « አንመጣም! በእኛ ላይ ራስህን አለቃ ታደርጋለህ?" አሉ 【ዘኁ ፲፮፥፲፪/፲፫】 አወይ መመሳሰላችን እናንተዬ። ዛሬም አስኬማውን ከማጀት እንደተገኘ የቤታቸው ድስት አጥልቀው በየጎሳቸው የሚሮጡ ሲጠሩ እምቢኝ ብለው በየጓዳው የሚቀላውጡ አቤሮናውያን አየን። ብቻ ተክህነናል ያሉቱ መሬት ተከፍታ ዋጠቻቸው 250ዎቹን አጣኝ ነን ባዮች ደቂቀ ቆሬና 14,700 ተከታዮቻቸውን መቅሰፍት እሳት ከሰማይ ወርዳ በልታቸዋለች። ያን ጊዜ ካህኑ አሮን ወደቀሩት ሕያዋን መቅሰፍት እሳቱ እዳይሻገር ከሙታኑ መንደር እንዲቀር በመካከል ቆሞ ያጥን ጀመር ያን ጊዜ ። ‘ወበማዕከሎሙ ቀዊሞ ከተረ መዓተ’ ይለዋል። “በሙታንና በሕያዋን መካከል ቆመ፤ መቅሠፍቱም ተከለከለ።” 【ዘኁ ፲፮፥፵፰】 ጠቢቡ ሰሎሞን ላለፈው የካህኑ አሮንን ለሚመጣው የሊቀ ካህናቱ የክርሰቶስን አይቶ ነገሩን እንዲህ እያለ በጥበብ መጽሐፍ ያስተምርበታል። "ወቀዊሞ ማዕከለ ሕያዋን ወሙታን ከተረ መዓተ አኮ በኃይለ ሥጋ ወኢበግብረ ንዋየ ሐቅል አላ በቃለ ዚአከ በዘአዘከረ ሎቱ መሐላ አበው ወኪዳኖሙ ☞ በሥጋዊ ኃይልና ለጦርነት በሚሆን መሣርያ አይደለም በራስህ ቃል ለቅዱሳን አበው የማለውን መሐላ የገባላቸውን ቃልኪዳን አስቦ በሞታንና በሕያዋን መካከል ቆሞ መዓቱን ከተረ/አቆመ " 【ጥበ. ፲፰፥፳፫】 የቀደመው አሮን በሙታኑና በሕያዋኑ መካከል ቆሞ "ተዘከር አብርሃምሃ ወይስሐቅሃ ወያዕቆብሃ ዘመሐልከ በርእስከ ☞ ለአብርሃም ለይስሐቅና ለያዕቆብ በራስህ የማልከውን መሐላ አስብ" እያለ መዓቱን ከለከለ መቅሰፍቱን አቆመ። ከተራ ይለዋል እንዲህ ያለውን የመዓቱን መቆም የምሕረቱን መምጣት! ቀዳማዊና ደኃራዊ ፊተኛውና ኋላኛው ዘልዓለማዊው የሐዲሱ ኪዳን ሊቀ ካህናት ክርስቶስ "የማታውቁት በመካከላችሁ ቆሟል" ተብሎ በበረኛው በዮሐንስ መጥምቅ የተመሰከረለት የነፍሳችን እረኛ በጥምቀቱ በኦሪታውያኑ ምውታንና በሀዲስ ኪዳኑ ሕያዋን መካከል ቆሞ በቁጣው እሳት በአዳም ዘር ላይ የነደደውን መርገማችንን ደምስሶ መዓቱን በምሕረት መልሶ ባርነቱን አቆመልን። ይህ ነው። ① የበጉ እናት የሊቀ ካህናቱ ወላዲት እመቤታችን ድንግል ማርያም ስለዚህ ከተራ መዓቱን አርቆ ምሕረቱን ልኮ ድኅነቱ ስለተሠጠበት ምሥጢር ይህን ትሰብክልናለች “እንደዚህ ለአባቶቻችን ምሕረት አደረገ፤ ለአባታችን ለአብርሃምም የማለውን መሐላውን ቅዱሱን ኪዳን አሰበ” 【ሉቃስ ፩፥፸፪-፸፫】 ② ይህን ከተራ ከድግል እመቤታችን ቀጥላ የሰበከችው አንቀጽ የተባለች ዮርዳኖስ ናት፤ ራሷ ቆማና ሸሽታ ከተራውን በተግባር እየመሰከረች “አንቺ ባሕር የሸሸሽ፥ አንቺም ዮርዳኖስ ወደ ኋላሽ የተመለስሽ፥ምን ሆናችኋል?” 【መዝ ፻፲፬፥፭】 ③ በጥምቀቱ የተፈጸመልንን የነገረ ከተራውን ምስክርነት ዐጻዌ ኆኅት፣ ጺያሔ ፍኖት የተባለ መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ እንዲህ ሲል ለሦስተኛ ጊዜ አጽንቶታል “በነገው ዮሐንስ ኢየሱስን ወደ እርሱ ሲመጣ አይቶ እንዲህ አለ፦ እነሆ የዓለምን ኃጢአት የሚያስወግድ (የሚከትር) የእግዚአብሔር በግ።” 【ዮሐ ፩፥፳፱】 ከተራ የሚለው ቃል በቁሙ ከመነሻው ከተረ ብሎ ዘጋ አቆመ አገደ ከለከለ ማለት ነው በቀረበ አውድ ደግሞ ከበበ ዐጠረ ዙሪያውን ያዘ ማለትም ይሆናል በተከበበ ገንዳ በታጠረ ሥፍራ ጥምቀቱን ከከተራ አንስተን ማክበራችን ለዚሁ ነው። ከወንጌሉ ክፍል ለማጠቃለያ የሚሆነንን አንድ ምንባብ እናንሳና ነገረ ከተራችንን እንቋጭ "እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ ወደ በጎች በረት በበሩ የማይገባ በሌላ መንገድ ግን የሚወጣ እርሱ ሌባ ወንበዴም ነው፤ በበሩ የሚገባ ግን የበጎች እረኛ ነው። ለእርሱ በረኛው ይከፍትለታል፤ በጎቹም ድምፁን ይሰሙታል፥ የራሱንም በጎች በየስማቸው ጠርቶ ይወስዳቸዋል። የራሱንም ሁሉ ካወጣቸው በኋላ በፊታቸው ይሄዳል፥ በጎቹም ድምፁን ያውቃሉና ይከተሉታል፤ ከሌላው ግን ይሸሻሉ እንጂ አይከተሉትም፥ የሌሎችን ድምፅ አያውቁምና" የዮሐንስ ወንጌል ምዕራፍ ፲ ከቁጥር ፩―፲ በበሩ የማይገቡ «ቅዱሳን ነን ካህናት ነን» ባዮች ብዙ ወንበዴዎች አሉ። እነዚህ መዓት የማይከተርላቸው እሳተ ሲዖል የሚበላቸው የገሃነም አፍ የሚውጣቸው ናቸው። ሊቃውንቱ በሩን ወደእርሱ መግባትን ያገኘንባት እረኛችን ክርስቶስ እኛን ያገኘባት የምሥጢራቱ መግቢያ ቅድስት ጥምቀት ናት ይሉናል። ☞ ኖላዊ ኄር ዘይቤ እግዚእነ ወመድኃኒነ ኢየሱስ ክርስቶስ ውእቱ (‹‹ቸር ጠባቂ›› ያለው ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።) ☞ ወአንቀጽኒ ፈለገ ዮርዳኖስ ውእቱ (‹‹በርም›› የዮርዳኖስ ወንዝ(ጥምቀት) ነው።) ☞ ወዐጻዊሰ ዮሐንስ መጥምቅ ውእቱ (‹‹በረኛውም›› ዮሐንስ መጥምቅ ነው፡፡) ☞ ወዐጸድ መንግሥተ ሰማያት ይእቲ ( ‹‹ስፍራም›› መንግሥተ ሰማያት ናት፡፡ ) አበው ሲተርቱ «ባጤ ሞት የተከተረ በስለት የተመተረ አንድ ነው» ይላሉ። ለእኛ የሕይወታችን ዐጤ የነፍሳችን ንጉሠ ነገሥት ክርስቶስ ከሥፍራችን እንዳንታጣ ከቤቱ እንዳንወጣ በሞት ሳይሆን በሕይወት እንዲከትረን ከዘልዓለማዊ ዐጸድ ከሰማይ ቤቱ እንዳንጎድልና በፍርዱ ሠይፍ እንዳንመተር ከሥላሴ ልጅነታችን ከተዋህዶ ሃይማኖታችን አያናውጸን። ✍️ በቴዎድሮስ በለጠ ከተራ ፳፻፲፮ ዓ.ም. ከደቡብ ሱዳን ጁባ ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክርስቲያን
    Mostrar más ...
    4 935
    17
    3 750
    6
    "ወቀዊሞ ማዕከለ ሕያዋን ወሙታን ከተረ መዓተ" 【መጽሐፈ ጥበብ ምዕራፍ ፲፰ ቁጥር ፳፫】 °✞°°°°°°°°°°°°°°°✥°°°°°°°°°°°°°°°°†°() «አሁንስ አበዛችሁት!» ይላሉ ዳታንና አቤሮን እንዲሁም ሐሳባቸውን የገዙ ቆሬና ልጆቹ【ዘኁ. ፲፮፥፫】 የዛሬዎቹን ‘ሁላችን የሀዲስ ኪዳን ካህናት ነን’ ባዮቹን መስለውና በሙሴ ፊት በመቆም ‘አሮንን ብቻ ማን ካህን አደረገው እኛስ ካህን ለመሆን ምን ያንሰናል?’ እያሉ ጨምረው እንዲህ ይላሉ «ማኅበሩ ሁላቸውም እያንዳንዳቸው ቅዱሳን ናቸው» ወይ መመሳሰል እንዴት ይደንቃል! ራሳችሁን ቅዱሳን ቅዱሳን እያላችሁ የምትጠራሩና የምትንጠራሩ ደቂቀ ዳታን ውሉደ አቤሮን ኧረ አድቡ። በእግዚአብሔር ምርጫ ላይ አፍ የሚከፍቱትን መሬት ተከፍታ ውጣቸዋለች እኮ! ዛሬ በውሥጥ በውጪ የቸገረ ነገር የሆነው እንዲህ ዐይነቱ ግብረ ዕቡያን ነው። ⇄ በውሥጥ «አሁንስ እጅግ አበዛችሁት!» እያሉ ከመንበረ ፓትርያርክ ውጪ <መንበረ ሃሮ ዘኦሮሚያ> እና <መንበረ አክሱም ዘትግራይ> እያሉ ራሳቸውን በየሰፈራቸው የቀባቡና የተቀባቡ በሥልጣነ መለኮት ላይ የተሳለቁ የጥምቀት ማግሥት ጉዶች አየን። ⇆ በውጭ ክርስቲያን ነን የሚሉ ደፍረው ራሳቸውን ቅዱስ እያሉ የጠሩ ባለክህነት ለመሆንስ ማን ከልክሎን ብለው በዘፈቀደ የሚሿሿሙ! ውጤቱ ምን ነበር? ሙሴ ለቆሬ ልጆች «እጅግ ያበዛችሁትስ እናንተ ናችሁ» 【ዘኁ ፲፮፥፯】እኛ አልከለከልናችሁ ተፈቀደልን ካላችሁ በሉ ከእግዚአብሔር ጠይቃችሁ አግኙት አላቸው ፤ እነ ሙሴ እነ አሮነን ተሰበሰቡ በጉዳዩ ወደ እግዚአብሔር አመለከቱ ከዚያ ጠሯቸው « አንመጣም! በእኛ ላይ ራስህን አለቃ ታደርጋለህ?" አሉ 【ዘኁ ፲፮፥፲፪/፲፫】 አወይ መመሳሰላችን እናንተዬ። ዛሬም አስኬማውን ከማጀት እንደተገኘ የቤታቸው ድስት አጥልቀው በየጎሳቸው የሚሮጡ ሲጠሩ እምቢኝ ብለው በየጓዳው የሚቀላውጡ አቤሮናውያን አየን። ብቻ ተክህነናል ያሉቱ መሬት ተከፍታ ዋጠቻቸው 250ዎቹን አጣኝ ነን ባዮች ደቂቀ ቆሬና 14,700 ተከታዮቻቸውን መቅሰፍት እሳት ከሰማይ ወርዳ በልታቸዋለች። ያን ጊዜ ካህኑ አሮን ወደቀሩት ሕያዋን መቅሰፍት እሳቱ እዳይሻገር ከሙታኑ መንደር እንዲቀር በመካከል ቆሞ ያጥን ጀመር ያን ጊዜ ። ‘ወበማዕከሎሙ ቀዊሞ ከተረ መዓተ’ ይለዋል። “በሙታንና በሕያዋን መካከል ቆመ፤ መቅሠፍቱም ተከለከለ።” 【ዘኁ ፲፮፥፵፰】 ጠቢቡ ሰሎሞን ላለፈው የካህኑ አሮንን ለሚመጣው የሊቀ ካህናቱ የክርሰቶስን አይቶ ነገሩን እንዲህ እያለ በጥበብ መጽሐፍ ያስተምርበታል። "ወቀዊሞ ማዕከለ ሕያዋን ወሙታን ከተረ መዓተ አኮ በኃይለ ሥጋ ወኢበግብረ ንዋየ ሐቅል አላ በቃለ ዚአከ በዘአዘከረ ሎቱ መሐላ አበው ወኪዳኖሙ ☞ በሥጋዊ ኃይልና ለጦርነት በሚሆን መሣርያ አይደለም በራስህ ቃል ለቅዱሳን አበው የማለውን መሐላ የገባላቸውን ቃልኪዳን አስቦ በሞታንና በሕያዋን መካከል ቆሞ መዓቱን ከተረ/አቆመ " 【ጥበ. ፲፰፥፳፫】 የቀደመው አሮን በሙታኑና በሕያዋኑ መካከል ቆሞ "ተዘከር አብርሃምሃ ወይስሐቅሃ ወያዕቆብሃ ዘመሐልከ በርእስከ ☞ ለአብርሃም ለይስሐቅና ለያዕቆብ በራስህ የማልከውን መሐላ አስብ" እያለ መዓቱን ከለከለ መቅሰፍቱን አቆመ። ከተራ ይለዋል እንዲህ ያለውን የመዓቱን መቆም የምሕረቱን መምጣት! ቀዳማዊና ደኃራዊ ፊተኛውና ኋላኛው ዘልዓለማዊው የሐዲሱ ኪዳን ሊቀ ካህናት ክርስቶስ "የማታውቁት በመካከላችሁ ቆሟል" ተብሎ በበረኛው በዮሐንስ መጥምቅ የተመሰከረለት የነፍሳችን እረኛ በጥምቀቱ በኦሪታውያኑ ምውታንና በሀዲስ ኪዳኑ ሕያዋን መካከል ቆሞ በቁጣው እሳት በአዳም ዘር ላይ የነደደውን መርገማችንን ደምስሶ መዓቱን በምሕረት መልሶ ባርነቱን አቆመልን። ይህ ነው። ① የበጉ እናት የሊቀ ካህናቱ ወላዲት እመቤታችን ድንግል ማርያም ስለዚህ ከተራ መዓቱን አርቆ ምሕረቱን ልኮ ድኅነቱ ስለተሠጠበት ምሥጢር ይህን ትሰብክልናለች “እንደዚህ ለአባቶቻችን ምሕረት አደረገ፤ ለአባታችን ለአብርሃምም የማለውን መሐላውን ቅዱሱን ኪዳን አሰበ” 【ሉቃስ ፩፥፸፪-፸፫】 ② ይህን ከተራ ከድግል እመቤታችን ቀጥላ የሰበከችው አንቀጽ የተባለች ዮርዳኖስ ናት፤ ራሷ ቆማና ሸሽታ ከተራውን በተግባር እየመሰከረች “አንቺ ባሕር የሸሸሽ፥ አንቺም ዮርዳኖስ ወደ ኋላሽ የተመለስሽ፥ምን ሆናችኋል?” 【መዝ ፻፲፬፥፭】 ③ በጥምቀቱ የተፈጸመልንን የነገረ ከተራውን ምስክርነት ዐጻዌ ኆኅት፣ ጺያሔ ፍኖት የተባለ መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ እንዲህ ሲል ለሦስተኛ ጊዜ አጽንቶታል “በነገው ዮሐንስ ኢየሱስን ወደ እርሱ ሲመጣ አይቶ እንዲህ አለ፦ እነሆ የዓለምን ኃጢአት የሚያስወግድ (የሚከትር) የእግዚአብሔር በግ።” 【ዮሐ ፩፥፳፱】 ከተራ የሚለው ቃል በቁሙ ከመነሻው ከተረ ብሎ ዘጋ አቆመ አገደ ከለከለ ማለት ነው በቀረበ አውድ ደግሞ ከበበ ዐጠረ ዙሪያውን ያዘ ማለትም ይሆናል በተከበበ ገንዳ በታጠረ ሥፍራ ጥምቀቱን ከከተራ አንስተን ማክበራችን ለዚሁ ነው። ከወንጌሉ ክፍል ለማጠቃለያ የሚሆነንን አንድ ምንባብ እናንሳና ነገረ ከተራችንን እንቋጭ "እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ ወደ በጎች በረት በበሩ የማይገባ በሌላ መንገድ ግን የሚወጣ እርሱ ሌባ ወንበዴም ነው፤ በበሩ የሚገባ ግን የበጎች እረኛ ነው። ለእርሱ በረኛው ይከፍትለታል፤ በጎቹም ድምፁን ይሰሙታል፥ የራሱንም በጎች በየስማቸው ጠርቶ ይወስዳቸዋል። የራሱንም ሁሉ ካወጣቸው በኋላ በፊታቸው ይሄዳል፥ በጎቹም ድምፁን ያውቃሉና ይከተሉታል፤ ከሌላው ግን ይሸሻሉ እንጂ አይከተሉትም፥ የሌሎችን ድምፅ አያውቁምና" የዮሐንስ ወንጌል ምዕራፍ ፲ ከቁጥር ፩―፲ በበሩ የማይገቡ «ቅዱሳን ነን ካህናት ነን» ባዮች ብዙ ወንበዴዎች አሉ። እነዚህ መዓት የማይከተርላቸው እሳተ ሲዖል የሚበላቸው የገሃነም አፍ የሚውጣቸው ናቸው። ሊቃውንቱ በሩን ወደእርሱ መግባትን ያገኘንባት እረኛችን ክርስቶስ እኛን ያገኘባት የምሥጢራቱ መግቢያ ቅድስት ጥምቀት ናት ይሉናል። ☞ ኖላዊ ኄር ዘይቤ እግዚእነ ወመድኃኒነ ኢየሱስ ክርስቶስ ውእቱ (‹‹ቸር ጠባቂ›› ያለው ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።) ☞ ወአንቀጽኒ ፈለገ ዮርዳኖስ ውእቱ (‹‹በርም›› የዮርዳኖስ ወንዝ(ጥምቀት) ነው።) ☞ ወዐጻዊሰ ዮሐንስ መጥምቅ ውእቱ (‹‹በረኛውም›› ዮሐንስ መጥምቅ ነው፡፡) ☞ ወዐጸድ መንግሥተ ሰማያት ይእቲ ( ‹‹ስፍራም›› መንግሥተ ሰማያት ናት፡፡ ) አበው ሲተርቱ «ባጤ ሞት የተከተረ በስለት የተመተረ አንድ ነው» ይላሉ። ለእኛ የሕይወታችን ዐጤ የነፍሳችን ንጉሠ ነገሥት ክርስቶስ ከሥፍራችን እንዳንታጣ ከቤቱ እንዳንወጣ በሞት ሳይሆን በሕይወት እንዲከትረን ከዘልዓለማዊ ዐጸድ ከሰማይ ቤቱ እንዳንጎድልና በፍርዱ ሠይፍ እንዳንመተር ከሥላሴ ልጅነታችን ከተዋህዶ ሃይማኖታችን አያናውጸን። ✍️ በቴዎድሮስ በለጠ ከተራ ፳፻፲፮ ዓ.ም. ከደቡብ ሱዳን ጁባ ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክርስቲያን
    Mostrar más ...
    1
    0
    መ) ከዜማ ቤቱ ደግሞ ዮሐንስን በብሔረ ሕያዋን አየሁት የሚለን የኘቅዱስ ያሬድ ነው። በድጓው ደጋግሞ ምስክርነቱን ሠጥቶናል «ይኔጽር ዓየራተ ይነግር ኅቡዓተ እንዘ ይጽሐፍ በእደዊሑ ዘወንጌል ቃላተ በቅናተ እግዚኡ ሐቌሁ ቀነተ ዮሐንስ ድንግል ዘኢጥዕመ ሞተ » 【በድጓ በግእዝ አርያሙ ክፍል ለጥር ፬ቱ ቁመት መነሻ እንዲሆን የጻፈልን ነው። ብራና ገጽ ፻፺፩】 በንጽሕና በድንግልና የኖረው ዮሐንስ ሞትን አልቀመሰም ይልና በሌላም ሥፍራ ከሞት ተለይቶ እንደመላእክቱ በሕይወት አለ ሲል ዳግመኛ ምስክርነቱን እንዲህ እያለ ያጸናዋል «በንጽሕ ከመ መላእክት ተሠርገወ ወእመዊት ከማሆሙ ሐይወ» ሠ) በመልኩ ክፍልና በገድለ ሐዋርያት ማጠቃለያ የመሰወሩ ምስክርነት ተቀምጦ እናገኛለን « ሰላም ለልብስከ ወለአሣእኒከ ደርገ፤ ተዝካረ ሕይወትከ ያዑቅ ለአብሮኮሮስ ዘተኃድገ፤ ዮሐንስ ዘኮንከ ምስለ መላእክት ዘውገ፤ ምሉዓ ወድግዱገ ዘሰላምከ ፈለገ፤ በውሣጤ ከርሥየ ኢይኩን ንቱገ፡፡ » 【የመኖርህን ነገር ያስረዳ ዘንድ ለተተወ ፤ ለልብስህ ከጫማህ ጋር ክብር ይገባል፤ ከመላእክት ጋር ወዳጅ የሆንክ ዮሐንስ ሆይ! ሞልቶ የተትረፈረፈ የፍቅር አንድነትህ ወንዝ በሆዴ ውስጥ የጎደለ አይሁን /ይሙላ/።】 ረ) የሊቃውንት ቅኔ ለጊዜው በዝክረ ሊቃውንት ከተዘገቡት ሁለቱን ልጠቁም « ወልደ ነጐድጓድ ተሰደ እንዘ የኀድግ ሀገረ፤ እምኅበ አጥፍአ ሞተ ሰብእ ሦረ፤ ገራህቱ መቅበርት አምጣነ አብቈለት ሣዕረ» «ዘማ መቅበርት ለወልደ ነጎድጓድ ትቤሎ፤ እመ ትጸልአኒ አንተ ዘያፈቅረኒ ሀሎ» ሰ) ከውጭ የተገኙ ቀደምት ምንጮች በውጭ ሀገራት ቀደምት ድርሳናትና ሊቃውንትም ዘንድ ቢሆን ከላይ ያነሳነውን ጭብጥ የሚደግፍ ታሪክ ተመዝግቦ ይገኛል። . በሌላ ሥፍራ የተገኘው ደግሞ ይህን ይላል ቅዱስ ዮሐንስ የሚነጠቅበት ሠዓት እንደደረሰ ሲያውቅ በመስቀል ቅርጽ የተሰናዳ መቃብር እንዲያዘጋጁለት አርድእቱን አዟል እነርሱም በበዛ እንባ መምህራቸውን እየሳሙ ካለመታዘዝ እንዳይቆጠርባቸው ፊቱን በጨርቅ ሸፍነው ወደ መቃብሩ ሥፍራ አኑረውት ሄደዋል። ከደቀ መዛሙርቱ አንዱ ( ቅዱስ አብሮኮሮስ) ወደቦታው ተመልሶ ቢመጣ መቃብሩን ቢከፍተው ባዶ ሆኖ አግኝቶታል። «He bade them prepare for him a cross-shaped grave, in which he lay, telling his disciples that they should cover him over with the soil. The disciples tearfully kissed their beloved teacher, but not wanting to be disobedient, they fulfilled his bidding. They covered the face of the saint with a cloth and filled in the grave. Learning of this, other disciples of Saint John came to the place of his burial. , they found it empty.» በአብሮኮሮስ ስለተሠጠው ምስክርነት (testimony of St. Prochorus) ደግሞ ተከታዩት አስረጂ በሊንኩ ታግዘው ቢያዩ የበከጠ ሐሳባችንን ያግዛል። ✧ ለማስማማት በሚነሳው የማስታረቂያ ሐሳብ በኤፌሶን/ ቱርክ የመቃብሩ ሥፍራ ይህ ነው እየተባለ ዛሬም ለጎብኚዎች ይታያል። ይሁንና ግን ☞ገራህቱ መቅበርት አምጣነ አብቈለት ሣዕረ ፣ ☞ልብሱ ለዮሐንስ ወአሣእኑ ዘተኃድገ ለአብሮኮሮስ ከመ ያዑቅ ሕይወቱ ፣ ☞ When they opened the grave, they found it empty ከሚሉቱ ሳይስማማ ሞቷል ለሚሉቱ ድጋፍ መስሎ ቀርቧል። በመላእክት ቢሎ በደቀመዛሙርቱ መቃብሩ መዘጋጀቱ እውነት ቢሆንም ሥጋው ከዚያ መታጣቱና የአብሮኮሮስ ምስክርነት ተሰውሯል ወደሚለው ያደርሰናል። የስንክሳሩን አገላለጥ በሚመለከት ደግሞ ወደ ብሔረ ሕያዋን ተነጥቀዋል ብላ ቤ/ክርስቲያን የምትናገርላቸውን ቅዱሳንን ዐዕረፈ ብሎ ማስቀመጥ በአያሌው የተለመደ ነው። ዐረፈ የሚለው በአገባቡ ሞትን ብቻ አይገልጥም ከዚህ ዐለም ድካም መለየትን ካለንበት ዓለመ መሬት (ምድር) በሕይወት ወደ ብሔረ ብፁዓን አልያም ብሔረ ሕያዋን መሻገር ዕረፍት ተብሎ ይነገራል የሌሎቹን አበው ወደብሔረ ሕያዋን መሔድ ዕረፍት ይለዋል ለአብነት ግንቦት ፲፩ ስለ ቅዱስ ያሬድ ሲናገር «በዚህች ዕለት የሱራፌል አምሳያቸው ኢትዮጵያዊው ማሕሌታይ ያሬድ ዐረፈ» ይላል። እንደመውጫ ቅዱስ ዳዊት “ሕያው ሆኖ የሚኖር፥ ሞትንስ የማያይ ማን ነው? ነፍሱንስ ከሲኦል እጅ የሚያድን ማን ነው?” ይላል【መዝ ፹፱ ፥፵፰ 】ከሰው ወገን ሕያው ሆኖ ለዘለዓለም ነዋሪ ሞትንም ሳያይ በምድር ላይ ቀሪ የሆነ ማንም የለም። የሐዋርያው ክብርና ቅድስናም ከመሞቱ አልያም ወደ ብሔረ ሕያዋን ከመነጠቁ ጋር በቀጥታ የሚያያዝበት ልኬት የለውም። ባለመሞቱ የሚከብርበት በመሞቱ የሚቀርበት መንገድ ስለሌለ ክርስቶስ አይሞትም አላለም እስክመጣ ቢኖር… አለ እንጂ። ሰው ሕያዊት ነፍሱበ በሞት ከተለየችው እንደፈሰሰ ውኃ ነው ፈሶ የታፈሰ ውኃ 【ማይ ዘገብኣ እምድኅረ ተክዕወ】 የቅዱሱ መጽሐፍ ብሂል እንዲህ ይላል "ዘእምከመ ተክዕወ ማይ ውስተ ምድር ኢይትገባእ" እኛም እንጂ ይህን ይዘን «የፈሰሰ ውኃ አይታፈስም» እንል የለ!? 【፪ኛ ሳሙ፲፬፥፲፬ 】 ዮሐንስ ግን ሞቶ ተቀበረ ሲሉት ተነስቶ የተነጠቀ ነውና የታፈሰ ውኃ ነውና "ማይ ዘገብኣ እምድኅረ ተክዕወ" አልነው። ሞተ የተባለ በሰዎች ኅሊና የተቀበረውን ማንነታችን ወደልዕልናው በቸርነቱ ይንጠቅልን ሎቱ ስብሐት ለዘበስብሐተ አቡሁ ይሴባሕ፤ ወሎቱ ቅድሳት ለዘበቅድሳተ መንፈ ሱይትቄደስ 🙏 በቴዎድሮስ በለጠ ጥር ፬ ቀን ፳፻፲፮ ዓ.ም. ከደብረ ነጎድጓድ
    Mostrar más ...
    Our Patron Saint - St. John the Evangelist Orthodox Church
    The Holy, Glorious All-laudable Apostle and Evangelist, Virgin, and Beloved Friend of Christ, John the Theologian was the son of Zebedee and Salome, a daughter of St Joseph the Betrothed. He was called by our Lord Jesus Christ to be one of His Apostles at the same time as his elder brother James. This took place at Lake Gennesareth (i.e. the Sea of Galilee). Leaving behind their father, both brothers followed the Lord.The Apostle John was especially loved by the […]
    5 369
    12
    ሀለዉ ዝየ ይቀውሙ እለ ኢይጥእምዋ ለሞት . በዚህ ከቆሙት ሞትን የማይቀምሱ አሉ ✥ °°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°° ✥ ይኽን ቃል የትህትና አባት ከሆነውና የራሱን ክብር ከመግለጥ ከተቆጠበው ቅዱስ ዮሐንስ በቀር ቀሪዎቹ የከበሩ ወንጌላውያን በክታባቸው አኑረውልናል። ቅዱስ ማቴዎስ “እውነት እላችኋለሁ፥ የሰው ልጅ በመንግሥቱ ሲመጣ እስኪያዩ ድረስ እዚህ ከሚቆሙት ሞትን የማይቀምሱ አንዳንድ አሉ።” 【ማቴ. ፲፮፥፳፰】 ቅዱስ ማርቆስ “እውነት እላችኋለሁ፥ በዚህ ከቆሙት ሰዎች የእግዚአብሔር መንግሥት በኃይል ስትመጣ እስኪያዩ ድረስ፥ ሞትን የማይቀምሱ አንዳንዶች አሉ አላቸው።” 【ማር. ፱፥፩】 ቅዱስ ሉቃስ “እውነት እላችኋለሁ፥ በዚህ ከሚቆሙት ሰዎች የእግዚአብሔርን መንግሥት እስኪያዩ ድረስ ሞትን የማይቀምሱ አንዳንድ አሉ።” 【ሉቃ. ፱፥፳፯ 】 ቅዱስ ዮሐንስ በምድር ላይ የነበረውን የዘመኑን ፍፃሜ በሁለት የታሪክ ዘውጎች የሚተርኩ መዛግብትና ሊቃውንት አሉ። ① አንዳንዶች ሞቷል በሥጋና ነፍስ መለያየት በሚመጣ ሞት ዐረፍተ ዘመን ገቷቸው ነፍሳቸው በገነት እስከ ትንሳኤ ዘጉባኤ ከምትጠበቅ ጻድቃን ተደምሯል ይላሉ ② ሌሎች ደግሞ ‘የለም’ ቅዱስ ዮሐንስ እንደነ ኤልያስ ወደ ብሔረ ሕያዋን የተነቀ በመሆኑ አርጓል ተሠውሯል ይላሉ። አርፏል ለማለት እንደ ስንክሳር ያሉ መጻሕፍት ድርሳነ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ እና ከውጪ መዛግብት የተገኙ ቀደምት ምስክሮች በአስረጂነት ይቀርባሉ። «ወበዛቲ ዕለት ዐዕረፈ …» ስንክሳር «እስመ መብዝኅተ አዕፅምቲሆሙ ለሐዋርያት ኢነአምር አይቴ ውእቱ ወዘያሌቡሰ ላዕለ ዝንቱ ከመ መቃብረ ጴጥሮስ ወጳውሎስ ወዮሐንስ ወቶማስ እሙራን ወክሡታን እሙንቱ» የሚለውን የቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ድርሳን ፳፮ ንባብ ይዘው ሞቷል ተቀብሯል ይላሉ። አለመሞቱን ለመሞገት «ዐዕረፈ» ፣ «እሙር መቃብሩ» … ያለውን ለማስታረቅ ብዙ አስረጂ የሚያቀርቡ ሊቃውንት እንዲህ ያለ በመጻሕፍት የታሪክ ክፍተት የዘይቤ አለመስማማት ሲገኝ ሁለት መፍትሔ እንዲወሰድ ይመክራሉ። ፩ኛ) ቅድሚያ ለአብያተ ጉባኤ ትርጓሜ የወንበር ትምህርቶች ቦታ መስጠት ብሉያት ሐዲሳት ሊቃውንትና መነኮሳት የምንላቸውን ፬ቱን ትርጓሜ መጻሕፍት ሌሎች የዜማ ቤት የቅዱስ ያሬድ ገጸ በረከቶች እና በቅኔ ቤት የሚነገሩ ታሪኮች ከየቤተ ጉባኤ መምህራን ቀለማት ጋር ማሳተት ፪ኛ) የዘይቤና የታሪክ ክፍተቶችን በምሥጢር አስታርቆ ማስማማት ለምሳሌ አንድ ታሪክ ቅድሚያ ቦታ ይሰጣቸው ብለን በጠቀስናቸው መጻሕፍት ላይ ቢገኝና እንደአሁኑ ዓይነት ከስንክሳሩ ታሪክ ጋር የተስማማ ባይመስል ሊቃውንት ይኽን ይላሉ «ስንክሳር ምን ቁም ነገር ነው? ነገር እንደ ጉባኤ ቤቱ መጻሕፍት ነው እንጂ! የለም ይህስ ስንክሳርን መንቀፍ እንደ ሃይማኖተ አበው ያሉ ደገኛ መጻሕፍትን መንቀፍ ነው ምክንያቱም መላሻቸው አንድ ነው ብሎ ማስታረቅ ይገባል እንጂ!» ስለዚህ ያ በዚህ ምክንያት ይህ ደግሞ በዚህ ምክንያት ትክክል ነው ብሎ መጽሐፍ በመጽሐፍና በተጠያቂ ሊቅ ይዳኛል። ✧ በቅድሚያ ሐሳቦችን በአስረጂ ወደመሞገት እንለፍ ሀ】ከወንጌል የተገኘ ምስክርነት ፩ ተከታዩን የቅዱስ መጽሐፍ ክፍል ልብ ብለን እናንብብ "ጴጥሮስም ዘወር ብሎ ኢየሱስ ይወደው የነበረውን ደቀ መዝሙር ሲከተለው አየ፤ እርሱም ደግሞ በእራት ጊዜ በደረቱ ተጠግቶ፦ ጌታ ሆይ፥ አሳልፎ የሚሰጥህ ማን ነው? ያለው ነበረ። ጴጥሮስም ይህን አይቶ ኢየሱስን፦ ጌታ ሆይ፥ ይህስ እንዴት ይሆናል? አለው። ኢየሱስም፦ እስክመጣ ድረስ ይኖር ዘንድ ብወድስ፥ ምን አግዶህ? አንተ ተከተለኝ አለው። ስለዚህ፦ ያ ደቀ መዝሙር አይሞትም የሚለው ይህ ነገር ወደ ወንድሞች ወጣ፤ ነገር ግን ኢየሱስ፦ እስክመጣ ድረስ ይኖር ዘንድ ብወድስ ምን አግዶህ? አለው እንጂ አይሞትም አላለውም" 【የዮሐንስ ወንጌል ምዕራፍ ፳፩ ከቁጥር ፳ እስከ ፳፫ 】 ከዚህ ክፍል "እመኬ ፈቀድኩ የሀሉ እስከ ሶበ እመጽእ ሚላዕሌከ⇨ እስክመጣ ድረስ ይኖር ዘንድ ብወድስ ምን አግዶህ" የሚለውን ሲተረጉም አልሞተም አንድም ሞቷል የሚል መልስ እንደሚከተለው አብራርቶ ያኖርልናል «እኔ ከወደድኩ እስክመጣ ቢኖር ምን አግዶህ አለው እንጂ አትሞትም አላለም። ዮሐንስ ሞቷልን አልሞተም ቢሉ አልሞተም። ይህ እንዳይሆን ሊቁ «መቃብረ ጴጥሮስ ወጳውሎስ ወዮሐንስ እሙራን ወክሡታን እሙንቱ» ይላል ብሎ ሞቷል። ይህም ሊታወቅ መላእክት መቃብሩን ቆፍረዋል ከመቃብሩ ገብቶ ሲጸልይ ደቀ መዝሙሩን ፋጊርን (አብሮኮሮስን?) የኤፌሶንን ሰዎች በተማራችሁት ትምህርት ጸንታችሁ ኑሩ ብለህ ንገራቸው ብሎ ላከው ነግሮ ቢመለስ መቃብሩ የለፋ መስክ ሁኖ አጽፉን መቋሚያውን መነሣንሡን ከዳሩ አግኝቶታል።» መደረቢያው በትሩና ጭራው መገኘቱ መቃብር ሳትይዘው ለመውጣቱ በአስረጂነት ይቀርባል። በንባቡም ጌታው እስኪመጣ ድረስ እንዲኖር ወዷል ለሞቷል ባይ "ቢኖር ምን አግዶህ?» የሚል መልስ በባለቤቱ መሠጠቱን ማስተዋል ይገባል። ተሰውሯል የሚሉቱም ቢሆኑ አይሞትም ሳይሆን አልሞተም ባዮች መሆናቸውን መረዳት ይገባል። ለ) ሁለተኛው ከላይ በመነሻነት የተቀመጡ የሦስቱን ወንጌላውያን መልእክት ስናነብ በመጽሐፍ ቤት የሐዲሳቱ ሊቃውንት ደብረ ታቦር አልፎ በተናገረበት አውድ ሲፈቱ ትርጓሜውን ለዮሐንስ ሰጥተው «የእግዚአብሔር መንግሥት በኃይል ስትመጣ እስኪያዩ ድረስ፥ ሞትን የማይቀምሱ አንዳንዶች» የተባለው እርሱን የሚወክል እንደሆነ ነግረዋል አንዳንዶች ብሎ ማብዛቱ መጽሐፍ ስም ካልጠራ ማብዛት ልማዱ ነውና ለምሳሌ ፦ በተአምኖ አመ ነገርዎ ለኖኅ (የነገረው አንድ መልአክ ሆኖ ሳለ) ፣ ብፅዕት አንቲ እንተ ተአምኒ ዘነገሩኪ (ያበሠረው አንዱ ቅዱስ ገብርኤል ሆኖ ሳለ) በሌላ መልኩ በሁሉ ወንጌላውያን ተጠቅሶ በእርሱ አለመጻፉ ራሱን የሚመለከት ቢሆን ነው። ክብሬ ይገለጥልኝ መወደዴ ይነገርልኝ ብሎ ጉዳዩ ባለበት መነገሩን ሳያኖርልን የቀረው ስለትህትና እንደሚሆን ይታመናል። ሐ) ደብረታቦርን ካነሳን እግረ መንገድ ቅዱሱ አባታችን ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ በመጽሐፈ ምሥጢር ምሥጢረ ታቦርን ደጋግሞ ከአማናዊት የሐዲስ ኪዳን መርጡል ጋር እያዛመደ አስተምሮበታል። በሥፍራው የተገኘውን አልያስን አንስቶ ወደብሔረ ሕያዋን እንዴት እንደተነጠቀ ሲነግረን «ወከበቶሙ እግዚአብሔር ውስተ ምድር ኅብእት እንተ ተሠወረት በጥበበ ዚኣሁ ወአልቦ ሥልጣነ ሞት» ይላል። ታዲያ መሰሉን አብነት ይዘው መምህራን በቦታው የተገኘውን ኤልያስ ከዮሐንስ እንድናነፃፅር ያመለክቱናል። አምላካችን ክርስቶስ እና ቅዱስ ጴጥሮስ ጴጥሮስ በመስቀል ተሰቅለው ቢያልፉ ፣ ሊቀ ነቢያት ሙሴና የዘብዴዎስ ልጅ ያዕቆብ ዕረፍተ ሰላም ይኽን ዓለም ተሰናብተዋል፤ ታላቁ ነቢይ ኤልያስና ተወዳጁ ደቀ መዝሙር ዮሐንስ ወደ ብሔረ ሕያዋን ተጠርተዋልና… በፍጻሜ መገናኛቸው እንደሚገናኙ ሊያሳይ አወዳጅቶ አገናኛቸው ተገናኛቸውም ይላሉ።
    Mostrar más ...
    Our Patron Saint - St. John the Evangelist Orthodox Church
    The Holy, Glorious All-laudable Apostle and Evangelist, Virgin, and Beloved Friend of Christ, John the Theologian was the son of Zebedee and Salome, a daughter of St Joseph the Betrothed. He was called by our Lord Jesus Christ to be one of His Apostles at the same time as his elder brother James. This took place at Lake Gennesareth (i.e. the Sea of Galilee). Leaving behind their father, both brothers followed the Lord.The Apostle John was especially loved by the […]
    4 728
    9
    Última actualización: 11.07.23
    Política de privacidad Telemetrio