Best analytics service

Add your telegram channel for

  • get advanced analytics
  • get more advertisers
  • find out the gender of subscriber
Categoría
Ubicación del canal e idioma

audience statistics Ethiopian Business Daily

Stay ahead of the curve with EBD. We provides daily updates on business news and trends in Ethiopia, perfect for start-ups, entrepreneurs, businessmen, & anyone interested. Contact us:  @EBD_enquiries  Join Discussion Group:  https://t.me/+eq3KEXbX55s1YWQ0  
Mostrar más
33 414-8
~3 265
~4
11.50%
Calificación general de Telegram
Globalmente
31 207lugar
de 78 777
233lugar
de 396
En categoría
727lugar
de 1 704

Género de suscriptores

Averigua cuántos suscriptores masculinos y femeninos tienes en el canal.
?%
?%

Idioma de la audiencia

Descubre la distribución de los suscriptores de canales por idioma
Ruso?%Inglés?%Árabe?%
Crecimiento del canal
GráficoTabla
D
W
M
Y
help

La carga de datos está en curso

Duración del usuario en el canal

Descubra cuánto tiempo permanecen los suscriptores en el canal.
Hasta una semana?%Viejos?%Hasta un mes?%
Ganancia de suscriptores
GráficoTabla
D
W
M
Y
help

La carga de datos está en curso

Since the beginning of the war, more than 2000 civilians have been killed by Russian missiles, according to official data. Help us protect Ukrainians from missiles - provide max military assisstance to Ukraine #Ukraine. #StandWithUkraine
Partner's Content: ⚠️ ሐዋሳ ውስጥ ከሆናችሁ! ⚠️ ቢዝነስዎን ስኬታማ ለማድረግ እንደግፍዎታለን! በ ተመዝግበው ቦታዎን ያሲዙ። 🗓 መስከረም 20, 2017 ዓ.ም 🕒 ከጠዋቱ 3:30 እስከ 6:30 📍 በኬር አውድ ኢንተርናሽናል ሆቴል (Ker-Awud International Hotel), ሐዋሳ የመስራት ስራ ፈጠራ ፕሮግራም Info Session ጥቅሙ ምንድን ነው?      - መስራት ምን እንደሆነና ቢዝነስዎትን እንዴት እንደሚደግፍ ያውቃሉ፣      - ፕሮግራሙን እንዴት መቀላቀል እንደሚቻል ያውቃሉ፣      - ስለሚሰጡት ድጋፎች እና ለሚኖርዎት ጥያቄ መልስ ያገኙበታል።      - በቴሌግራም ቦት በኩል ለሚሰጥ ሥልጠና መመዝገብ ይችላሉ።
644
1
የገንዘብ ሚኒስቴር በተፈጥሮ እና ሰው ሰራሽ አደጋዎች ምክንያት ለአደጋ ጊዜ እርዳታ የሚለገሱ ሸቀጦች ከቀረጥ ነፃ እንዲገብ የሚፈቅደውን መመሪያ ማዉጣቱን አስታዉቀዋል ። ሚኒስትሩ ያወጣዉ አዲሱ መመሪያው "ከማህበራዊ  ልማት  ቀረጥ ነፃ የተደረጉ ዕቃዎችን ለመወሰን" የሚል ሲሆን ይህም የትምህርት፣ የጤና እና የአደጋ መከላከል ስራዎችን ለመደገፍ ዓላማ ያለዉ መሆኑ ተመላክቷል። በዚህ መመሪያ ዉስጥ ከውጪ የሚገቡ ቁልፍ የመከላከያ እና የህዝብ ደህንነት ዕቃዎች፣ ለምሳሌ የሀገር መከላከያ ሚኒስቴር፣ የፖሊስ ሃይሎች እና የብሄራዊ መረጃ አገልግሎቶች መሳሪያዎች፣  ከቀረጥ ነጻ የሆኑ እቃዎች ዝርዝር መካከል ይገኝበታል ። የገንዘብ ሚኒስቴር ከማህበራዊ ልማት ቀረጥ ነፃ ለማድረግ ዓላማ ባደረገዉ መመሪያ ቁጥር 1023/2024 መሰረት ትምህርት ቤቶች፣ ሆስፒታሎች እና ህጻናትን፣ ሴቶችን፣ አዛውንቶችን እና አካል ጉዳተኞችን የሚረዱ ድርጅቶችን ጨምሮ ለመንግስት ተቋማት የተበረከቱ እቃዎች ከቀረጥ ነፃ ወደ ሀገር ውስጥ ይገባሉ ተብሏል። የጉምሩክ ኮሚሽኑ  ከቀረጥ ነፃ የወጡ ዕቃዎችን አጠቃቀም በቅርበት ተከታትሎ የሩብ ዓመቱን ሪፖርት ለገንዘብ ሚኒስቴር  እንደሚያቀርብ ተገልጿል። Source: capitalethiopia
Mostrar más ...
812
0
ወደ አገር በሚገቡ እቃዎች ላይ ከተጣለው የማህበራዊ ልማት የሚሆኑ እቃዎችን ለመወሰን ገንዘብ ሚኒስቴር መመሪያ አውጥቷል። ይኸው መመሪያ" መመሪያ ቁጥር 1023/2017" ይሰኛል። በዚህ መመሪያ መሰረት ፥ ለህብረተሰቡ በነጻ የሚሰጡ የትምህርት እና የጤና አገልግሎቶችን ለማስፋፋት እንዲሁም በሰው ሰራሽ እና በተፈጥሮ አደጋ ምክንያት ችግር ላይ የሚገኙ ወገኖችን ለመርዳት ከውጭ አገር በእርዳታ የሚላኩ እቃዎች የማህበራዊ ልማት ቀረጥ የተጣለበትን አላማ ለማሳካት የሚያግዙ በመሆኑ ከቀረጥ ነጻ እንዲሆኑ ተደርጓል። ከማህበራዊ ልማት ቀረጥ ነጻ የተደረጉ እቃዎች? የሚከተሉት እቃዎች ከማህበራዊ ልማት ቀረጥ ነፃ ሆነው ወደ ሀገር ይገባሉ፡፡ 1. ለሚከተሉት የማህበራዊ አገልግሎት መስጫ ተቋማት ከውጭ አገር በእርዳታ የሚላኩ እቃዎች :- . . . Source: theethiopianeconomistview
Mostrar más ...
2 308
10
Partner's Content: #የቴክኖ የአዲስ ዓመት ልዩ የበዓል ስጦታ! የአዲስ አመት ልዪ ስጦታ ከቴክኖ ሞባይል ኢትዮጵያ፣ ከየትኛውም የቴክኖ ሱቅ የቴክኖ ስማርት ስልክን ሲገዙ አብሮት ካለ ወዳጅ ዘመድ ወይም ጓደኛ ጋር ፎቶ በመነሳት የማህበራዊ ገጾት ላይ በመለጠፍ እና ብዙ ላይክ በማግኘት የዱባይ ደርሶ መልስ የቢዝነስ ክላስ የአውሮፕላን ትኬት፣ ላፕቶፖች፣ የቴክኖ ስማርት ስልኮችን እና ገደብ አልባ የኢንተርኔት ፓኬጆችን ይሸለሙ፡፡ የውድድሩ መመሪያ 1. የቴክኖ ኢትዮጵያን ፌስ ቡክ ፣ ኢንስታግራም እና ቲክቶክ ገጾችን ፎሎው ያድርጉ፡፡ 2. የተነሱትን ፎቶ በመረጡት ማህበራዊ ሚዲያ ሲለጥፉ የቴክኖ ኢትዮጵያን ገፅ ከፖስቶት ጋር ታግ ያድርጉ፡፡ ብዙ ላይክ እና ኢንጌጅመንት ያገኘው ተሸላሚ ይሆናል፡፡ - Tag ሲያደርጉን ለ Facebook ፣ ለ Instagram እና ለ TikTok ን  ሜንሽን ማድረግ እንዳይረሱ።) - በተጨማሪም ን keyword መጠቀም እንዳይረሱ)
Mostrar más ...
2 399
0
የቤቶች ኮርፖሬሽን በዚህ ዓመት በድሬደዋ የመኖሪያ ቤት ግንባታ እንደሚያካሂድ ገለጸ። የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በድሬዳዋ አስተዳደር በወሰደው መሬት ላይ የነበረው የይገባኛል ክርክር በመቋቸቱ በዚህ ዓመት የመኖሪያ ቤት ግንባታ ሊያካሂድ መሆኑ አስታዉቋል። የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን ከዚህ በተጨማሪ በድሬዳዋ እና በአዲስ አበባ በዚህ አመት ለሚያከናውኗቸው የልማት ስራዎች 7 ቢሊዮን ብር በጀት መያዙን የኮርፖሬሽኑ የድሬዳዋ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ሀላፊ አቶ እዉነቱ ወርቅነህ ገልጸዋል። የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በድሬዳዋ ከተማ ወደ 1993 ቤቶችን ያስተዳድራል። ከነዚህም ዉስጥ 541 የንግድ ቤቶች ናቸዉ። የተቋሙ ሀላፊ እንደሚሉት በ2016 ዓ.ም የንግድ ቤቶች ላይ መጠነኛ የዋጋ ጭማሪ በማድረግ በዓመቱ መጨረሻ 38 ሚሊዮን ብር መሰብሰብ ተችሏል። Source: tikvahethmagazine
Mostrar más ...
2 722
2
Partner's Content: ኤክስፐርት ለመሆን እና ከፍተኛ ተፈላጊነት ባላቸው ሙያዎች የምስክር ወረቀት ማግኘት ይፈልጋሉ? የ Safaricom Talent Cloud ትክክለኛው ቦታ ነው፡ በመረጡት የትምህርት ዘርፍ እውቀትን ለመገንባት በጥሩ ሁኔታ ከተዘጋጁ ኮርሶች በተጨማሪ የሚከተሉትን ያገኛሉ፡- - በመረጡት የሙያ መስክ የላቀ ለመሆን እንዲረዳዎ በባለሙያዎች የተመረጡ የትምህርት ካሪኩለሞች - እጅግ ታዋቂ ከሆነው Pluralsight የonline መማሪያ ድህረገጽ ሰርተፍኬት ልምድ ባላቸው ባለሙያዎች የሚመሩ የስልጠና ቡድኖችን - በየወሩ ነጻ የ6 GB የኢንተርኔት አገልግሎት ተጠቃሚም ይሆናሉ እነዚህን ተጨማሪ ጥቅማጥቅሞችና ግልጋሎቶች በማግኘት በፍጥነት ያሎትን እዉቀትና ክህሎት በማሳደግ በስራ ዘርፎ ዉጤታማ መሆን ይችላሉ። ይጎብኙ! ለበለጠ መረጃ ቴሌግራሞ ቻናላችንን ይቀላቀሉ
Mostrar más ...
2 686
6
Ethiopian Reinsurance Saves USD 50 Million in Foreign Currency Ethiopian Reinsurance, established eight years ago with an initial capital of Birr 1 billion, announced that it has saved the country USD 50 million in foreign currency. The company, which provides reinsurance services to Ethiopian insurance companies, has played a crucial role in retaining funds that were previously spent abroad. Source: 2merkato
2 700
4
⚠️ ሐዋሳ ውስጥ ከሆናችሁ! ⚠️ ቢዝነስዎን ስኬታማ ለማድረግ እንደግፍዎታለን! በ ተመዝግበው ቦታዎን ያሲዙ። 🗓 መስከረም 20, 2017 ዓ.ም 🕒 ከጠዋቱ 3:30 እስከ 6:30 📍 በኬር አውድ ኢንተርናሽናል ሆቴል (Ker-Awud International Hotel), ሐዋሳ የመስራት ስራ ፈጠራ ፕሮግራም Info Session ጥቅሙ ምንድን ነው? - መስራት ምን እንደሆነና ቢዝነስዎትን እንዴት እንደሚደግፍ ያውቃሉ፣ - ፕሮግራሙን እንዴት መቀላቀል እንደሚቻል ያውቃሉ፣ - ስለሚሰጡት ድጋፎች እና ለሚኖርዎት ጥያቄ መልስ ያገኙበታል። - በቴሌግራም ቦት በኩል ለሚሰጥ ሥልጠና መመዝገብ ይችላሉ።
Mostrar más ...
3
0
የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ሥራ አስፈፃሚ የታሪፍ ማሻሻያ እንደሚኖር ፍንጭ ሰጡ የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ሥራ አሥፈጻሚ ፍሬሕይወት ታምሩ የተቋሙን የ2017 በጀት ዓመት እቅድ ይፋ አደረጉበት መግለጫ ላይ ከታሪፍማሻሻ ጋር ተያይዞ ጥያቄ ቀርቦላቸዋል። “ዋጋ ሳታስተካክሉ እናንተስ መቀጠል ትችላላችሁ ወይ ለሚለው ጥያቄ፤ ተገቢ እና ትክክለኛ ነው” ያሉት ዋና ስራ አስፈጻሚዋ፤ “ዘለን ታሪፉን ያለስተካከለው የደንበኞቻችንን እንዲሁም በአጠቃላይ የማክሮ ኢኮኖሚ ለውጡ እንዲረጋጋ እና ጤናማ እንዲሆን ስለምንፈልግ ነው” ብለዋል። ዋና ስራ አስፈጻሚዋ ፍሬህወት ታምሩ በመግለጫቸው ላይ “በጣም በተጠና መልኩ የደንበኞችን የመክፈል አቅም ታሳቢ ያደረገ መጠነኛ የሆኑ የዋጋ ጭማሪዎች ይኖረናል፤ ነገር ግን በሁሉም ደንበኞች ላይ ተፈጻሚ አይደረግም” ብለዋል። Source: seleda
Mostrar más ...
3 672
10
Ethio Telecom Rolls Out $1 Billion Budget for Massive Expansion Ethio Telecom, the state-owned telecom provider with 130 years of service, has unveiled a formidable budget of around $1 billion as it gears up to launch 260 new products and services in the coming year. Source: shegamedia
3 810
11
Partner's Content: ገቢዎን እና ወጪዎን እንዴት ማስተዳደር እንደሚችሉ ይማሩ! 📊💡 "የግል በጀት አወጣጥ መሠረታዊ ነገሮች" በሚል ላዘጋጀነው የኦንላይን ስልጠና ይመዝገቡ! 🗓 መስከረም 10, 2017 ዓ.ም ⏰ ከቀኑ 8:00 እስከ 11:00 ሰዓት 💻 በመጠቀም ይመዝገቡ! ይህ አጋጣሚ እንዳያመልጥዎ!
3 726
7
ኢትዮ ቴሌኮም በ2017 በጀት ዓመት የቴሌብር ደንበኞችን ቁጥር በ15.7% በመጨመር 55 ሚሊዮን ለማድረስ ማቀዱን በዛሬው ዕለት ይፋ ባደረገው የሦስት ዓመት ስትራቴጂ እና የ2017 ዓ.ም በጀት ዓመት የቢዝነስ ዕቅድ መግለጫ ላይ ጠቅሷል። ኩባንያው፥ የቴሌብር ወኪሎችን ቁጥር በ28% በማሳደግም 275 ሺህ ለማድረስ እንዲሁም በቴሌብር ግብይት የሚፈጽሙ ነጋዴዎችን (Merchant) ቁጥር በ102% በማሳደግ 367 ሺህ ለማድረስ በእቅዱ እንደተቀመጠም ጠቅሷል። በተጨማሪም፥ የኤሌክትሮኒክ ንግድ ክፍያዎችን፣ አለም አቀፍ የኦንላይን ክፍያዎችን፣ ተጨማሪ አጋሮችን በማሳተፍ የሃዋላ አገልግሎቶችን ለማሳደግ እንደሚሰራም ነው የገለጸው። Source: tikvahethmagazine
3 853
3
ኢንቨስት ስናደርግ ምናይነት የአደጋ ስጋት መከላከያ መንገዶችን መጠቀም ይኖርብናል? - የመጀመሪያው ኢንቨስት ምናደርግበትን ሰነደመዋለንዋዮችን ብዝሃነት መጨመር ነው። “Don’t put all your eggs in one basket” እንደሚባለው ያለንን ገንዘብ በሙሉ በተመሳሳይ ነገር ላይ ኢንቨስት ማድረግ የለብንም። - ኢንቨስት ያደረግንባቸው ነገሮች ፈጣን የዋጋ ለውጥ እንዳይታይባቸው መጠንቀቅ ያስፈልጋል። ለምሳሌ ኢንቨስት ያደረግነው አክሲዮንና ቦንድ ላይ ከሆነ አክሲዮኖች በብዛት ለvolitility የተጋለጡ ስለሆኑ portfolio ውስጥ ቦንዶችንም በመጨመር ይህንን ማመጣጠን አለብን። - በቋሚነት ኢንቨስት ማድረጋችንን አለማቆም። ትርፍ ለማግኘት, "ትክክለኛ" አክሲዮን መምረጥ እና "በትክክለኛ" ጊዜ መሸጥ እጅግ በጣም አስፈላጊ ነው። ይህ ሁሉ በትዕግስት እና በረጅም ጊዜ እቅድ ላይ የተመሰረተ ነው። - የኢንቨስትመንት ሪስክን በአግባቡ በማጤን በቁጥራዊ ስሌቶች ልናስቀምጠው የምንችለው ሪስክ ማድረግ መቻል ይኖርብናል። ሁሉም ሪስክ ልንለካው በምንችለው መንገድ ልኬት ማስቀመጥና ቀጣይ እርምጃዎች ላይ የተጠና ስልት መከተል ይኖርብናል። - በተጨማሪ ደግሞ margin of safety ለኢንቨስትመንታችን ማስቀመጥ ይኖርብናል። ይህም ማለት አንድ ባለሀብት ዋስትናዎችን የሚገዛበት የገበያ ዋጋቸው ከድርጅቶቹ ውስጣዊ እሴት በታች ከሆነ ብቻ የሚገዛበት የኢንቨስትመንት መርህ ነው። - በመጨረሻ ደግሞ አቅማችን ሚችለውንና ልንቋቋም የምንችለውን የሪስክ መጠን (maximum loss plan) ማወቅ አስፈላጊ ነው። Source: stockmarketet
Mostrar más ...
3 695
26
ብሉምበርግ ሚዲያ ኢኒሼቲቭ አፍሪካ (BMIA) የፋይናንሺያል ጋዜጠኝነት ስልጠና ፕሮግራም በኢትዮጵያ ጀመረ። በመጀመሪያው ቡድን ውስጥ 55 ከመገናኛ ብዙሃን፣ ከፋይናንስ እና ከመንግስት ሴክተሮች የተውጣጡ ሰልጣኞች ይሳተፋሉ። ፕሮግራሙ በመረጃ ላይ የተመሰረተ ዘገባ ላይ በማተኮር የንግድ እና የፋይናንስ ጋዜጠኝነትን ለማሳደግ የተነደፈ ነው። ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ፣ ከዩኒቲ ዩኒቨርሲቲ እና ከስትራትሞር ዩኒቨርሲቲ (ቢዝነስ ት/ቤት በኬንያ) ጋር በመተባበር ይሰጣል። ተሳታፊዎች በመረጃ ትንተና፣ በካፒታል ገበያ፣ በኢኮኖሚክስ፣ በፐብሊክ ፖሊሲ ​​የሚሰለጠኑ ይሆናል። የ BMIA ፕሮግራም ከ2015 ጀምሮ በመላው አፍሪካ ከ900 በላይ ጋዜጠኞችን አሰልጥኗል። Source: stockmarketet
3 754
13
The Traffic Management Authority has introduced a series of measures to ensure compliance, including licensing requirements, safety protocols, and standardised parking indicators. Officials plan to conduct a comprehensive impact assessment and engage with the public to gather feedback and address concerns. Source: addisfortune
3 959
3
Ethiopia Unveils First-Ever Tourism Satellite Account Ethiopia has launched its first-ever Tourism Satellite Account (ET-TSA), a strategic initiative designed to unlock the full economic potential of the country's tourism sector. Source: 2merkato
4 199
3
NBE Launches Campaign to Boost Remittance Revenue and Foreign Currency Flow The National Bank of Ethiopia (NBE) has unveiled a strategic initiative to enhance foreign currency inflows by launching a six-month campaign aimed at increasing remittances. The campaign, which involves government agencies, financial institutions, diplomatic missions, and the diaspora, is part of broader efforts to stimulate hard currency generation. Source: capitalethiopia
4 405
5
የዶላር ምንዛሬ ዋጋ ከፍ ያለ ጭማሪ አሳይቷል። በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ለ7 ቀናት ጭማሪ ያልታየበት ወጥ የምንዛሬ ዋጋ ነበር። ባንኩ ዛሬ ሲያገበያይበት የነበረው የምንዛሬ ዋጋ ከፍ ያለ ጭማሪ የታየበት ነበር። አንዱ የአሜሪካ ዶላር መግዣው ወደ 112 ብር ከ3957 ሳንቲም ደርሷል። የመጫው ዋጋም 124 ብር ከ7592 ሳንቲም ገብቷል። በፓውንድ ላይም ጭማሪ ተመዝግቧል። አንዱ ፓውንድ መግዣው 141 ብር ከ6314 ሳንቲም ተቆርጦለት ውሏል። መሸጫው 157 ብር ከ9487 ሳንቲም ነበር። ዩሮ መግዣው 125 ብር ከ0177 ሳንቲም መሸጫው 138 ብር ከ7697 ሳንቲም ሆኖ ውሏል። የUAE ድርሃም መግዣው 30 ብር ከ6030 ሳንቲም መሸጫው 33 ብር ከ9693 ሳንቲም ገብቷል። Source: tikvahethiopia
4 383
9
ዘመን ባንክ የተከፈለ ካፒታሉ ወደ 7.5 ቢሊዮን ብር መድረሱን አስታዉቋል የባንክ ኢንደስትሪዉን ከተቀላቀለ 16 ዓመታትን ያስቆጠረው ዘመን ባንክ የተፈረመ ካፒታሉ ወደ 15 ቢሊዮን ብር መድረሱንና የተከፈለ ካፒታሉ ደግሞ ወደ 7.5 ቢሊዮን ብር መጠጋቱን አስታዉቋል። ባንኩ በተጠናቀቀዉ በጀት ዓመት ህጋዊ መጠባበቂያዉ ወደ 1.7 ቢሊዮን ብር ማሳደግ መቻሉን ያስታወቀዉ ከ 200 በላይ በባንኩ ረዥም ጊዜ አብረውት ሲሰሩ የነበሩ ደንበኞችን እና አጋሮቹን እዉቅና በሰጠበት መድረክ ላይ ነዉ ። የባንኩ ዋና አስፈፃሚዉ አቶ ደረጀ ዘነበ እንደተናገሩት የፋይናንስ ዘርፉ እና አገልግሎቶቹ ነፃ እየሆኑ ባለበት በአሁኑ ጊዜ ከደንበኞቹ እና አጋሮቹ ጋር መስራት በመቻላችን እድለኞች ያደርገናል ብለዋል። ከዘመን ባንክ እዉቅና የተሰጣቸው በንግድና ኢንቨስትመንት ፣ አበባ እርሻ ልማት ፣ በቴክኖሎጂ ፣ በአየር ትራንስፖርት ፣ በሆቴል እና በቱሪዝም ላይ የተሰማሩ የአገልግሎቱ ተጠቃሚ ደንበኞች መሆናቸዉ ተነግሯል ። Source: capitalethiopia
Mostrar más ...
3 407
5
የኢትዮጵያ ቤተሰብ የንግድ ስራዎች በኢኮኖሚው ዉስጥ ጉልህ አስተዋጽኦ ቢኖራቸዉም "ደካማ የአስተዳደር መዋቅሮች" ፈተና ሆኖባቸዋል ተባለ የኢትዮጵያ የቤተሰብ ንግድ ሥራዎች በኢኮኖሚው ውስጥ ጉልህ አስተዋፅዖ የሚያደርጉ ቢሆንም ደካማ የሆነ የአስተዳደር መዋቅሮች፣ መደበኛ ተተኪ እቅድ አለመኖር እና በቂ ያልሆነ የችሎታ አስተዳደር ልምዶችን ጨምሮ ወሳኝ ተግዳሮቶች ያጋጥሟቸዋል ተብሏል። ይህ የተገለፀው “ችቦውን ማሻገር ለኢትዮጵያ የቤተሰብ ንግድ ዘላቂ ስኬት” በሚል መሪ ቃል የኢትዮጵያ ቤተሰብ ቢዝነስ ፎረም የመክፈቻ ጉባኤ ዛሬ በተካሄደበት ወቅት ነዉ። በዚህ ወቅት የኤች ኤስ ቲ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ሰለሞን ግዛዉ እንደተናገሩት "የኢትዮጵያ ቤተሰብ ቢዝነስ ፎረም የተቋቋመው የቤተሰብ ቢዝነሶች በኢኮኖሚው ውስጥ ያለውን ጠቀሜታ ለመቅረፍ እና እድገታቸውን ለመደገፍ ነው" ብለዋል። በቤተሰብ ንግዶች ውስጥ ካሉት ወሳኝ ተግዳሮቶች አንዱ የሽግግር እቅድ ማውጣት ይህም አመራር እና ባለቤትነትን ከአንዱ ትውልድ ወደ ሌላ ትውልድ ያለ ውጣውረድ እንዲተላለፍ አስቀድሞ እንደሚያዘጋጅ አቶ ሰለሞን ገልፀዋል ። ፎረሙ የኢትዮጵያ ቤተሰብ ንግድ እንዲያድግ እና ቀጣይነት እንዲኖረው ለመርዳት በ ኤች ኤስ ቲ የተቋቋመ መሆኑ ለማወቅ ተችሏል። Source: capitalethiopia
Mostrar más ...
3 355
12
በወጪ ንግድ ላይ የተሰማሩ ባለሃብቶች ለቻይና ገበያ ምርቶቻቸዉን በቀጥታ እያቀረብ ባለመሆናቸዉ ምክንያት የገበያ ድርሻቸውን እያጡ መሆኑን ተናገሩ የኢትዮጵያ መንግስት ወደ ቻይና የሚሄዱ ኤክሰፖርት በሙሉ ክፍያቸዉን በንግድ ባንክ በኩል ብቻ እንዲፈፀም በማድረጉ በዘርፉ የተሰማሩ ባለሃብቶች የገበያ ድርሻቸውን እያጡ መሆኑን አስታዉቀዋል። ከዛሬ ስምንት ዓመት በፊት የኢትዮጵያ መንግስት ለአለም ባንክ እና አለም አቀፍ ገንዘብ ድርጅት ( አይኤምኤፍ ) የተበደረችውን ብድሮች ክፍያ የሚፈፀመዉ በንግድ ባንክ ብቻ እንዲሆን አድርጎታል። ይህን ተከትሎ በተመሳሳይ ወደ ቻይና የሚሄዱ ኤክስፖርት በሙሉ በንግድ ባንክ በኩል እንዲሆን ተደርጓል። ይሁን እንጂ በዚህ ዉሳኔ ምክንያት ለዓመታት በውጪ ንግድ ላይ የተሰማሩ ባለሃብቶች የግብርና ምርታቸውን ለቻይና በቀጥታ ሳይሆን በተዘዋዋሪ ነዉ እያቀረቡ የሚገኙት በዚህ ምክንያት ትርፋማ መሆን ሲገባቸዉ ለኪሳራ እየዳረጋቸው መሆኑን አስረድተዋል ። የኢትዮጵያ ምርቶችን በቀጥታ ሳይሆን ከሌሎች ጎሮቤት ሃገራት እንድትረከብ የተደገገችዉ ቻይና አፈፃፀሙ ዝቅተኛ መሆኑ በወጪ ንግድ ላይ የተሰማሩ ባለሃብቶች በግል ባንኮች በኩል ክፍያ እንዲፈፅሙ ባለመደረጉ መሆኑን አንስተዋል ። Source: capitalethiopia
Mostrar más ...
4 313
9
Ethiopia Achieves Record Coffee Export Revenue Ethiopia secured over USD 196 million from the export of 42,322 tons of coffee in just one month, setting a new record for foreign currency earnings, according to the Ethiopian Coffee and Tea Authority. Source: 2merkato
4 218
5
Ethiopian Electric Power Reveals Major Infrastructure Projects for 2024/25 Ethiopian Electric Power (EEP) announced that it was on track to complete five key infrastructure projects, including power transmission and distribution stations, within the current fiscal year. Source: 2merkato
3 986
1
Partner's Content: በአዲሱ ዓመት በአዲስ ክህሎቶች ራሳችሁን ብቁ አድርጉ። በሳፋሪኮም ታለንት ክላውድ ላይ የ 20% ቅናሽ ለወንዶች : 5,706 ብር የነበረው አሁን በ 1,141 ብር ብቻ ያግኙ። - 6000+ tech and non tech ኮርሶች - በ ቀጣሪዎች ዘንድ ተቀባይነት ያላቸው ሰርተፍኬቶች - በተለያዩ ፕሮጀክቶቻችሁ ላይ ከአቻ ባልደረቦቻችሁ ጋር አብራችሁ የምትሰሩበት እድል - ልምድ ባላቸው ባለሙያዎች የሚመሩ የስልጠና ቡድኖችን - በየወሩ ነጻ የ6 GB የኢንተርኔት አገልግሎት ተጠቃሚም ይሆናሉ በዚህ አዲስ ዓመት ግቦችን ብቻ አታስቀምጡ፣ ግቦቹን አሳኩት። አሁኑኑ ይመዝገቡ : ለተጨማሪ መረጃ የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ:
4 105
18
የቱሪዝም ዘርፍን በስታቲስቲክስ  ማዕቀፍ ስር እንዲሆን የሚያስችል አዲሱ አሰራር ተግባራዊ ሊደረግ መሆኑ ተነገረ ኢትዮጵያ የቱሪዝም ዘርፍ ለኢኮኖሚ የሚያበረክተውን አስተዋጽኦ በትክክል ለመለካት የሚያስችል ጠንካራ የስታቲስቲክስ ማዕቀፍ ወደ ስራ ልታስገባ መሆኑ ተሰምቷል ።  ካሁን ቀደም የነበረው የተበታተነ የመረጃ አሰባሰብ ሂደት አመርቂ የፖሊሲ ቀረጻ እና አተገባበር አዳይኖር ምክንያት ሆኖ መቆየቱ ተገልጿል ። በዚህም አሁን ላይ ባለዉ የመረጃ ክፍተት ቱሪዝም የሚያስገኘውን የኢኮኖሚ ጥቅም ሀገሪቷ አሟጣ መጠቀም እንዳትችል አድርጓታል። የዚህን ተግዳሮት ለመፍታት የቱሪዝም ሚኒስትር "የቱሪዝም ሳተላይት አካውንት" የሚል አዲስ የስታትስቲክስ ማዕቀፍ ተግባራዊ ሊያደርግ መሆኑን አስታዉቋል። በአሁኑ ወቅት የኢትዮጵያ የቱሪዝም ዘርፍን የተመለከተ የመረጃ ውስንነት ያለ ሲሆን ይህን ችግር ለመቅረፍ ቱሪዝም ሚኒሰቴር ከዩ ኤን ኢሲኤ የቴክኒካል ድጋፍ አማካኝንት "የኢትዮጵያን ቱሪዝም ሳተላይት አካውንት" ማዘጋጀቱን ነዉ ያስታወቀው ። የኢትዮጵያ የቱሪዝም ሳተላይት አካውንት ዝግጅት ከፕላን እና ልማት ሚኒስቴር እና ከሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር እ.ኤ.አ በ2023 የካቲት ወር የተጀመረ ሲሆን በነገው  እለት መስከረም 7፤2017 ዓ.ም.አድዋ ሙዚየም ይፋ ይደረጋል ተብሏል። Source: capitalethiopia
Mostrar más ...
4 033
5
#የቴክኖ የአዲስ ዓመት ልዩ የበዓል ስጦታ! የአዲስ አመት ልዪ ስጦታ ከቴክኖ ሞባይል ኢትዮጵያ፣ ከየትኛውም የቴክኖ ሱቅ የቴክኖ ስማርት ስልክን ሲገዙ አብሮት ካለ ወዳጅ ዘመድ ወይም ጓደኛ ጋር ፎቶ በመነሳት የማህበራዊ ገጾት ላይ በመለጠፍ እና ብዙ ላይክ በማግኘት የዱባይ ደርሶ መልስ የቢዝነስ ክላስ የአውሮፕላን ትኬት፣ ላፕቶፖች፣ የቴክኖ ስማርት ስልኮችን እና ገደብ አልባ የኢንተርኔት ፓኬጆችን ይሸለሙ፡፡ የውድድሩ መመሪያ 1. የቴክኖ ኢትዮጵያን ፌስ ቡክ ፣ ኢንስታግራም እና ቲክቶክ ገጾችን ፎሎው ያድርጉ፡፡ 2. የተነሱትን ፎቶ በመረጡት ማህበራዊ ሚዲያ ሲለጥፉ የቴክኖ ኢትዮጵያን ገፅ ከፖስቶት ጋር ታግ ያድርጉ፡፡ ብዙ ላይክ እና ኢንጌጅመንት ያገኘው ተሸላሚ ይሆናል፡፡ - Tag ሲያደርጉን ለ Facebook ፣ ለ Instagram እና ለ TikTok ን  ሜንሽን ማድረግ እንዳይረሱ።) - በተጨማሪም ን keyword መጠቀም እንዳይረሱ)
Mostrar más ...
4 289
1
የኢትዮጵያ ኢኮኖሚክስ ባለሙያዎች ማኅበር  በገበያ ላይ የተመሠረተ የውጭ ምንዛሬ ፖሊሲውን በተመለከተ ያጠናው ባለ 19 ገፅ የዳሰሳ ጥናት ማንበብ ለምትፈልጉ! Source: theethiopianeconomistview

Exchange-rate-reform_2016.pdf

4 940
71
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የነበረበትን ዕዳ ወደ 20 በመቶ ዝቅ ማድረግ መቻሉን አስታወቀ በመንግስት እየተመራ ካለው የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ጋር ተያይዞ ከፍተኛ ለውጥ እያመጣ መሆኑን ግዙፉ የመንግስት ድርጅት የሆነው የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አስታዉቋል ። በዚህም የኢኮኖሚ ሪፎርም ትግበራ የተቋሙን ዕዳ ከ55 በመቶ ወደ 20 በመቶ ዝቅ ማድረግ መቻሉ ተገልጿል። በተቋሙ የፋይናንስ ዘርፍ ሥራ ሥራ አስፈፃሚ አቶ ደመረ አሰፋ እንደተናገሩ ተቋሙ በ2014 ዓ.ም እንደ አዲስ ሲቋቋም 34 ነጥብ 768 ቢሊዮን ብር የተከፈለ ካፒታል በመያዝ እንደነበርና ይህ አኀዝ በብዙ እጥፍ በማደጉ አዋጁን ማሻሻል እንደሚያስፈልግ አብራርተዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይልና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ያዘጋጁት ረቂቅ የኃይል ሽያጭ ታሪፍ ክለሳን በተመለከተ፣ ከሶስት ወር በፊት ሰኔ 6 ቀን 2016 ዓ.ም. በዓድዋ ሙዚየም የስብሰባ አዳራሽ በጋራ ባዘጋጁት መድረክ ከሚዲያ ባለሙያዎችና ባለድርሻ አካላት ዉይይት ላይ እንደተገለጸው  " አገልግሎቱ ኪሳራ ላይ ነው ባይባልም ዓመታዊ የተጣራ ትርፉ ግን አራት ትራንስፎርመሮችን እንኳን መግዛት የማያስችል መሆኑ ተነግሮ ነበር። የተቋሙ አጠቃላይ ሀብት 709 ቢሊዮን ብር መድረሱ የተነገረ ሲሆን አሁን  ካለው ከ709 ቢሊዮን አጠቃላይ ሀብት መካከል 586 ቢሊዮን ብሩ የተከፈለ ካፒታል ነው። በሚያመነጨው ኃይል መጠንና በማመንጫዎቹ ከአፍሪካ የኤሌክትሪክ ኃይል አስተዳዳሪ ተቋማት ሦስተኛ ደረጃ ላይ የሚገኘው የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል፣ እስከ ሰኔ 30 ቀን 2015 ዓ.ም. ድረስ 367 ቢሊዮን ብር እዳ እንዳለበት ማስታወቁ ይታወሳል ። Source: capitalethiopia
Mostrar más ...
5 099
3
ኢትዮጵያ በሰሊጥ ምርት በቻይና ገበያ የነበራት ድርሻ ወደ 5 በመቶ ዝቅ ማለቱ ተገለፀ ከአፍሪካ አገሮች በሰሊጥ ምርት ግንባር ቀደም እንደሆነች የሚነገርላት ኢትዮጵያ አሁን ላይ በአለም አገራት ያላትን የገበያ ድርሻ ከጊዜ ወደ ጊዜ እያጣች መሆኑ ተጠቁሟል ። ከአስር ዓመታት በፊት በቻይና ገበያ የኢትዮጵያ የሰሊጥ ምርት የ50 በመቶ ድርሻ የነበረዉ ቢሆንም አሁን ግን ይኼ ድርሻ ወደ 5 በመቶ መዉረዱን የኢትዮጵያ ጥራጥሬ፣ቅባት እህሎችና ቅመማ ቅመም አዘጋጅቶ ላኪዎች ማህበር አስታዉቋል። የማህበሩ ቦርድ ፕሬዝዳንት የሆኑት አቶ ኤዳዎ አብዲ እንደተናገሩት "አሁን ላይከሌሎች አገራት ጋር በዋጋ እየተወዳደርን አይደለም" የገበያ ድርሻችንን እያጣን ነው ያሉ ሲሆን ለዚህም የአቅርቦት ሰንሰለትና የምርታማነት እንከኖች በጉልህ ይጠቀሳሉ በማለት ለምርቱ መቀነስ ምክንያት ነዉ ያሉትን ጉዳይ አንስተዋል ። Source: capitalethiopia
Mostrar más ...
5 251
14
ውድ የ@Ethiopianbusinessdaily ሙስሊም ቤተሠቦቻችን እንኳን ለ1499ኛው የታላቁ ነብዩ መሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) የመውሊድ በዓል በሠላም አደረሳችሁ!
5 386
3
Última actualización: 11.07.23
Política de privacidad Telemetrio