አኽላቃችን
አል_በይሀቂ ሹዐቡል_ኢማን ላይ
እንደዘገቡት አቡ-ደርዳእ የሚባሉት
ታላቅ ሰሓቢይ رضي الله عنه
አንድ ሌሊት ላይ ለይል እየሰገዱ
የሚከተለውን ዱዓእ ብቻ እየደጋገሙ
ለሊቱ ነጋ፣ (አሏህ ሆይ፦ ውጫዊ
ገጽታንዬን/አፈጣጠሬን እንዳሳመርከው
ሁሉ ስነ-ምግባሬንም አሳምርልኝ)
በማግስቱ ባለቤታቸው "የደርዳእ
አባት ሆይ፥ምነው ማታ ስለ መልካም
ስነ-ምግባር ብቻ ዱዓእ እያደረግክ አደርክ?!"
አለቻቸው። እሳቸውም "የደርዳእ እናት
ሆይ፥ ሙስሊም ስነ-ምግባሩ እያማረ..
እያማረ ሲሄድ መጨረሻ ላይ መልካም
ስነ-ምግባሩ ጀነት እንዲገባ ያደርገዋል፣
ስነ-ምግባሩ እየተበላሸ... እየተበላሸ..
ሲሄድ ደግሞ መጨረሻ ላይ የጀሀነም
እሳት ውስጥ እንዲገባ ያደርገዋል..."
ብለው መለሱላት።
🍁አሏህ አኽላቃችንን ያሳምርልን፣
🍁እርሱና የአዕምሮ ባለቤቶች ከሚጠሉት
ዓይነት አኽላቅ በሙሉ ያርቀን።
✅መልካም አኽላቅ ይህን የላቀ ደረጃ
የሚያስገኘው ለብዙ መልካም ነገር
ሰበብ ስለሚሆን ነው።
መልካም ስነ-ምግባራችን ብዙዎች
ዲናችንን እንዲወዱ ያደርጋል፣ በህይወት
እያለንም ይሁን ከሞትን በኋላ ያስታወሱን
ሁሉ ዱዓእ ያደርጉልናል።
መጥፎ ስነ-ምግባር ደግሞ ከዚህ
በተቃራኒ ብዙ ችግሮችን ያስከትላል።
ስለዚህ ሙስሊሞች ሆይ፥ ባላችሁበትና
በሄዳችሁበት ሁሉ መልካም ስነ-ምግባርን
ተላበሱ! ትሁት፣ ቅን፣ ታጋሽና ቻይ፣ አዛኝ፣
ለጋስና ታታሪ፣ ታላቅን አክባሪና ታናሽን
መካሪ ወዘተ እንሁን።
ይሄኔ አሏህ ይወደናል፣ ትክክለኛ የነቢዩ ﷺ ተከታይም እንሆናለን፣ ነገ በኣኺራም
ከርሳቸው ቅርብና ጎረቤት የመሆንን
እድል እናገኛለን!
አሏህ ሆይ፥ ውጫዊ ገጽታዬን/ አፈጣጠሬን እንዳሳመርከው ሁሉ
ስነ-ምግባሬንም አሳምርልኝ!
አሏህ በተከበረው ቃሉ እንዲህ ይላል:-
وَتَزَوَّدُوا فَإِنَّ خَيْرَ الزَّادِ التَّقْوَىٰ ۚ وَاتَّقُونِ
يَا أُولِي الْأَلْبَابِ
"ስንቅ ያዙ፤ ከስንቆች ሁሉ በላጩ አሏህን
መፍራት ነው፤ የአእምሮ/ የልብ ባለቤቶች
ሆይ ፍሩኝ" ሱረቱል በቀራ /197
↷⇣🌹⇣↷
Mostrar más ...