El servicio también está disponible en tu idioma. Para cambiar el idioma, pulseEnglish
Best analytics service

Add your telegram channel for

  • get advanced analytics
  • get more advertisers
  • find out the gender of subscriber
Categoría
Ubicación del canal e idioma

all posts ሰሌዳ | Seleda

የመረጃዎች ቁንጮ የሆነውን ሰሌዳ ለሚወዱት ጓደኞችዎ እና ቤተሰብዎ ያካፍሉ። አንድ ላይ፣ ዘምነን እንቆይ!  @seleda_support  ለማንኛውም አይነት ጥያቄ 
50 501-33
~6 573
~20
12.81%
Calificación general de Telegram
Globalmente
20 040lugar
de 78 777
157lugar
de 396
En categoría
1 103lugar
de 3 169
Archivo de publicaciones
የከንቲባዋ እና የጠቅላይ ሚኒስቴሩ ደሞዝ ተቃራራ መሆንኑ ግን ልብ ብለዋል😴 ጨዋታን ጨዋታ ያነሳዋል እንዲሉ አበው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ ወርሃዊ ደሞዛቸው 20ሺህ ብር መሆኑን ዛሬ መንግስታዊ ሚድያዎች ሲዘግቡት ውለዋ፤ እኛም አድርሰናችሁ ነበር። ታድያ ከንቲባዋ ወርሃዊ ደሞዛቸው ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ ወርሃዊ ደሞዝ ጋር ተቀራራቢ ነው ይላል የአሻም ቲቪ ዘገባ ደግሞ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ ከአምስት ዓመታት በፊት በአንድ መድረክ ባደረጉት ንግግር ወርሃዊ ደሞዛቸው 400 የአሜሪካ ዶላር ገደማ መሆኑን መግለፃቸው በመጥቀስ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በወቅቱ ለተነሱላቸው በርካታ ጥያቄዎች በሰጡት ምላሽ << እኔ የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ሁኜ በወር አራት መቶ(400) ምናምን ዶላር ነው የምበላው፤ እንደምታውቀው አልሰርቅም >> ብለው ነበር። በአሁኑ የውጭ ምንዛሬ እንግዲ ጠቅላይ ሚኒስቴሩ ወደ 24 ሺ ብር ብቻ ነው ሚያገኙት እንደማለት ነው። በሉ ደና ደሩ🙋‍♂
Mostrar más ...
4 825
28
ሰሜን ለንደን ደርቢ በአርሰናል አሸናፊነት ተጠናቁዋል አርሰናል በመሪነቱ ቀጥሉዋል መድፈኞቹ በሰሜን ለንደን ደርቢው 🔥                              ቶትንሃም 1-3 አርሰናል         ሮሜሮ ⚽️     ሆይበርግ ⚽️ (በራሱ)                          ሳካ ⚽️                        ሀቨርትስ ⚽️
5 992
6
6 574
74
ሳያት ደምሴ ከለዛ ሽልማት መውጣቷን አዘጋጁ ገለፀ ተዋናይት ሳያት ደምሴ ከማንኛውም የሀገር ውስጥ ውድድር ራሷን ማግለሏ የዛሬ 2 ዓመት ገደማ ማሳወቋን ይታወቃል:: ይህንን ተከትሎ የለዛ ሽልማት እስከ አሁን ድረስ እያወዳደራት የነበረ ቢሆንም የእሷን ሀሳብ በማክበር አዘጋጁ ብርሀኑ ድጋፌ በማህበራዊ ገፁ ላይ ይህንን አስፍሯል:: ምርጥ ተዋናይት ምድብ ዕጩዎች 4 ቀርተዋል:: ይህም የሆነው ከአክብሮት ጋር በሚል ተዋናይት ሳያት ደምሴ ከማንኛውም የአገር ውስጥ ውድድር ራሴን ማግለሌ ይታወቅልኝ ባለችው መሠረት ነው ይህ የሆነው :: ሃሣቧን እናከብራለን :: 13ኛው የለዛ ሽልማት የመጨረሻ ዙር እጩዎች ድምፅ መስጠት ሚያዚያ 23 ያበቃል! ብርሀኑ ድጋፌ የለዛ ሽልማት
6 150
2
አትሌት ቀነኒሳ በቀለ አቀባበል ተደረገለት አትሌት ቀነኒሳ በቀለ በሆሳዕና እለት ወደ ሀገሩ ሲገባ በቤተሰቡ፣ በወዳጆቹ ቀነኒሳ ሆቴል አቀባበል ተደረገለት። አትሌት ቀነኒሳ በቀለ በፈታኙ ሎንዶን ማራቶን 2.04.15 በመግባት ሁለተኛ ሆኖ ውድድሩን ማጠናቀቁ ይታወሳል። 📷 Focus Studio
5 354
5
North London Derby 🧤 የአርሰናልን የዋንጫ ጉዞ የሚወስነው ሌላኛው ተጠባቂ ጨዋታ በለንደን ተቀናቃኖቹ መሀል ይካሄዳል የእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ በ 35ኛ ሳምንት የጨዋታ መርሀ ግብሮቹ የከተማ ባላንጣዎቹን ቶተንሀም ሆትስፐርስ ከ አርሰናል ያገናኛል። የሊጉን መሪነት የተቆናጠጡት አሰናሎች የቻምፒየንስ ሊግ ቦታን ይዞ ለማጠናቀቅ እየተጫወቱ ያሉትን ቶተንሀም ሆትስፐርስ ይገጥማሉ። 35ኛ ሳምንት እንግሊዝ ፕሪምየር ጨዋታ ቶተንሀም ሆትስፐርስ ከ አርሰናል የጨዋታ ሰዓት - ቀን 10:00 ስታድየም - ቶተንሀም ሆትስፐርስ ስታድየም
5 923
5
አሜሪካ ለዓለም ፍጻሜ መሸሸጊያ የሚውል አውሮፕላን እንዲሰራ አዘዘች🫢 ይህ የክፉ ቀን መሸሸጊያ አውሮፕላን 13 ቢሊዮን ዶላር ወጪ ፈጃል ተብሏልሴራ ኔቫዳ ኮርፖሬሽን የተሰኘው ተቋም ይህን ግዙፍ አውሮፕላን ለመስራት ተስማምቷል አሜሪካ ለዓለም ፍጻሜ መሸሸጊያ የሚውል አውሮፕላን እንዲሰራ አዘዘች፡፡ የዓለማችን ልዕለ ሀያል ሀገር አሜሪካ እንደ ኑክሌር አይነት ጦርነት ቢነሳ ከአደጋ መጠበቅ የሚቻልበት አውሮፕላን እንዲሰራ ማዘዟ ተገልጿል፡፡ እንደ ሮይተርስ ዘገባ አሜሪካ በ1970ዎቹ የተሰራ የክፉ ቀን መጠለያ አውሮፕላን የሰራች ሲሆን ይህ አውሮፕላን አርጅቷል በሚል አዲስ ልዩ አውሮፕላን እንዲሰራ ስምምነት ላይ ተደርሷል፡፡ ለክፉ ቀን ማምለጫ ይሆናል የተባለው ይህ አውሮፕላንም 13 ቢሊዮን ዶላር ወጪ ይፈጃል የተባለ ሲሆን ሴራ ኔቫዳ ኮርፖሬሽን የተሰኘው ኩባንያ አዲሱን አውሮፕላን እንደሚሰራው በዘገባው ላይ ተጠቅሷል፡፡ ኢ-4ቢ የተሰኘ ስያሜ ያለው ይህ አዲስ አውሮፕላን አውሮፕላን በፈረንጆቹ 2036 ላይ እንደሚጠናቀቅም ተገልጿል፡፡ የአሜሪካ አየር ሀይል ንብረት የሆነው ይህ ልዩ የክፉ ቀን መሸሸጊያ አውሮፕላን የሀገሪቱ ፕሬዝዳንትን ጨምሮ ሌሎች ቁልፍ አመራሮች፣ ባለሙያዎች እና ሌሎች እጅግ አስፈላጊ የሆኑ መረጃዎች እና ቴክኖሎጂዎችን ይዟል ተብሏል፡፡ እንዲሁም አውሮፕላኑ እንደ ኑክሌር ጦርነት፣ አውዳሚ አደጋዎች እና ሌሎች አስጊ ክስተቶች ቢከሰቱ መሪዎች በዚህ አውሮፕላን ላይ በመሆን ትዕዛዝ እና ውሳኔዎችን እንዲያካሂዱ ያገለግላልም ተብሏል፡፡ የመሰብሰቢያ ቢሮዎች፣ የነዳጅ መሙያዎች እና የተግባቦት መሳሪያዎችም ያሉት ሲሆን አሁን በስራ ላይ ያለው የክፉ ቀን መሸሸጊያ አውሮፕላን ከ2030 በኋላ ከአገልግሎት ውጪ እንደሚሆን ተገልጿል፡፡(Alain)
Mostrar más ...
6 119
31
ታንዛኒያ‼ ታንዛኒያ ውስጥ በከባድ ዝናብ የ115 ሰዎች ሲሞቱ፣ 200ሺሕ የሚሆነት ደግሞ ገፈት ቀማሽ ሆኑ። በድንገተኛው ከባድ ዝናብ 115 ሰዎች ሲምቱ፣ 236 ጉዳት እንደደረሰባቸው፣ 200 ሺሕ ሰዎች ደግሞ የአደጋው ገፈት ቀማሽ እንደሆኑ ተነግሯል። ዝናቡ ጎርፍ  እና የመሬት መንሸራተት አደጋ ማስከተሉን ጠቅላይ ሚኒስትር ቃሲም ማጃሊዋ ተናግረዋል። ታንዛኒያን ጨምሮ አብዛኛዎቹ የምስራቅ አፍሪካ ሀገራት ከፍተኛ የጎርፍ ጉዳት እየገጠማቸው እንደሚገኝ ቻነልስ ቲቪን ጠቅሶ thiqaheth አስነብቧል።
6 288
5
ሆሳዕና በአርያም 🌴 እንኳን አደረሳችሁ የ “ሆሳዕና በአርያም” በዓል በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ እና በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን አማኞች ዘንድ ዛሬ በድምቀት እየተከበረ ነው፡፡ ሆሳዕና በአርያም ከፋሲካ በፊት ያለው እና የዐቢይ ጾም የመጨረሻው ሣምንት ሲሆን÷ “አቤቱ እባክህ አሁን አድን፣ አቤቱ እባክህ አሁን አቅና፣ በእግዚአብሔር ስም የሚመጣ ብሩክ ነው” የሚሉ ትርጉሞችም እንዳሉት የዕምነቶቹ አባቶች ያስተምራሉ። የዕምነቶቹ ተከታዮች በሆሳዕና በአርያም በዓል መሪው ተመሪውን ዝቅ ማለትን ያስተማረበት እና ተመሪውም የሚመራውን ጨርቁን እያነጠፈ እና ዘንባባ እየጎዘጎዘ ያከበረበት የትህትና እና የፍቅር በዓል ተደርጎ የሚወሰድ ነው፡፡ ሆሳዕና በአርያም ኢየሱስ ክርስቶስ በአህያ ጀርባ ተቀምጦ ወደ ኢየሩሳሌም ሲገባ በተለይም÷ አረጋውያን፣ ሴቶች፣ ወንዶች፣ ወጣቶች እና ሕጻናት “ሆሳዕና ለዳዊት ልጅ፣ ሆሳዕና በዓርያም” በማለት በክብር መቀበላቸው የሚታወስበት በዓል ነው፡፡
Mostrar más ...
5 994
15
🔴 የውጪ ባለሃብቶች በተከለሉ የወጪ፣ የገቢ፣  የጅምላ እና የችርቻሮ ንግድ ኢንቨስትመንቶች የሚሳተፉባቸው ሁኔታዎች ምን ምን ናቸው? ከላይ የተያያዘውን መረጃ ይመልከቱ👆
6 143
16
«ምንም አታመጡም አይነት አካሄድ ከፍላችሁ የማትጨርሱት እዳ ውስጥ ይዞችሁ ይገባል» ስትል አርቲስት ቤዛዊት መስፍን አስጠነቀቀች "እስር ቤት ለሴት ልጅ እጅግ ከባድ ነው" በማለት አስተያየቷን የጀመረችው ተዋናይት ቤዛዊት መስፍን ተዋናይት አዲስአለም ጌታነህ ጨምሮ ሌሎች ጎደኞቼ በገዛ ፍቃዳቸው እና ገንዘባቸው በየ ክፍለሀገሩ በመሄድ ወግ እና ልማዳቸውን ባህላቸውን የሚያስተዋውቁ ምንም ውስጥ የሌሉ ሴቶች ናቸው፣ ከዛሬ ነገ ይፈታሉ ብለን ብናስብም ይሄው እስከዛሬ አልተፈቱም እና እባካችሁ ሰው በሀገሩ በነፃነት እንዲኖር ፍቀዱለት በገዛ ሀገራችን እና ርስታችን አታሸማቁን በሀገራችን ተስፋ እንድንቆርጥ እንድንሰደድ አታድርጉን! ፍቱልን እህቶቻችን ሰትል አርቲስት ጓደኞቿ እንዲፈቱ በማህበራዊ ገጿ ላይ ያሰፈረችውን ፅሁፍ ፋስት መረጃ ተመልክቷል። እስከ ዛሬ በእህቶቼ ዙሪያ ምንም ያላልኩት ነገሮች እንዳይካበድባቸው በማሰብ ነው በማለት ዝምታዋን መስበሯን ገልጻለች። «ህዝቡን ብታከብሩት እና ብትፈሩት ይሻላል ይሄ ምንም አታመጡም አይነት አካሄድ ከፍላችሁ የማትጨርሱት እዳ ውስጥ ይዞችሁ ይገባል» ስትል ቤዛዊት መስፍን ከዱባይ አስጠንቅቃለች። fastmereja
Mostrar más ...
5 748
7
ፈተናው በኦላይን ይሰጣል ተብሏል የ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና በተመረጡ ከተሞች በኦን ላይን ለመስጠት እየተሠራ መሆኑን ተገልጿል። የትምህርት ሚኒስትሩ ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ በአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ምክክር መድረክ ላይ ባደረጉት ንግግር የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና በተመረጡ ከተሞች በኦንላይን ለመስጠት እየተሠራ መሆኑን ገልፀዋል ። የ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ሙሉ በሙሉ በኦንላይን ለመስጠት ባይቻልም በሁሉም ክልሎች በተመረጡ ከተሞች ለመስጠት እየተሠራ መሆኑን ተናግረዋል። በዚህም በሁሉም ክልሎች ያሉ የተመረጡ ተማሪዎች በኦንላይን ፈተናቸውን የሚወስዱ ሲሆን ቀሪዎቹ ደግሞ በተለመደው አግባብ ፈተናቸውን ይወስዳሉም ብለዋል። የሀገር አቀፍ ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር (ዶ/ር) እሸቱ ከበደ በበኩላቸው ፈተናውን በኦንላይን ለመሥጠት የሚያስችል የቅድመ ዝግጅት ሥራ እየተሠራ መሆኑን ገልፀዋል። ተማሪዎች የሙከራ ፈተና የሚለቀቅላቸው ሲሆን ደጋግመው እንዲሞክሩና እንዲለማመዱ ይደረጋልም ከሚኒስቴሩ የተገኘው መረጃ ያመላክታል። ለዚህም እንዲረዳ የአሰልጣኞች ስልጠና በመሥጠት ተማሪዎች ተደጋጋሚ ስልጠና እንደሚሠጣቸውም ዋና ዳይሬክተሩ ገልፀዋል። ከቀጣይ ሳምንት ጀምሮ የአሰልጣኞች ስልጠና መስጠት እንደሚጀምርም በመድረኩ ተገልጿል።
Mostrar más ...
6 224
4
ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ፣ በአገሪቱ የሚዘረጋቸውን የቴሌኮም ታዎሩች ብዛት በቀጣዮቹ ሦስት ዓመታት በሦስት እጥፍ ለማሳደግ ማቀዱን እንደገለጠ ሪፖርተር ጋዜጣ ዘግቧል። ኩባንያው ባሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ 2 ሺህ 500 የቴሌኮም ታዎሮች ያሉት ሲኾን፣ 1 ሺህ 500ዎቹ ታዎሮች ከኢትዮ ቴሌኮም ኩባንያ የተከራያቸው ናቸው። ኾኖም መላ አገሪቱን ለመሸፈን 7 ሺህ ታዎሮች እንደሚያስፈልጉት የኩባንያው ሃላፊዎች እንደነገሩት ዘገባው ጠቅሷል። ዘገባው፣ በአገሪቱ በርካታ አካባቢዎች የተከሰቱ የጸጥታ ችግሮች ግን በኩባንያው እቅዶች ላይ ትልቅ እንቅፋት ደቅነውብኛል ማለቱንም ዜና ምንጩ አመልክቷል።
6 994
8
" ኑሮ ውድነቱ መፍትሄ ይሻል። መፍትሄ እንሻለን " - የኢሰማኮ ፕሬዝዳንት ካሳሁን ፎሎ የኢትዮጵያ ሰራተኞች ማህበራት ኮንፌዴሬሽን (ኢሰማኮ) ፕሬዝዳንት ካሳሁን ፎሎ ከኑሮ ውድነቱ አንፃር የዘገየው የሰራተኞች ዝቅተኛ የደሞዝ ወለል እና የግብር ቅነሳ ምላሽ ማግኘት እንዳለበት ገልፀዋል። " አሁንም በቀን አንድ ጊዜ ብቻ በልቶ ለመዋል የሚቸገር ሰራተኛ ነው ያለው " ያሉት አቶ ካሳሁን ሰራተኛው ካለው ገቢ አንፃር ችግሩ የሰፋ እንደሆነ አስረድተዋል። እነዚህ ጥያቄዎች በአዎንታዊ መልኩ መታየት እንዳለባቸው ጠቁመዋል። አቶ ካሳሁን " ዝቅተኛ የደሞዝ ወለል በሚመለከት ስራና ክህሎት ሚኒስቴር የዝቅተኛ የደሞዝ ወለል የሚወስን ቦርድ የሚቋቋምበት ደምብ ላይ ጥናት ማድረጋቸውን በቅርቡ አሳውቀውናል " ሲሉ ተናግረዋል። የኑሮ ውድነት በጣም አሳሳቢ እየሆነ በመምጣቱ ሰራተኛው ችግር ውስጥ መግባቱን የጠቆሙት ፕሬዝዳንቱ " ትክክለኛ ግብር ከፋይ ሰራተኛው ነው። ለመንግስት ቀኝ እጁ በሚከፍለው ግብር ሰራተኛው ነው። የግብር ቅነሳው አንድ እና ሁለት የለውም ዘግይቷል " ሲሉ ጠቁመዋል። አቶ ካሳሁን ፤ ሚያዚያ 23 ቀን በኢትዮጵያ ለ49ኛ ጊዜ በሚከበረው ዓለም አቀፉ የሠራተኞች ቀን (ሜይዴይ) አዳራሽ ውስጥ እንደሚከበር አሳውቀዋል። " አሁንም ቢሆን ባልተመለሱልን ጉዳዮች ላይ ነው የምንወያየው። የቀኑ መሪ ቃል ' ለሰላም እና ለኑሮ ውድነት መፍትሄ እንሻለን ' የሚል ነው ብለዋል። " የሰላም ችግር አለ። ሰራተኞች በአንዳንድ ቦታዎች ይታገታሉ ፣ ይሞታሉ " ያሉት አቶ ካሳሁን ፎሎ ፤ " ይሄ እስከ መቼ ይቀጥላል ? ማንኛውም ማህበረሰብ ላይ እንደሚደርሰው ጉዳት ሁሉ ሰራተኛውም ላይ እየደረሰ ነው ፤ ስለዚህ ለሰላም መፍትሄ መምጣት አለበት " ሲሉ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል። (ቲክቫህ ኢትዮጵያ)
Mostrar más ...
7 212
6
ሶል በዳይመንድ ሊግ 5ሺ ሜትር አንደኛ በመውጣት ወደ አሸናፊነት ተመልሷል። welcome back sol🥰
6 876
1
ሊቨርፑል ያከተመለት ይመስላል🥺 35ኛ ሳምንት የእንግሊዘ ፕሪምየር ሊግ ጨዋታ                       ⏰ ተጠናቀቀ    ዌስትሃም ዩናይትድ 2-2 ሊቨርፑል      43'            48'        77'        (OG) 65' 🏟 ለንደን ስታድየም
6 303
1
ፑላ አድቫይዘርስ ለ 122 ሺህ አርሶአደሮች 39 ሚሊዮን ብር የሰብል መድህን ካሳ ክፍያ ፈፀመ በግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢንስቲትዩት ፣ በአለም ምግብ ፕሮግራም እና በፑላ አድቫይዘር ጥምረት በኢትዮጵያ ትልቁን የሰብል መድህን ፕሮግራም የክፍያ ስርአት በትናንትናው እለት በሀያት ሪጀንሲ የጀመሪያውን ፕሮግራም አከናውኗል። በኢትዮጵያ የሰብል መድህን ታሪክ ዉስጥ ትልቁ መሆኑ በተነገረለት ይህ ፕሮግራም የኦሮሚያ ኢንሹራንስ ኩባንያ ለዚህ ፕሮግራም የመድህን ውል ሰጪ እና የካሳ ከፋይ ተቋም በመሆን አገልግሏል። የመጀመሪያው ምዕራፍ እንደሆነ በተገለጸው በዚህ ስርዓት እንደመጀመሪያ በአማራ ክልል የሚገኙ አነስተኛ አርሶአደሮች ተጠቃሚ ያደረገ ሲሆን በቀጣይ በተለያዩ ክልሎች ለሚገኙ ለ 7.5 ሚሊዮን አርሶአደሮች ተደራሽ እንደሚሆንም ከፕሮግራሙ ለመረዳት ችለናል። በመጨረሻም የመድህን ካሳ ክፍያ ቼክ አርሶ አደሮችን በመወከል ለተገኙ አርሷደሮን እና ለአማራ ክልል ግብርና ቢሮ ተበርክቷል። (EthioTube)
Mostrar más ...
6 365
2
" በቀጣይ አመት ማንችስተር ዩናይትድ የሊጉን ዋንጫ ለማሸነፍ የሚፎካከርበት ሁኔታ ላይ አይደለም " አሰልጣኝ ኤሪክ ቴንሀግ🤨 ይህን ያሉት ከዛሬው የበርንለይ ጨዋታ በፊት ሲሆን አሰልጣኙ እንደሚሉት ለአራት ውስጥም የምንፎካከረው ሁሉም ጉዳት ላይ ያሉ ተጨዋቾቻችን ከተመለሱልን ብቻ ነው ብለዋል። አያይዘውም ኔዘርላንዳዊው አሰልጣኝ በመጭው ክረምት ጥሩ የሚባል ዝውውሮች ካደረግን ምናልባት ለዋንጫ ከሚፎካከሩት ቡድኖች ጋር የመጠጋት እድል አለን ብለዋል።
6 482
4
አትሌት መዲና ኢሳ በ5 ኪሎ ሜትር ከ20 ዓመት በታች የሩጫ ውድድር የዓለም ክብረ ወሰን ሰበረች የአዲዳስ ኩባንያ ባዘጋጀው አዲዜሮ የ5ኪሎ ሜትር ውድድር አትሌት መዲና ኢሳ ከ20 ዓመት በታች የዓለም ክብረ ወሰንን በመስበር አሸነፈች፡፡ የ19 ዓመቷ አትሌት መዲና ርቀቱን 14 ደቂቃ ከ38 ሰከንድ በማጠናቀቅ ነው የዓለም ክብረ ወሰንን በመስበር ጭምር ያሸነፈችው፡፡ በዚሁ ውድድር አትሌት መልክናት ውዱ ሁለተኛ እንዲሁም ፎቲየን ተስፋይ ሦስተኛ ደረጃን በመያዝ አጠናቅቀዋል፡፡ በወንዶች ዮሚፍ ቀጄልቻ በ13 ደቂቃ በመግባት ሲያሸንፍ ይሁኔ አዲሱ በ5 ሴኮንዶች ዘግይቶ በመግባት ሁለተኛ ደረጃን ይዞ አጠናቋል፡፡(ፋና)
6 750
3
650ሺህ ብር የተጠራው ሰንጋ😳 ታላቁ የሆሳዕና ገበያ በዘንድሮው አመት ያልተጠበቁ ሪከርዶችን ይዞ ተከስቷል። ወጣት ሚጥዬ ታደለ በእነዋሪ ከተማ አስተዳደር ነዋሪ ነው። ወጣቱ በከብት ማድለብ ስራ ከተሰማራ በርካታ አመታትን አስቆጥሯል። በ2016 ዓ.ም በእነዋሪ ከተማ አስተዳደር ከግማሽ ሚሊዮን ብር በላይ ያወጣል የተባለውን በጣዕሙ እና በአይነቱ ልዩ የሆውን የጅሩ ሰንጋ በሬ አድልቧል። ወጣት ሚጥዬ በንግግሩ በዘንድሮው አመት በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥም ሆነን ሁላችንም የጅሩ አርሶ አደሮች ጣዕም ያለውን ሰንጋ አድልበናል ጊዜውን ጠብቀንም ለገበያ አምጥተናል ሲል ለእነዋሪ ከተማ አስተዳደር ሚዲያ ተናግሯል። 650ሺህ ብር የተጠራው የጅሩስ ሰንጋ ስንት ብር ይሸጥ ይሆን? እየተባለ ገዢዎችን እየጠበቀ ነው።(FastMereja)
6 851
68
መልካምነት ለእራስ ነው 🥰 በአጋጣሚ ከማያቁት ሰው በርከት ያለ ገንዘብ በባንክ አካውንቱ ቢላክሎ ምን ያደርጋሉ ??? 🤔 ነገሩ እንዲህ ነው በአሰሪ እና ሰራተኛ አገናኝ እንዲሁም በድለላ ስራ ቤተሰቡን የሚያስተዳደር የባቱ ከተማ ነዋሪ የሆነው አቶ ቱፋ ሰለሞን የተለመደውን ስራ ለመስራት የእለት እንጀራውን ለማግኝት በስራው ለይ እያለ ባጋጣሚ ወደ ባንክ አካውንቱ 2,000,000 ብር ይገባል። የዚን ጊዜ ከየት የመጣ በረከት ነው ብሎ ብሩን አውጥቶ ለመጠቀም አይደልም ያሰበው ከየት እንደመጣ ለማውቅ ነው የቸኩለው በስህተትም ይሆናል ብሎ አስቦ ነበር። ፈላጊው እስኪገኝ ድረስ ለ1 ወር ያክል ገንዘቡን ሳይነካ ባለቤቱ እስኪመጣ ሲጠባበቅ ነበር። በመጨረሻም ከ1 ወር ቁይታ በዋላ አብነት ግርማ የተባለች የአዲስ አበባ ነዋሪ በስህተት ወደ ቱፋ ሰለሞን አካውንት ማስገባቷ ከተረጋገጠ በዋላ አቶ ቱፋ ሰለሞን ገንዘቡን ለባለቤቷ በመመለስ ታማኝነታቸውን አሳይተዋል። ለፍቶ አዳሪው አቶ ቱፋ ለታማኝነታቸው ምስጋና ይገባቸዋል 🙏🙏🙏
Mostrar más ...
6 761
5
ጊፍት ሪል ስቴት ከመንግስት ጋር በአጋርነት 2 ሺህ ቤቶችን በ3 ዓመታት ውስጥ ለመገንባት ስምምነት ተፈራረመ የአዲስ አበባ ከንቲባ አዳነች አቤቤ በተገኙበት ጊፍት ሪል ስቴት ከመንግስት ጋር የሚሰራዉን የቤቶች ፕሮጀክት ግንባታ በይፋ አስጀመረ። አዲስ ማለዳ በተገኘችበት በዚህ መርሃ ግብር ጊፍት ሪል ስቴት በዋና ከተማዋ ለገሃር አካባቢ በመጀመሪያ ዙር ግንባታ 4 ሺህ ቤቶችን መስራት መጀመሩ ተገልጿል። በሪል ስቴቱ የለገሃር መኖሪያ መንደር አነስተኛ እና መካከለኛ ገቢ ያላቸው የህብረተሰብ አካላትን በተመጣጣኝ ዋጋ ተደራሽ እንደሚያደርግ ጊፍት ሪል ስቴት አስታወቋል። የዚህ የጊፍት ሪል ስቴት የለገሀር የመኖሪያ መንደር ፕሮጀክት ግንባታ በ3 ዓመታት ውስጥ የሚጠናቀቅ ሲሆን 3 ሺህ 540 የመኖሪያ እንዲሁም 460 የንግድ ቤቶች እንደሚኖሩት አዲስ ማለዳ ሰምታለች። የመኖሪያ መንደሩ ትምህርት ቤት እና ሌሎች ማህበራዊና ማህበረሰባዊ መገልገያዎችን ያካተተ እንደሚሆን የተገለጸ ሲሆን የሕንጻዎቹ ከፍታ ከ14 እስከ 22 ወለል ይሆናል ተብሏል። በሁለተኛ ዙር ለሚገነቡ 8 ሺህ የመኖሪያና የንግድ ቤቶች ግንባታ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑም ተመላክቷል። addismaleda
Mostrar más ...
7 038
10
ቲክቶከሯ በአሰቃቂ ሁኔታ ተገደለች 😭 አቢ ትባላለች ቲክቶክ ላይ የምትሸጣቸዉን የባሕል ልብሶች በማስተዋወቅ ትታወቅ ነበር።ጦር ሐይሎች አካባቢ ጂም ቤት ዉስጥ የሚያሠራት አሠልጣኝ በአሰቃቂ ሁኔታ በስለት ገድሏታል። የግድያዉ ምክንያት ደሞ ለምን ቲክቶክ ላይ ጂም ቤት ዉስጥ የምሰሪዉን ቪዲዮ ለምን ለቀቅሽ የሚል ነዉ።እናቷ የፍትሕ ያለ እያሉ ነዉ።አቢ የ5 አመት ሴት ልጅ እናት ነበረች። ነፍስ ይማር😥
6 398
21
የሊቨርፑል ቀጣዩ አሰልጣኝ ታውቋል ! ሊቨርፑል በቀጣይ ክረምት ከክሎፕ ጋር ከተለያየ በኋላ የሱ ተተኪ በመሆን የፌዮኖርዱ አሰልጣኝ አርኔ ስሌት ወደ አንፊልድ እንደሚሄድ ተረጋግጧል። በ2024/25 ለሊቨርፑል አዲስ ምዕራፍ ይጀምራል ።
6 856
8
አዲስ አበባ በርካታ የፖሊስ አባላት በቁጥጥር ስር እየዋሉ ነው ተብሏል። የአዲስ አበባ ፀጥታ ቢሮ እንዳስታወቀው ከሆነ ከሚሰጣቸው ሀላፊነት እና ስልጣን ውጪ ሲንቀሳቀሱ የነበሩ በርካታ የፀጥታ ሀይሎች በቁጥጥር ስር እንዲውሉ መደረጉን እና ህጋዊ እርምጃ እየተወሰደ መሆኑን ይፋ አድርገዋል። የከተማዋ አንዳንድ የፀጥታ አካላት በአማራ ክልል የተጣለውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ተገን በማደረግ ህገወጥ እስራት እና እንግልት እንደፈፀሙ ሪፖርተር ጋዜጣ ዘግቧል። የአዲስ አበባ ሰላም እና ፀጥታ ቢሮ በአማራ ክልል የተጣለው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ በአዲስ አበባ እንደማይገበር ገልፀው ከተማው ውስጥም ጉዳዮች ሲኖሩ በየትኛውም ሰዓት ኦፕሬሽን እንደሚሰራ ጠቁመዋል። በቅርቡ በተደረገው ፍተሻ ከ140ሚሊዮን ብር በላይ በቁጥጥር ስር መዋሉ ተጠቁሟል።በዚህም 1.5 ሚሊዮን ብር በቁማር የተሰበሰበ ብርን ጨምሮ ሌሎች ሀሰተኛ የብር ኖቶች ተይዘዋል ተብሏል። ከዚህ በተጨማሪም ከ16,000 በላይ ተተኳሿችን ጨምሮ የስውር ትጥቅ እስከ ትልልቅ መሳሪያዎች መያዛቸው ተገልጿል። ለስራ ፍለጋ እና ለሌሎች ጉዳዮች ወደ አዲስ አበባ የሚገቡ የሰዎች ብዛት በአጅጉ መጨመሩን ቢሮዉ አስታውቋል።
Mostrar más ...
6 524
4
CONFIRMED 🔥🔥 አምና ከፕርሜርሊጉ የወረደው ሌስተር ሲቲ በአቱ ተመልሷል።👏 2024/25 የኢንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ላይ ተሳታፊ መሆኑን በይፋ አርጋግጧል። "ጀግንነት አለመውደቅ የሚመስለው፣ ፈሪ ነው። ወድቆ በጥንካሬ የሚነሳ እርሱ ጀግና ነው!!" Welcome back😍😍😍😍😍
6 132
4
ABD እየመጣ ነው😍 “የኔን ስራ ጨርሻለሁ ለአዲስ አልበሜ ተዘጋጁ" - አብዱ ኪያር ተወዳጁ ድምፃዊ አብዱ ኪያር አዲስ አልበሙን ለአድማጭ ለማቅረብ ዝግጅት እያደረገ እንደሚገኝ አስታወቀ:: ድምፃዊዉ በይፋዊዉ የማህበራዊ ትስስር ገፁ እንዳለው "የኔን ስራ ጨርሻለው ደስም ብሎኛል" ሲል በአጭሩ አዲስ አልበሙ መጠናቀቁን ገልፆል:: አብዱ ኪያር 5ተኛ የስቱዲዮ አልበሙ መጠናቀቁን ይግለፅ እንጂ በቅርብ ለአድማጭ ጆሮ እንደሚደርስ ከመጠቆም ውጭ የሚወጣበትን ቀን በግልፅ አላስቀመጠም:: "ከመርካቶ ሰፈሬ" የመጀመሪያ አልበሙ ጀምሮ በተከታታይ የሰራቸው አልበሞቹ ተወዳጅ የሆኑለት አብዱ ኪያር በሙዚቃዎቹ ውስጥ የሚጠቀማቸው ግጥሞችም ለማህበረሰቡ ኑሮ የቀረቡ እና በጥሩ ዜማ ተዋዝተው መቅረባቸው በበርካቶች ያስደንቀዋል::(ኤፍኤም 97.1)
6 253
6
በኮሪደር ልማት 1 ሺህ 135 ሰዎች አሁንም ምትክ ቤት ወይም ቦታ አለማግኘታቸዉን የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት አባል ዶ/ር ሲሳይ መንግስቴ ተናገሩ🤔 👉🏼 ከንቲባ አዳነች አቤቤ በበኩላቸዉ አንድም ሰው ቤት ሳይሰጠው ተነስቶ ሌላ ቦታ የገባ ሰው የለም ብለዋል በትናንትናው የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት መደበኛ ጉባኤ ላይ ጥያቄ ካቀረቡ የምክር ቤት አባላት መካከል አንዱ የሆኑት ዶ/ር ሲሳይ መንግስቴ፤ ከኮሪደር ልማት ተነሺዎች መካከል “1,135 ሰዎች አሁንም ምትክ ቤት ወይም ቦታ አለማግኘታቸውን” በማንሳት ጥያቄ አቅርበዋል። “1,135 ሰው ማለት ቀላል አይደለም። በዚህ ወቅት፣ በዚህ የኑሮ ውድነት፣ በዚህ ጊዜ ተረጋግቶ የሚኖርበት አጋጣሚ ካልተፈጠረ፤ የሚሰራውን ስራ ሁሉ በዜሮ ድምር የሚያባዛ ነው የሚሆነውና እርሱ ለምን ግምት ውስጥ አልገባም?” ሲሉ መጠየቃቸውን ኢትዮጵያ ኢንሳይደር አስነብቧል። የአዲስ አበባ የኮሪደር ልማት ፕሮጀክት በ90 ቀናት እንዲጠናቀቅ እቅድ እንደተያዘለት በመጥቀስም፤ “የግድ በዚህ ሶስት ወር ውስጥ ስራ ማለቅ አለበት ወይ?” ሲሉ ተጨማሪ ጥያቄ አስከትለዋል። “በጊዜ ተለክቶ ስራ መሰራት አለበት፤ ልክ ነው። አምናም የ90 ቀን እቅድ ተብሎ ውጤታማ ስራዎች ተሰርተዋል። ሁልጊዜ ግን በዚህ መልክ በዘመቻ መሰራት አለበት ወይ? የሚል ጥያቄ ይስነሳል” ያሉት ዶ/ር ሲሳይ፤ “ነገሮች በተረጋጋ እና በታቀደ መልኩ እንዲሄዱ ለማድረግ መሰራት የለበትም ወይ?” ሲሉ አስተያየት አዘል ጥያቄ ማንሳታቸውን ዳጉ ጆርናል ከዘገባው ተመልክቷል። ከንቲባ አዳነች አቤቤ ለዚህ ጥያቄ በሰጡት ምላሽ፤ የምክር ቤት አባሉ ከጠቀሷቸው የልማት ተነሺዎች ውስጥ “አንድም ሰው ቤት ሳይሰጠው ተነስቶ ሌላ ቦታ የገባ ሰው የለም። በተለይ የመንግስት ቤት ተከራይ፣ የቀበሌ፣ የኪራይ ቤቶች፣ የቤተክህነት ጭምር ማለት ነው” ብለዋል። የከተማ አስተዳደሩ የልማት ተነሺዎችን በዚህ መልኩ የማስተናገድ አካሄድ ሲከተል “ለመጀመሪያ ጊዜ” መሆኑንም ጠቁመዋል። ዳጉ_ጆርናል
Mostrar más ...
6 743
4
ከ18 ሺህ በላይ የውጭ ዜጎችን ከሀገር ተባረዋል የኢምግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት በሐሰተኛ የመኖሪያ ፍቃድ በአገር ውስጥ ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ከ18 ሺህ በላይ የውጭ አገር ዜጎችን ከአገር ማባረሩን ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ትናንት ባቀረበው ሪፖርት ገልጧል። ከአገር ከተባረሩት መካከል፣ ለሌሎች የውጭ ዜጎች ሐሰተኛ የመኖሪያ ፍቃድ አዘጋጅተው በገንዘብ ሲሸጡ የነበሩ እንደሚገኙበት ተቋሙ ገልጧል። በኢንቨስትመንት ፍቃድ ወደ አገሪቱ የገቡ የውጭ ዜጎች ለበርካታ ዓመታት በሕገወጥ ሥራዎች ላይ ተሳታፊ ኾነው እንደተገኙም ተቋሙ ጠቅሷል።(ዋዜማ)
6 875
6
ለ28 አመት ታጥፎ የኖረውን ግለሰብ ያዳነው የህክምና ጥበብ👏 ሊ ኋ ይባላል፡፡ ቻይናዊ ነው፡፡ ታዲያ ሊ አንኪሎሲንግ ስፖንዲላይትስ (Ankylosing spondylitis) በተሰኘ የአጥንት በሽታ ለ28 አመታት ፊቱን ከጉልበቱ ላይ ማንሳት ሳይችል እንደታጠፈ ኖሯል፡፡ የሊኋ የጀርባ አጥንቶች በጣም ስለታጠፉ መቀመጥም ሆነ መነሳት ወይንም ጋደም ማለት ባለመቻሉ 28 የስቃይ አመታትን አሳልፏል፡፡ ይህ እጥፋቱም የቻይናዊውን ቁመት ወደ 90 ሳንቲ ሜትር አውርዶት ነበር፡፡ ታዲያ እ.ኤ.አ በ2018 ህክምና ሊደረግለት ቢሞከርም ቀዶ ጥገናው እጅግ አደገኛ ስለነበር ሐኪሞቹ ሊሰሩለት አልመረጡም ነበር፡፡ በጊዜ ሂደት ግን ሊኋን ለማዳን ቆርጠው ተነሱ፡፡ በዛ ላይ ኋ ቀና ካልተደረገና በልቡና ሳንባው ላይ ያለውን ጫና መቀነስ ካልተቻለ ሕይወቱ አስጊ ወደ ሆነ ደረጃ በመሸጋገሩ ህክምናው የግድ ሆነ፡፡ በመሆኑም በቻይና ሸንዘን ዩኒቨርስቲ አጠቃላይ ሆስፒታል የአጥንትና መገጣጠሚያ ክፍል ኃላፊ የሆኑት ፕሮፌሰር ዌይረንን ጨምሮ ሌሎች የሕክምና ቡድን አባላት ሊን ቀጥ አድርጎ የሚያራምደውን ህክምና ጀመሩ፡፡ ህክምናው የግለሰቡን ታጥፈው የነበሩትን የጀርባ አጥንቶ አንድ በአንድ እየሰበሩና ድጋሚ ቀጥ አድርጎ የመገጣጠም ስራ ነበር፡፡ በዚህም ከአራት ዙር አስቸጋሪ ቀዶ ጥገናዎች በኋላ የተሳካ ስራ መስራት ችለዋል፡፡ የእግሩ አጥንቶችም እንደዚሁ ተሰብረው መልሰው መጠገን ቻሉ፡፡ ሆስፒታሉ የቀዶ ጥገናውን ክብደት ሲገልጽ የኤቨረስት ተራራን እንደመውጣት ነበር ነው ያለው፡፡ በዚህም ሊ በድንቅ የህክምና ጥበብ ከ28 አመት በኋላ ቀጥ ብሎ መቆምና መራመድ ችሏል፡፡ Via አዲስ ዋልታ
Mostrar más ...
7 707
25
አምና የወረደው ኢትዮ ኤሌክትሪክ ተመልሷል 🔥 የኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ ምድብ አንድን እየመራ የሚገኘው ኢትዮ ኤሌክትሪክ ወደ ኢትዮጵያ ፕርሚየር ሊግ ማደጉን አረጋግጧል። ሁለተኛ ደረጃ ላይ የሚገኘው ኦሮሚያ ፖሊስ ነጥብ መጣሉን ተከትሎ ኢትዮ ኤሌክትሪክ አምስት ጨዋታዎች እየቀሩት ከወዲሁ ወደ ኢትዮጵያ ፕርሚየር ሊግ ማደግ ችሏል። ባለፈው አመት ወደ ታችኛው ሊግ የወረደው ኢትዮ ኤሌክትሪክ ከአንድ አመት ቆይታ በኋላ ወደ ሀገሪቱ ትልቅ ሊግ መመለሱን ማረጋገጥ ችሏል። ምንጭ :- የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን
7 542
2
"የስፖርት ውርርድ / የቤቲንግ ቤቶች ሊታገዱ ይገባል" ሲል የሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳዮች ሚኒስቴር አሳሰበ። ሚኒስቴሩ ዛሬ የ9 ወር የስራ አፈጻጸም ሪፖርቱን ለተ/ም/ቤት አቅርቦ ነበር። በዚህ ወቅት ፤ " የወጣቶች ሱሰኝነት በሀገር ደረጃ እየተባባሰ መጥቷል ፤ በተለይ አሉታዊ መጤ ልማዶች እና አደንዛዥ ዕጽ እንደ ሀገር እየተስፋፋ መጥቷል " ሲል ገልጿል። ይህም ብዙ ወጣቶችን እያሳጣን ነው ሲል አስረድቷል። ወጣቶች ሰብዕና ግንባታ ላይ ተግዳሮት እየፈጠረ ከሚገኘው አንዱ የስፖርት ውርርድ እንደሆነ ያመለከተው ሚኒስቴሩ " የስፖርት ውርርድ ለሀገሪቱ ከሚያስገባው ገቢ አኳያ ብቻ መታየት የለበትም " ብሏል። " ' ስፖርት ቤቲንግ ' ላይ ያሉት፣ ካሁን በፊት የወጡት መመሪያዎች፣ ደንቦች፤ ጥናትን መሰረት አድርገው ሊታገዱ ይገባል " ሲል ገልጿል። ፓርላማውም በዚህ ረገድ እገዛ ሊያደርግ እንደሚገባ አሳስቧል። " ገቢ አንድ ነገር ነው። ሀገር ገቢ ማግኘት አለባት " ያለው መ/ቤቱ ነገር ግን ፦ ➡️ በወጣቶቹ ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ እያስከተለ ስለሆነ፣ ➡️ ብዙ ወጣቶች እያሳጣ ስለሆነ፣ ➡️ ብዙ ቤተሰብም ስለሆነ ሊታገድ እንደሚገባ ገልጿል። በህ/ተ/ም/ቤት የጤና ማህበራዊ ልማት፣ ባህልና ስፖርት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ፤ " ብሔራዊ ሎተሪ ከገቢ ጋር አይቶታል። በዚህም በኩል ደግሞ ሌላ ችግር እየፈጠረ ነው " ያለ ሲሆን " ተማሪዎች ዩኒፎርማቸውን እያወለቁ የስፖርት ውርርድ ቤት ይገባሉ። ስለዚህ መቼ ያጥኑ። አእምሮአቸው ሊጎዳ ስለሚችል ጥንቃቄ ተደርጎ መሰራት አለበት " ብሏል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በስፖርት ውርርድ ላይ በተሰማሩ አገልግሎት ሰጪዎች ላይ በቅርቡ የወሰደውን እርምጃ " ጥሩ ስራ " ሲል አወድሷል። በሌሎች አካባቢዎች በተሞክሮ ሊወሰድ ይገባል ሲል ጠቁሟል። የሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳዮች ሚኒስቴርም ፤ ከስፖርት ውርርድ ጋር በተያያዘ ያለውን የወጣቶች ሁኔታ የወደፊት የትኩረት አቅጣጫ አድርጎ እንዲያየው እና ጠንካራ ክትትል እንዲያደርግ መክሯል። ከዚህ ቀደምም የሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳዮች ሚኒስቴር የስፖርት ውርርድ / ቤቲንግ / ' ' ነው ብሎ እንደሚያምን ገልጾ እንዲታገድ ጥሪ ማቅረቡ ይታወሳል። የብሔራዊ ሎተሪ አስተዳደር ግን ፤ " ቤቲንግ " ' ' እንጂ ' ቁማር ' ነው ብሎ እንደማያምን ገልጾ ነበር። ቤቲንግ አትራፊና ብዙ ወጣቶች ስራ እንዲያገኙ ያደረገና በከፍተኛ ሁኔታ ገንዘብ እንዲንቀሳቀስ የሚያደርግ መሆኑንም አስረድቶ ነበር። በስርዓት እንዲመራም መመሪያዎች ወጥተውለት እየተሰራ መሆኑን በመግለጽ " እኛ ጨዋታውን አቅርበናል ተጫዋቹ ደግሞ በኃላፊነት መጫወት አለበት " ሲል ነበር የመለሰው። via - tikvahethiopia
Mostrar más ...
8 014
6
7 017
0
የከባድ ተሽከርካሪ አሽከርካሪዎች በፍተሻ ኬላዎች አላግባብ ከፍተኛ ገንዘብ እንዲከፍሉ እየተጠየቁ ነው ተባለ ለአገር አጠቃላይ የምጣኔ ሀብት እንቅስቃሴ ዋነኛ መሆኑ የሚነገርለት የትራንስፖርቱ ዘርፍ በርካታ ፈተናዎች እንደተጋረጡበት ያስታወቀው የከባድ ተሽከርካሪ አሽከርካሪዎች ማህበር ነው፡፡ የማህበሩ ስራ አስኪያጅ አቶ ሰለሞን ዘውዴ ከዚህ ቀደም የረጅም ርቀት አሽከርካሪዎች እገታ፤ ዝርፊያ፤ ግድያ እና ሌሎች ጥቃቶችም ሲደርስባቸው እንደነበር ገልጸው፤ አሁን ላይ ግን በአንጻራዊነት መሻሻሎች እንዳሉ ጠቁመዋል፡፡ ይሁን እንጂ አሁን ላይ አሽከርካሪዎች በሚያቀኑባቸው አከባቢዎች ባሉ የፍተሻ ኬላዎች አላግባብ እንዲከፍሉ የሚጠየቁት ገንዘብ ከፍተኛ መሆኑን እና ይህም በዘርፉ ላይ ችግር እየፈጠረ እንዳለ ተናግረዋል፡፡ ስራ አስኪያጁ እንደሚሉት ከሆነ ተሸከርካሪዎች በሚንቀሳቀሱባቸው ኬላዎች ከ5ሺህ እስከ 30 ሺህ የሚደርስ ገንዘብ እንዲከፍሉ እየተገደዱ ነው፡፡ ዘርፉ ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ የተለያዩ ፈተናዎች እንደተጋረጡበት ማህበሩ ያስታወቀ ሲሆን፤ የትራንስፖርት እና ሎጀስቲክ ሚኒስቴር በበኩሉ በአሽከርካሪ እና ተሽከርካሪዎች ላይ እየደረሰ ያለውን ጥቃት ለማስቆም ከባለድርሻ አካላት ጋር በመቀናጀት እየሰራው ነው ማለቱ የሚታወቅ ነው፡፡(መናኸሪያ ሬዲዮ)
Mostrar más ...
7 185
6
የቢል እና ሜሊንዳ ጌትስ ፋውንዴሽን በተለያዩ ዘርፎች የሚሰጠው ድጋፍ ለኢትዮጵያ እድገት ከፍ ያለ አስተዋጽዖ ያለው ነው፡- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የቢል እና ሜሊንዳ ጌትስ ፋውንዴሽን በተለያዩ ዘርፎች የሚሰጠው ጠቃሚ ድጋፍ ለኢትዮጵያ እድገት ከፍ ያለ አስተዋጽዖ ያለው ነው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ባሰፈሩት መልዕክት፤ "ዛሬ የቢል እና ሜሊንዳ ጌትስ ፋውንዴሽን ዋና ሥራ አስፈፃሚ ማርክ ሱዝማን እና ቡድናቸውን በመቀበሌ ደስታ ተሰምቶኛል" ሲሉ ገልጸዋል። የቢል እና ጌትስ ፋውንዴሽን በግብርና፣ ጤና፣ በስርዓተ ምግብ፣ በአካታች የፋይናንስ ስርዓት እና በሌሎች ዘርፎች የሚሰጠው ጠቃሚ ድጋፍ ለኢትዮጵያ እድገት ከፍ ያለ አስተዋጽዖ ያለው መሆኑን ተናግረዋል። ይህን ትብብር በማላቅ እና በአዳዲስ ዘርፎች በመተባበር እንሰራለን ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ።
Mostrar más ...
6 745
5
ራይድ በኤሌክትሪክ መኪና የታገዘ የትራንስፖርት አገልግሎት መጀመሩን አስታወቀ ራይድ የአረንጓዴ ትራንስፖርት አገልግሎት አካል የሆነውን የኤሌክትሪክ መኪኖች አገልግሎትን ማስጀመሩን በዛሬው እለት በአድዋ ሙዚየም የተለያዩ ተቋማት ሚንስትሮች፣ የአዲስ አባባ ከተማ አስተዳደር የሥራ ኃላፊዎች፣ ሌሎች ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት፣ የዓለም አቀፍ እና የአህጉራዊ ድርጅት ተወካዮች፣ አምባሳደሮች እና ዘርፉን ለማሳደግ ከፍተኛ ጥረት እያደረጉ የሚገኙ ግለሰቦች በተገኙበት ገልጿል፡፡ የራይድ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ሳምራዊት ፍቅሩ የራይድ የትራንስፖርት ዘርፉ ወደ ኤሌክትሪክ መኪኖች የሚያደርገዉን ሽግግር በይፋ በሚጀመርበት በዚህ ቀን እንደገለጹት በሀገራችን የአረንጓዴ ትራንስፖርት ዘርፉን ለማስፋት እየተደረገ ያለዉን ርብርብ ራይድ በርካታ የኤሌክትሪክ መኪኖችን ወደ አገልግሎት በማስገባት ከቴከኖሎጂው ፈር ቀዳጆች ተርታ ተቀምጧል ብለዋል ከ2006 ዓ.ም ጀምሮ በሞባይል መተግበሪያ እና በጥሪ ማዕከል አማካኝነት ቀልጣፋ የትራንስፖርት አገልግሎት በማቅረብ ላይ የሚገኘዉ ራይድ የኤሌክትሪከ መኪኖች ወደመገልገል መሸጋገሩ የተገለፀ ሲሆን ይህ አግልግሎቱ "የራይድ ራዕይ 2030” አንዱ (RIDE'S 3G, Vision 2030) ማስጀመሪያ ጭምር መሆኑም ተነግሯል። እነዚህ የተስላ ብራንድ የሆኑት ከ150 በላይ የኤሌክትሪክ መኪኖች ወደ አገልግሎት የሚገቡበት የመጀመሪያ ዙር የራይድ የአረንጓዴ ትራንስፖርት አገልግሎት ላይ ባንኮች፣ የኢንሹራንስ ተቋማት እና የመኪና አስመጪዎች ተሳትፈውበታል ተብሏል ። ራይድ በአሁን ሰአት ከ400 በላይ ለሆኑ ሰዎች የስራ እድል የፈጠረ ሲሆን ከዚህ ውስጥ 85 በመቶ የሚሆኑት ሴቶች ናቸው። (በድሬቲዩብ ሪፖርተር)
Mostrar más ...
6 768
10
የአገር ውስጥ በረራ በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ መሆኑን የኢትዮጵያ አየር መንገድ አስታወቀ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ጣሰው እንደገለጹት እየተጠናቀቀ ባለው በጀት አመት የአገር ውስጥ ተጓጓዦች ቁጥር 3.5 ሚሊየን ይደርሳል፡፡ ይህ መጠን ከ2015 በጀት አመት አንጻር የ34.6 በመቶ ጭማሪ የሚኖረው ነው፡፡ በቀደመው አመት በአገር ውስጥ በረራ የተስተናገዱት ተሳፋሪዎች 2.6 ሚሊየን እንደነበሩ አቶ መስፍን አስታውሰዋል፡፡ አየር መንገዱ እየሰፋ ያለውን የደንበኞች ቁጥር ታሳቢ በማድረግ የቦሌ አለምአቀፍ አየር ማረፊያ አሁን በአመት ማስተናገድ ከሚችለው 25 ሚሊየን መንገደኞች ከ4 እጥፍ በላይ ማስተናገድ የሚችል አየር ማረፊያ እና ማስተናገጃ ለመገንባት በዝግጅት ላይ መሆኑ የተገለጸ ሲሆን፡፡ ሆኖም ይህ ማእከል የአለም አቀፍ እና በተወሰነ መልኩ የጭነት ማስተናገጃ ሆኖ የሚሰናዳ መሆኑን ዋና ስራ አስፈፃሚው ገልጸዋል፡፡ የቦሌ አየር ማረፊያ እያደገ የመጣውን የአገር ውስጥ በረራ በማሰተናገድ ይቀጥላል ያሉት አቶ መስፍን ; የጥገና እና የጭነት ማእከሉም በቦሌ እንደሚቀጥል አስታውቀዋል፡፡ አየር መንገዱ ለአፍሪካ እና መካከለኛው ምስራቅ የአየር መንገዶች የጥገና አገልግሎት እንደሚሰጥ ይታወቃል፡፡ ይህንኑ ስራ ለማስፋት ተጨማሪ የመለዋወጫ ማስቀመጫ እና የጥገና ማእከል እየሰራ ሲሆን እስከመጪው ታህሳስ እንደሚጠናቀቅ ይጠበቃል:: በተመሳሳይ እጅግ ዘመናዊ የጭነት ማእከል የገነባው አየር መንገዱ ዋነኛ የችነት ማእከሉን በቦሌ እንደሚቀጥል ነው ያስታወቀው፡፡ ከአዲስ አበባ ወደ ቢሾፍቱ 40 ኪሎሜትር ርቀት ላይ የሚገነባው አዲስ የአየርመንገድ ከተማ ከቦሌ አለምአቀፍ አየር ማረፊያ ጋር በፈጣን ባቡር እንደሚገናኝ ዋና ስራ አስፈፃሚው ገልፀዋል፡፡(Capital)
Mostrar más ...
6 864
7
አዲስ አበባ‼ ሀሰተኛ የጋብቻ ሰርተፍኬት እና መታወቂያ በመያዝ አገልግሎት ለማግኘት የሞከረው ግለሰብ በቁጥጥር ስር  ዋለ   በየካ ክፍለ ከተማ  በሀሰተኛ  ማስረጃ  አገልግሎት  ለማግኘት የሞከሩ አራት ደንበኞች እና ባለሙያዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን  የአዲስ አበባምዝገባ እና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ አስታውቋል፡፡ በየካ ክ/ከተማ ወረዳ 6 የሲቪል ምዝገባ እና የነዋሪነት አገልግሎት ጽ/ቤት ሁለት ሃሰተኛ ሰነድ ይዘው አገልግሎት ለማግኘት የቀረቡ ተገልጋዮችን ጨምሮ  ሌሎች ሁለት በወንጀል ተግባሩ የተጠረጡ ግለሰቦች በፖሊስ ቁጥጥር ስር ውለው ምርመራ እየተደረገባቸው እንደሚገኝ የአዲስ አበባ ሲቪል ምዝገባ እና የነዋሪነት አግልግሎት ኤጀንሲ  ዋና ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ዮናስ ዓለማየሁ ተናግረዋል  ። አንደኛው ግለሰብ ሃሰተኛ የመታወቂያ እና ያላገባ ህገ ወጥ ማስረጃ በመያዝ ለጽ/ቤቱ ሰራተኛ ጉቦ በመስጠት አገልግሎት ለማግኘት የሞከረ ሲሆን   ከዓመታት በፊት ማስረጃውን በሌላ አገናኝ ደላላ ያገኘው መሆኑን ተረጋግጧል፡፡ በመሆኑም  ደላላው እና  ሁለተኛው ተጠርጣሪ የቂርቆስ ክ/ከተማ ነዋሪነት መልቀቅያን አስመስሎ በማሰራት አገልግሎት ለማግኘት ሙከራ ሲያደርግ ሃሰተኛ ሰነዱን ካዘጋጀው አስመዝጋቢ የቤት ባለቤት ነዋሪ ግለሰብ ጋር በፖሊስ ቁጥጥር ስር ውለዋል። ብስራት ሬዲዮ
Mostrar más ...
7 000
11
የአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ የትንሣኤ በዓል ገበያን ለማረጋጋት ግብረሃይል አቋቁሜ እየሰራሁ ነው አለ የአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ የንግድና ግብይት ዘርፍ ኃላፊ ፍሰሐ ጥበቡ በትንሣኤ በዓል በምርት አቅርቦትና ዋጋ ላይ ህገወጥ የንግድ እንቅስቃሴን ለመቆጣጠር የሚያስችል ግብረሃይል መቋቋሙን አስታውቀዋል። በከተማዋ የሚገኙት 188 የእሁድ ገበያዎች ከመጪው ሰኞ ጀምሮ ሳምንቱን ሙሉ አገልግሎት ይሰጣሉ። በተጨማሪም ከመደበኛው ግብይት ጎን ለጎን በለሚኩራ፣ በኮልፌና አቃቂ የሚገኙት የግብርና ምርቶች ማዕከላት ቅጥር ግቢ ባዛሮች መዘጋጀታቸው ተገልጿል። ከአትክልትና ፍራፍሬ፣ የሰብል፣ የእንስሳት ተዋፅዖ ምርቶች በተጨማሪ በቁም እንስሳት የገበያ ማዕከላት በቂ ፍየል፣ በግና የዳልጋ ከብት የሚቀርብበትን ትስስር ፈጥሬያለሁ ብሏል። በንግድ ዘርፉ ህግና ስርዓት እንዲከበር ከበዓሉ ጋር በተያያዘ ሊስተዋሉ የሚችሉ ህገወጥ የንግድ እንቅስቃሴዎችን ለመቆጣጠር መዘጋጀቱን ሰምተናል። Arada_Fm
Mostrar más ...
7 284
3
ይህንን ያውቃሉ ?? በመካከለኛው ዘመን ጀርመናውያን አንድ አስደናቂ እና አስገራሚ ልምምድ ነበራቸው ይሄም በወቅቱ በጥርስ ህመም የሚሰቃዩ ሰዎች ከጥርስ ህመም ለመፈወስ አህያ ይስሙ ነበር ምክንያቱም በጊዜው አህያን መሳም ለጥርስ ህመም እንደ መድሃኒት ይታመን ስለነበረ ነው እንደዛሬ ለምግብነት ሳትወል። 😇 via - samintunbetarik
7 115
34
#update ሱራፌል ኣሁንም በላውዶን ዩናይትድ ዝርዝር ውስጥ የለም። ባለፈው ሱራፌል የ3 ኣመት ኮንትራት ፈርሞ ሎውዶንን ተቀላቀለ ከተባለ በሁዋላ ተጫዋቹ ግን በክለቡ የሙከራ ግዜ እንጂ የቋሚ ተጫዋች ግዜ እያሳለፈ እንዳልሆነ ነግርያቹ ነበር።ከዛ ወዲም የተቀየረ የለም። በርግጥ መረጃውን ካጋራው በሁዋላ በዊኪፒድያ ላይ የሱራፌል የኣሁን መጫወቻ ክለብ ወደ ላውዶን ዩናይትድ ተጫዋችነት ኣፕዴት ሆኗል።ግን ክለቡ ስኳድ ውስጥ ኣሁንም የለም። ባገኘውት መረጃ ተጫዋቹ የፈረመው የኮንትራት ኣይነት "ስታንዳርድ ፕለየርስ ኣግሪመንት" ሚባል ሲሆን ኣይነቱ ደሞ "ጋራንትድ" ነው።የኣሜሪካ ሁለተኛው ሊግ usl የዝውውር መስኮት ከፌብራሪ ኣጋማሽ እስከ ሜይ ኣጋማሽ ተከፍቶ ሚቆይ ነውና።ኣሁንም ክፍት ነው።ስለዚህ በቀጣይ 20 ምናምን ቀናት ሚፈጠረውን መጠበቅ ነው። ስለጉዳዩ ለፌዴሬሽናችን ሶስት ኣመት ተብሎ ለምን ሙከራ ሆነ ብዬ ባቀረብኩት ጥያቄ "የስራ ወረቀት እስክያገኝ ድረስ ነው" የሚል ምላሽ ኣግኝቻለው። Ermiyas Belayeneh Gebremariam
Mostrar más ...
7 162
2
ኪት ቦይድ ላለፉት 270 ቀናት ከደቡብ አፍሪካዋ ኬፕ ታውን እስከ ግብፅ ካይሮ ሲሮጥ ከርሟል። ነገር ግን በሰሜን ኢትዮጵያ ያለው የፀጥታ ችግር ወደኋላ እያስቀረው እንደሆነ ተናግሯል። ቦይድ ሦስት ጊዜ በሰሜን ኢትዮጵያ በኩል ለማቋረጥ ያደረገው ሙከራ አልተሳካም። አልፎም አንድ ጊዜ የጦር መሣሪያ በያዙ ሰዎች ተይዞ እንደነበር እና ከመታፈን ለጥቂት እንዳመለጠ ተናግሯል። ብሪታኒያዊ-ደቡብ አፍሪካዊው ቦይድ እንዳለው ታጣቂዎች እሱን እና ካሜራ ይዞ የሚከተለውን ማይክል የማፈን ሙከራ እንዳደረጉባቸውም ያስታውሳል፡፡ አሁን ግን ህልሜ ሊከስም ተቃርቧል ብሏል ለቢቢሲ፡፡
6 858
5
#ትዝብት የእግረኛ መንገድ ላይ ቢጫው ለአይነስውራን መስሎኝ? 🤔 Via - Tedy Berhanu
6 973
21
ባይትዳንስ ' ቲክቶክ ' ን ለአሜሪካ ከመሸጥ አሜሪካ ውስጥ ቢዘጋው እንደሚመርጥ ሮይተርስ ለኩባንያው ቅርብ የሆኑ ምንጮችን ዋቢ አድርጎ ዘገበ። ኩባንያው በ' ቲክቶክ ' ጉዳይ እስከመጨረሻው ያሉትን የህግ አማራጮችን ተጠቅሞ እንዳይታገድ ማድረግ ካልቻለ ፤ ለአሜሪካ ከመሸጥ ይልቅ እስከመጨረሻው መዝጋት ይመርጣል ተብሏል። አሁን ' ቲክቶክ ' የሚሰራበት አልጎሪዝም ለኩባንያው እንደ ዋናው ነገር እንደሚቆጠርና በዚህ አልጎሪዝም መተገበሪያውን የመሸጥ እድሉ እጅግ ሲበዛ አነስተኛ እንደሆነ የኩባንያው ምንጮች ገልጸዋል። በዚህም ፤ ለአሜሪካ ገዢ ከመሸጥ አሜሪካ ውስጥ እስከወዲያኛው ድረስ መዝጋትን እንደሚመርጥ ተጠቁሟል። አሜሪካ ' ቲክቶክ ' እንዲሸጥ ከ9 ወር እስከ 1 ዓመት ገደብ አስቀምጣለች ካልሆነ ግን እስከ ወዲያኛው እንዲታገድ ሕግ አጽድቃለች። በርካታ ጉዳዩን የሚከታተሉ የዘርፉ ሰዎች አሁን ባለው የአሜሪካ አቋም 170 ሚሊዮን ተጠቃሚዎች ያሉት ' ቲክቶክ ' እስከ ወዲያኛው ድረስ የመወገዱ ነገር እውን መሆኑ አይቀርም ብለዋል።
Mostrar más ...
7 543
2
ኦሮሚያ ኢንሹራንስ ለ 122 ሺህ አርሶአደሮች 39 ሚሊዮን ብር የሰብል መድህን ካሳ ሊከፍል መሆኑ ተገለፀ በግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢንስቲትዩት ፣ በአለም ምግብ ፕሮግራም እና በፑላ አድቫይዘር ጥምረት ተጀምሯል የተባለውና በሀገሪቱ ትልቁ ነዉ የተባለው የሰብል መድህን ፕሮግራም የክፍ ስርአት መተግበር መጀመሩ ተነግሯል ። በኢትዮጵያ የሰብል መድህን ታሪክ ዉስጥ ትልቁ መሆኑ በተነገረለት ፕሮግራም የኦሮሚያ ኢንሹራንስ ኩባንያ የመድህን ሰጪ እና የካሳ ከፋይ ተቋም በመሆን ለትግበራዉ 39 ሚሊዮን ብር መመደብ ካፒታል ሰምቷል። የመጀመሪያው ምዕራፍ እንደሆነ በተገለጸው ቢዚህ ስርዓት በአማራ ክልል የሚገኙ አነስተኛ አርሶአደሮች ተጠቃሚ መሆናቸው የተነገረ ሲሆን በቀጣይ በተለያዩ ክልሎች ለሚገኙ ለ 7.5 ሚሊዮን አርሶአደሮች ተደራሽ ይደረጋል ተብሏል።(ካፒታል)
8 193
9
ተዋናይ አማኑኤል ሃብታሙ ዛሬ ጠዋት ከቤተሰብ እና ጠበቃው ጋር መገናኘቱ ተዘገበ ተዋናይ አማኑኤል ሃብታሙ "እብደት በሕብረት" የተሰኘ የአንድ ሰው ቴአትሩን ለማሳየት ወደ እስራኤል አገር ሊጓዝ ሲል ከአዲስ አበባ ኤርፖርት በፖሊሶች መያዙ ይታወሳል።በአዲስ አበባ ፖሊስ መምሪያ ውስጥ ታስሮ የሚገኘው ተዋናዩ የቅርብ ወዳጅ የሆነው ያሬድ ሹመቴ እንደገለጸው አማኑኤል ሃብታሙ "እጁ ከተያዘበት ሰዓት አንስቶ የተከሳሽነት ቃል ሳይሰጥ እንዲሁ በእስር ላይ" እንደሚገኝ ቤተሰቦቹን ዋቢ አድርጎ ጽፏል። ይኹን እንጂ የቤተሰብ ጠበቃ የማግኘት መብቱ ተጠብቆለት ከቤተሰብ እና ከጠበቃ ጋር ዛሬ ጠዋት ሊገናኝ መቻሉን እና "በመልካም" ሁኔታ ላይ መኾኑ ተመልካቷል። በሕጉ መሰረት ወደ ቀጣይ ሕጋዊ ሂደቶች ለማምራት እስከ ነገ የሚሆነውን ለማየትም ቤተሰቦቹ እየተጠባበቁ ነው ተብሏል።  እያዩ ፈንገስ የአንድ ሰው ቴያትር 'ቧለቲካ' የተሰኘው ምዕራፉ ለዕይታ ከቀረበ ከእጭር ጊዜ በኋላ ማለትም ከጥር 2 ቀን 2016 ጀምሮ የመንግስት የፀጥታ አካላት ለዓለም ሲኒማ የስራ ሀላፊዎች ባስተላለፉት ትእዛዝ  ለህዝብ እንዳይታይ መከልከሉ አይዘነጋም። Via Addis Maleda
Mostrar más ...
8 388
12
የቀድሞዋ የኢትዮጵያ ጤና ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሰ የሃርቫርድ የሚኒስትሮች አመራር ፕሮግራምን እየመራች ነው። "በርካታ የመሪነት ሚናዎች ውስጥ በማለፌ፣ አዎንታዊ ለውጥ ለማምጣት፤ መሪ ምን ያህል ጠንካራ መሆን እንዳለበት አውቃለሁ። በዓለም ዙሪያ አመራርን ለማሻሻል ማበርከት የምችለው ማንኛውም ነገር በእውነት ያስደስተኛል። – ዶ/ር ሊያ ታደሰ ገብረመድህን
8 151
11
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዛሬ በቤሩት የገጠመው አስገራሚ የገር!🤔 የኢትዮጵያ አየር መንገድ የሚበርባቸውን አየር ማረፊያዎችና የቱሪዝም መዳረሳዎችን ስም በአውሮፕላኖቹ ላይ ይፅፋል። ለምሳሌ ኪሊማንጃሮ፣ ቶሮንቶ፣ ጀኔቫ፣ ዳሎል፣ ሰሜን ተራሮች፣ አድዋ ፤ አልነጃሺ ወዘተ ተጠቃሽ ናቸው (በፎቶው እንደሚታየው)። ዛሬ ታዲያ ወደ ቤሩት የበረረው አየር መንገዳችን የበረራ ቁጥር ET-AXK የውሮፕላን በቢሩት ራፊቅ አል ሃሪሪ አለም አቀፍ አየር ማረፊያ ደረሰ። አውሮፕላኑ ወደ ኋለኛው ክፍሉ ላይ በአነስተኛ ፅሁፍ "Tel Aviv" የሚል ስም የተፃፈበት ነበር። የሰሞኑ የእስራኤል ሃማስ ጦርነት ያመጣው ዳፋ ለኛም ተርፎ ጉዳዩን በበጎ አልተመለከቱትም የቤሩት ባለስልጣናት። የአገሪቱ የሲቪል አቪየሽን ዳሬክቶሬት ጀየራሉ አየር መንገዱ ተመልሶ ከመነሳቱ በፊት ስሙ መፋቅ እንዳለበት ገልፆ ከዚህ በኋላ አየር ማረፊያውን ሲጠቀም ከእስራኤል ጋር የተያያዙ ምልክትና ፅሁፎች መጠቀም እንደሌለበት ተገልፆለታል ተብሏል፡፡ via - Ibcgroup tv.
Mostrar más ...
7 233
23
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 300 ቢሊዮን ብር ብድር እዳ እንዳለበትና የዕዳ ጫናዉን ለማቃለል የባንክ ወለዱ ተፅዕኖ እያሳደረ መሆኑን አስታወቀ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ልማት ድርጅቶች ቋሚ ኮሚቴ የኢትዮጵያ ኤልክትሪክ ኃይል የ9 ወራት የስራ አፈፃጸም ሪፖርት ባዳመጠበት ወቅት የተቋሙ የብድር ጫና በጣም ከፍተኛ መሆኑን ገልጿል። የኢትዮጵያ ኤልክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ በሪፖርታቸው እንደገለፁት ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 300 ቢሊዮን ብር ብድር እንዳለበት እና የዕዳ ጫናውን ለማቃለል የባንክ ወልዱም ጭምር ተፅእኖ እያሳደረ መሆኑ አስረድተዋል፡፡ ቋሚ ኮሚቴው ተቋሙ ካለበት የዕዳ ጫና ለመውጣት የታሪፍ ማሻሻያዎችን የውጭ የሃይል ሽያጭ አቅሞችን በማጠናከር እና የውስጥ ገቢን በመሳደግ ለዕዳ ቅነሳው ትኩረት ሰጥቶ መስራት እንዳለበት ማሳሰብን ካፒታል ሰምቷል። (ካፒታል)
Mostrar más ...
7 398
9
አዳማ ከተማ የሆቴል ወጪውን ሳይሸፍን በመቅረቱ የቡድኑን ምክትል እሰልጣኝ አስያዘ አዳማ ከተማ በድሬድዋ ቆይታው በትሬሀንግል ሆቴል ቡድኑ የተጠቀመውን ሒሳብ በወቅቱ መክፈል ባለመቻሉ የተጫዋቾች ማመላለሺያ ሰርቩሱን እና የቡድኑን ምክትል አሰልጣኝ የሆኑትን አብዲ ቡሊን በማስያዣነት አስይዘው መውጣታቸውን ሸገር አሬና አረጋግጣለች:: አምናም በተመሳሳይ ሁኔታ በባህርዳር እና በድሬዳዋ ዋና አሰልጣኙን ይታገሱ እንዳለን ማስያዙ የሚታወቅ ነዉ::
7 192
21
የሲዳማ ቡናው ግብ ጠባቂ መክብብ ደገፉ የሙከራ እድል ከዱባይ መጥቶለታል። ክለቡ ግን ፍቃድ አልሰጠም። በኢትዮጵያ ፕ/ሊግ ውስጥ ለተለያዩ ክለቦች ሲጫወት ምናውቀውና የወቅቱ የሲዳማ ቡና ቋሚ ግብጠባቂ መክብብ ደገፉ ከዱባዩ ሽባብ አልሂላል የሙከራ እድል መጥቶለታል። የዱባዩ ክለብ በ16/4/24 ለሲዳማ ቡና በፃፈው ደብዳቤ መክብብን ለሙከራ እድል እንዲለቁት ጠይቋል።ተጫዋቹም ይህን ለክለቡ ኣሳውቋል።በዚህም ክለቡ በያዝነው ኤፕሪል ወር በ 29ነኛው ቀን የሙከራው ቀን እሚጀመርበት እንደሆነም ኣያይዞ ጠቅሷል። ሲዳማ ቡናዎች ግን በዚህ ወሳኝ ግዜ ዘንድሮ ድንቅ ብቃት ላይ ሚገኘውን መክብብን መልቀቅ እንደማይፈልጉ ለተጫዋቹ ነግረውታል። በረኛ ላይ ብዙ ችግር ከሚነሳባት ሀገራችን የተገኘውን መክብብን ከዱባዩ ክለብ ከኣንድ ኣመት በላይ ሲከታተሉት የቆዩ ሲሆን ለተጫዋቹ የሙከራ እድል ከሰጡ በሁዋላ በቋሚነት ለማስፈረም ፍላጎት ኣሳይተው ነበር።በጉዳዩ ላይ ለጥቂት ደቂቃዎች በፊት መክብብ ጋ ደውየለት ሚከተለውን ብሎኛል። "ይህ ለኔ ትልቅ እድል ነው።ለተከታታይ ሁለት ኣመታት ከዜጎች ጋ እየተፎካከርኩ ቋሚ ሆኜ ተጫውቻለው።የመጣው እድል ሁሌም ትችት ብቻ ለሚበዛባቸው ለሌሎችም የሀገር ውስጥ በረኞች ትልቅ ተስፋን ሚሰጥ ነው። የሙከራ እድሉን ክለቤ ኣሁን ካለበት ነገር ኣንፃር ኣንለቅህም ብሎኛል።ሂዱቱን እዩጨረሱልኝ ያሉት ጊዮርጊስና ቡናን ዱባይ ወስደው ያጫወቱት ናቸው።እና ኣሁንም ሁሉም ነገሮች ክፍት ናቸው።ሚሆነውን እናያለን" ሲል ነግሮኛል። [ ኤርሚያስ በላይነህ]
Mostrar más ...
6 988
3
የሀገሪቷን የታክስ ኦዲትን ጥራት የሚቆጣጠረው ተቋም ማንነት ግልፅ አይደለም ተባለ የታክስ ኦዲትን ጥራት የሚቆጣጠረው ተቋም ማንነት ግልጽና በታክስ ቢሮ ድረገጽ የሚወጡ ወቅታዊ የግብር መረጃዎች ለማግኘት አዳጋች መሆኑ በዘርፉ የተደረገዉ የፖሊሲ ሰነድ አመላክቷል። በኢትዮጵያ የሚገኘው የአዉሮፓ ቻምበር የሀገሪቷን የግብር አስተዳደርን በማሻሻል ላይ ያተኮረ የፖሊሲ ሰነድ በዛሬው ዕለት ይፋ አድርጓል ። በዚህ የፖሊሲ ሰነድ በተደጋጋሚ የሚደረጉ አድካሚ ኦዲቶችና ወጥ ባልሆነ የግምገማ ቴክኒኮች ምክንያት በአንድ ኦዲት ተቀባይነት ያገኘ ወጪ በሌላ ኦዲት ዉድቅ የሚደረግበት ግልፅ ያልሆነ አሰራር መኖሩን በዝርዝር አስቀምጧል። በግብር ኦዲተሮች ያልተገደበ ስልጣን እንዲሁም ዓለም አቀፍ የግብር ስምምነቶች ካላቸዉ የእዉቀት ዉስንነት ጋር ተዳምሮ የንግድ ስራ ሂደቱን አስቸጋሪ ማድረጉን ይሁ የፖሊሲ ሰነድ ዳሰሳ አመላክቷል ። በገቢዎች ሚኒስትርና እንደ ኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ባሉ የመንግስት መስሪያቤቶች የሚወጡ የግብር መመሪያዎች አለመጣጣም ደግሞ በግብር ከፋዮች ዘንድ ግራ መጋባት እንዲፈጠር ምክንያት መሆኑን ጠቁሟል ።
Mostrar más ...
7 214
9
በ60 አመቷ ለአርጀንቲና የቁንጅና ውድድር አልፋለች በአርጀንቲና መዲና ቦነስ አይረስ በቅርቡ በተካሄደ የቁንጅና ውድድር የ60 አመቷ አሌጃንድራ ማሪሳ ሮድሪጌዝ አሸንፋለች። ጠበቃና ጋዜጠኛዋ ሮድሪጌዝ፥ በግንቦት ወር መጨረሻ በሚካሄደው የአርጀንቲና ቆነጃጅት ውድድር ማለፏን አረጋግጣለች። በ20ዎቹ አልያም በ30ዎቹ ውስጥ የምትገኝ ወጣት እንጂ የ60 አመት አዛውንት የማትመስለው ሮድሪጌዝ ወጣት ቆነጃጂቶችን ማሸነፏ በአርጀንቲና የማህበራዊ ትስስር ገጾች መነጋገሪያ እንድትሆን አድርጓታል። የአለም የቁንጅና ወድድር ከፈረንጆቹ 1958 ጀምሮ ሲካሄድ ተወዳዳሪዎች እድሜያቸው ከ18 እስከ 28 አመት ባለው እንዲሆን ገደብ ተቀምጦ ነበር። ባለፈው አመት ግን የእድሜ ገደቡ መነሳቱ እንደ ሮድሪጌዝ ያሉ ተወዳዳሪዎች እንዲሳተፉ በሩን ከፍቷል። “የ2024 የቦነስ አይረስ ቁንጅና ውድድርን በማሸንፌ በጣም ደስተኛ ነኝ፤ ለሁሉም ሴቶች ውበት እድሜ እንደሌለው እና መሰናክሎችን መበጣጠስ እንደሚቻል ማሳየት እፈልጋለሁ” ብላለች አሸናፊዋ። እድሜዋ አሁንም አከራካሪ ሆኖ የቀጠለው ማሪሳ ሮድሪጌዝ፥ በሳምንት ለሶስት ቀናት ስፖርት መስራቷና በጊዜ የተገደበ አመጋገብ (አንድ ጊዜ ተመግቦ ለረጅም ስአት ከምግብ መራቅ) መከተሏ አቋምና የፊት ገጽታዋ የወጣት እንዲመስል እንዳደረገው ትገልጻለች። “ውበት የሚያበቃበት የጊዜ ገደብ የለውም፤ ወሳኙ ጉዳይ በራስ መተማመን እና ራስን ሆኖ መገኘት ነው” የምትለው የ60 አመቷ ሮድሪጌዝ፥ በውድድሩ ያሳየችው በራስ መተማመን ለውጤት እንዳበቃት ታምናለች። ሮድሪጌዝ ግንቦት 25 2024 በሚደረገው የወይዘሪት አርጀንቲና ውድድር በማሸነፍ ሀገሯን በአለማቀፉ መድረክ ለመወከል ዝግጅት እያደረገች መሆኑን መግለጿንም ኦዲቲ ሴንትራል ነው ያስነበበው ሲል ዐልአይን መረጃ ያመለክታል።
Mostrar más ...
7 082
31
ጎማ የተገጠመለት ተንቀሳቃሽ የአስክሬን ሳጥን ተሽከርካሪ በ29 ሺ የአሜሪካን ዶላር ገደማ መሸጡ ተሰማ ጎማ የተበጀለት የአስክሬን ሳጥን በተሽከርካሪ መልክ መቅረቡን ተከትሎ በ28,750 የአሜሪካን ዶላር የተሸጠ ሲሆን ያልተለመደው የሳጥኑ ቅርፅ መኪና ከፍተኛ መነጋገሪያ ሆኗል። እኤአ በ1965 ለእይታ ይቀርብ ከነበረው የቴሌቭዥን ተከታታይ ዘ ሙንስተር ትዕይንት ላይ ድራግ-ዩ-ላ የአስክሬን ሳጥን ተሽከርካሪ መነሳሻ ሆኖ እንደተሰራም ተሰምቷል።ይህ ያልተለመደ የአስክሬን ሳጥን ተሽከርካሪ የሳጥን-ፍሬም እና ስምንት የፋይበርግላስ ሳጥን በመጠቀም ስራ ላይ ውሏል። የሹፌሩ መቀመጫ የተበጀለት ሲሆን ለተመለከተው በሙሉ እውነተኛ አስክሬን የጫና እንዲመስል ሆኖ ተሰርቷል። የተሟላ ሰፊ የኋላ ጎማዎች በእሽቅድምድም ተንሸራታች ተደርገው የተሰሩ ሲሆን፣ ቀጥ ያሉ የጭስ ማውጫ ቱቦዎች እና የፋኖስ አይነት መልክ ያላቸው መብራት የተሞላው ይህ የሬሳ ሳጥን መኪና ከትክክለኛው ለመንገድ ብቁ ነው ከሚባለው ተሽከርካሪ ይልቅ ለፊልም የሚውል ንድፈ ሀሳብ ይመስላል። ነገር ግን ይህው የአስክሬን ሳጥን ተሽከርካሪ በኒውዮርክ ተመዝግቧል። በምዝገባውም በ1928 ፎርድ እና ትክክለኛ የሰሌዳ ቁጥር ተሰጥቶታል። የሹፌሩ ክፍል በሬሳ ሣጥኑ የኋላ ክፍል ላይ የሚገኝ ሲሆን አነስተኛ መቀመጫ በሰማያዊ ጨርቃ ተሸፍኗል። ቼቭሮሌት ቪ8 ሞተር በሻሲው ማእከሉ ወደ ኋላ ተቀምጧል። ባለአራት በርሜል ካርቡረተር፣ የኤደልብሮክ ማስገቢያ መያዣ እና ሪብብ ቫልቭ አሉት። የማርሽ ሳጥኑን በተመለከተ አውቶማቲክ ሲሆን በወርቅ ቀለም በተቀባ የጽጌረዳ ዘዬዎች ተቀርጿል። በስምኦን ደረጄ
Mostrar más ...
7 493
13
አቶ ብርሃኑተፈተዋል‼ ኦሮሚያ ክልል ሸገር ከተማ ለገጣፎ አቅራቢያ 44 ማዞሪያ ጅዳ ኩራ በተባለ ፖሊስ ጣቢያ ታስረው እንደነበር የተገለፀው አቶ ብርሃኑ የሚባሉት እኝህ አባት ትናንት መፈታታቸው ታውቋል። እሳቸው ላይ ዛቻና ማስፈራሪያን እንዲሁም የድብደባ ተግባር ሲፈፅሙባቸው የነበሩ 7 ወጣቶች በፍ/ቤት ጊዜ ቀጠሮ ተጠይቆባቸው በእስር ላይ እንደሚገኙ ታውቋል። (wasu)
7 868
8
"ሀብታም ቀልብ የለውም"❌ አልፎ ቀልብ ያውም አይጠፋ እንደ ጄጄ ኦካቻ❤️ ለሪል ስቴት በሊዝ የገዛውን መሬት ለሌላ ጥቅም ያዋለው ናይጄሪያዊ ኳስ ተጫዋች።🙏 ጄጄ ኦካቻ፡ ከቀድሞ የናይጄሪያ ቡድን ተጫዋችነቱ በተጨማሪ፡ ብዛት ባላቸው የአውሮፓ ክለቦች ያሳይ በነበረው ድንቅ ብቃት አለም ያወቀውና ተደናቂነትን ያተረፈ ዝነኛ ኳስ ተጫዋች ነበር። ጄጄ ከእግር ኳስ አለም በይፋ ከተሰናበተ በኋላም በሀገሩ ናይጄሪያ ውስጥ በተለያዩ ቢዝነሶች ላይ ተሰማርቶ የቆየ ሲሆን በቅርቡ ባደረገው ነገር መነጋገሪያ ሆኗል። ኦካቻ በሚኖርበት ከተማ ለራሱና ለቤተሰቡ የሚሆን እጅግ ዘመናዊ መኖሪያ ቤት ሰርቶ ካጠናቀቀ በኋላ ለዴልታ ስቴት ማዘጋጃ ቤት ብዛት ያላቸው ቤቶችን ለመስራት ጠይቆ ሰፊ መሬት በሊዝ ይገዛል። በዚህ በወሰደው መሬት ላይም ባጠቃላይ ብዛታቸው መቶ የሚሆኑ የተለያዩ ባለ አንድና ሁለት መኝታ ቤት መኖሪያ ቤቶችንና ኮንደሚኒየሞችን ካሰራ በኋላ... . . . በዴልታ ስቴት ለሚኖሩ ችግረኞችና የጎዳና ተዳዳሪዎች በነጻ ሰጥቶ ሰውን አስገርሟል።✌️ ጄጄ ሙሃመድ ያቪዝ ኦኮቻ ቤቶቹን ለነዚህ ሰወች ካስረከበ በኋላ እንደተናገረው... "እኔ ሚሊየን ዶላር የፈጀ ቪላ ውስጥ እየኖርኩ ለጎዳና ተዳዳሪዎችና ችግረኞች ምንም ማድረግ አለመፈለግ ሀጢያት ነው" ብሏል:: (ናይጄሪያ በአለም የታወቁ ሀብታሞች ያሉባት ሀገር ብትሆንም ለመስጠት በራሱ የሚሰጥ ልብ ይፈልጋል እነሱ ያላደረጉትን ነው ኦካቻ ያሰበው)
Mostrar más ...
7 878
14
ፀድቋል‼️ የአሜሪካው ፕሬዝደንት ጆ ባይደን ቲክቶክ ድርሻው ለአሜሪካ ኩባንያ ተሽጦ ከቻይና ካልተፋታ በመላው አሜሪካ እንዲታገድ የቀረበላቸው ረቂቅ ሕግ ላይ ፊርማቸውን በማኖር ሕግ ሆኖ እንዲወጣ አድርገዋል። የቲክቶክ ዋና ስራ አስፈጻሚ የሆኑት ሹ ዚ ቼው ፥ " የትም አንሄድም። ለመብታችን በፍርድ ቤት እንታገላለን። ሀቁ እና ህገ መንግስቱ ከጎናችን ናቸው፣ እናሸንፋለን ብለን እንጠብቃለን " ሲሉ ተናግረዋል።
7 648
10
ከ34 ቢሊዮን ብር በላይ ካሳ መጠየቁ ተሰማ የፌደራል መንገዶች አስተዳደር፣ በጸጥታ ችግር ሳቢያ በተስተጓጎሉ የመንገዶች ግንባታ ተቋራጮች ከ34 ቢሊዮን ብር በላይ ካሳ እንደጠየቁት ትናንት ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጋር ባደረገው ውይይት ላይ መናገሩን "ኢትዮጵያ ኢንሳይደር" ዘግቧል። አስተዳደሩ እስከ በጀት ዓመቱ አጋማሽ ድረስ 31 የመንገድ ፕሮጀክቶች በጸጥታ ችግር ሙሉ በሙሉ የግንባታ ውላቸው እንደተቋረጠ መግለጡን "ኢትዮጵያ ኢንሳይደር" ዘግቧል። በቀጣዩ በጀት ዓመት አዳዲስ የመንገድ ፕሮጀክቶች እንደማይጀመሩ ተገልጧል።
7 239
4
ኢትዮጵያ የአፍሪካ ዋንጫ ለማዘጋጀት እቅድ እንዳላትና ለእርሱም እየሰራች ነዉ ተባለ ኢትዮጵያ በሚቀጥሉት አመታት የአፍሪካ ዋንጫ ውድድርን እንድታዘጋጅ ለማድረግ እየተሰራ እንደሚገኝ የባህልና ስፖርት ሚኒስትር አቶ ቀጄላ መርዳሳ ተናግረዋል ። የአፍሪካ ዋንጫን እ.ኤ.አ በ 2029 ወይም በ2031 ለማዘጋጀት እየሰራን ነው ያሉት ሚኒስትሩ ለእቅዱ መሳካትም ቢያንስ ስድስት ደረጃቸውን የጠበቁ ስታዲየሞች አስፈላጊ መሆናቸውን ጠቁመዋል። ካፍ ከዚህ በፊት ያልነበሩ አዳዲስ መስፈርቶችን በማስቀመጡ ኢትዮጵያ አንድም ደረጃውን የጠበቀ ስታዲየም እንዳይኖራት አድርጓል ሲሉም አቶ ቀጀላ መርዳሳ አስረድተዋል። ኢትዮጵያ የካፍን ደረጃ የሚመጥኑ ስታዲየሞች የሌላት በመሆኑ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ረዘም ላሉ ጊዜያት ከሀገሩ ዉጪ ለመጫወት ተገድዶ የነበረ መሆኑ ይታወቃል። የዉድድሩ አዘጋጅ ሀገራት ቢያንስ ስድስት ስታዲየሞችን እንዲያዘጋጁ ካፍ ቢያዝም ኢትዮጵያ በዚህ ረገድ ምን ያህል ዝግጁ ናት የሚለዉ ግን አጠያያቂ ነዉ።አዲስ ዋልታ
Mostrar más ...
7 523
4
የኢትዮጵያን ስም ከፍ እያደረገ ያለው አስቻለው በሰፊ ልዩነት በ 48.84 በመምራት 5 ውስጥ ገባ ድምጻዊ አስቻለው ፈጠነ በ"ኮራ አዋርድ"በ47.84 በመቶ በማምጣት ምርጥ አምስትን በአንደኝነት መቀላቀሉን የሽልማት ድርጅቱ ከደቂቃዎች በፊት ይፋ አድርጓል። በ"እናትዋ ጎንደር" እና "ካሲናው ጎጃም" ባህላዊ ጣዕመ ሙዚቃዎችና በቅርቡ በተለቀቀው "አስቻለ" አልበም ተወዳጅነትን ያተረፈው ድምጻዊ አስቻለው ፈጠነ በኮራ አዋርድ "በኢትዮጵያ የባህል ሙዚቃ ዘርፍ" እጩ መሆኑ ይታወሳል። ምርጥ የቡድን ሙዚቀኞች፣ ባህላዊ ሙዚቃ፣ ምርጥ ዲጄ፣ በምርጥ አርቲስት፣ የዓመቱ ምርጥ አልበም፣ ምርጥ የሴት እና የወንድ ዘፋኝን ጨምሮ 20 በሚሆኑ ዘርፎች ሽልማቱን አዘጋጅቷል። አሸናፊው የሚወሰነው እኛ በምንሰጠው ድምጽ ስለሆነ ለድምጻዊ አስቻለው ፈጠነ ድምፃችሁን ለመስጠት የሚከተሉትን ሊንኮች ተጠቀሙ ተብላችኋል:- 1) በመጀመሪያ ሊንክ ይክፈቱት:- 2) ቀጥሎም በሚከፈተው ገፅ ወደ ግርጌ በመውረድ በምስል 1 ላይ ያለውን ማስፈንጠሪያ በመንካት የድምፅ መስጫውን ያግኙ፣ 3) በመቀጠል ከሚመጣው የእጩዎች ዝርዝር ውስጥ በምስል 2 የተመለከተውን ይክፈቱት፣ 4) በመጨረሻም በምስል 3 ላይ የተመለከተው የኢትዮጵያ እጩውን ምስል ያለበትን ያገኛሉ ፤ እሱን በመክፈት ድምፅ መስጠትዎን ያረጋግጡ ።
Mostrar más ...
7 732
15
ፕርሜርሊጉ ከ3 ፈረሶች ግልቢያ ወደ 2 ፈረሶች ግልቢያ የተቀየረ ይመስላል 😁 ሊቨርፑል ትላንት ምሽት ከፉክክሩ የተንሸራተተበትን አስደንጋጭ ሽንፈት በመርሲሳይድ ደርቢ አስተናግዷል። 29 ኛ ሳምንት እንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ የትላንት ተስተካካይ ጨዋታዎች ውጤት '        🇬🇧 ኤቨርተን 2-0 ሊቨርፑል 🇬🇧        ⚽ 27        ⚽  54'                         🇬🇧  ማን ዩናይትድ 4-2 ሼፊልድ 🇬🇧       ⚽ 42'    ⚽ 35'       ⚽ 61'      ⚽ 50'       ⚽ 81'       ⚽  85' የሊጉ ተፎካካሪዎች ሚኬል አርቴታ 🤝 ፔፕ
8 021
5
ዘመን ባንክ ሠራተኞቹን በእውቀትና በክህሎት ለማሻሻል ከሊንክድኢን ለርኒንግ ጋር ስምምነት በመፈፀም የመጀመሪያው የኢትዮጵያ ባንክ ሆነ ዘመን ባንክ በዓለም ላይ ትልቁ የኢንተርኔት የመማሪያ መድረክ ከሆነው ሊንክድኢን ሊርኒንግ ጋር የአጋርነት ስምምነት ተፈራረመ፡፡ የዘመን ባንክ የሰው ሀብት ምክትል ዋና ኦፊሰር አቶ ታከለ ዲበኩሉ ስለ ስምምነቱና ለሠራተኞች ክህሎት መጎልበትና የስራ እድገት የሚያደርገውን አስተዋፅኦ በዚህ መልኩ ገልፀዋል፡፡ “ዘመን ባንክ ለሠራተኞቹ ቀጣይነት ያለው የመማርና የሙያ እድገት ባህልን ለማሳደግ ቁርጠኛ ነው። ከሊንክድኢን ሊርኒንግ ጋር ያደረግነው ስምምነት ይህንን ቁርጠኝነት የሚያጎላ ከመሆኑም በላይ ሠራተኞቻችን በፋይናንስ ዘርፉ የሚጠይቀውን ችሎታ፣ እውቀትና ክህሎት እንዲያሳድጉ የሚረዳ ነው፡፡" የሊንክድኢን ታለንት ሶሉልዩሽን ዋና ኃላፊ ማቲው ግሬይ ስምምነቱን አስመልክተው «ከዘመን ባንክ ጋር ያደረግነው ስምምነት የሰራተኞቹን የክህሎትና የእውቀት ክፍተቶችን ለማሟላት እድሉን የሚሰጠን ከመሆኑም በላይ ሊንክድኢን ሊርኒንግ በአፍሪካ ተመራጭ የክህሎት ልማት መድረክ መሆኑን መቀጠሉን ስለሚያሳይ በዚህ እጅግ ተደስተናል። የዘመን ባንክ የሰው ሃብት ስትራቴጂ በቀጣይ አመታት ይበልጥ እንዲጎለብትና ውጤታማ እንዲሆን አብረን እንሰራለን።" ብለዋል የእነዚህ ኮርሶች ወጪዎች ሙሉ በሙሉ በዘመን ባንክ የተሸፈኑ ሲሆኑ ሠራተኞች በነፃ የሚሰለጥኑ ሲሆን በዚህ ስምምነት ዘመን ባንክ በኢትዮጵያ የባንክ አገልግሎት ዘርፍ የሰራተኞቹን የሥራ እውቀትና ክህሎት እድገት ላይ ያለውን ቁርጠኝነት በድጋሚ አረጋግጧል። ዘመንባንክ
Mostrar más ...
8 463
26
ኢትዮ ቴሌኮም የብሄራዊ ዲጂታል መታወቂያ ምዝገባን አስጀመረ! ኢትዮ ቴሌኮም በሀገር አቀፍ ደረጃ የብሄራዊ ዲጂታል መታወቂያ ምዝገባን በዛሬው ዕለት አስጀመረ፡፡በማስጀመሪያ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ በወር በአማካይ 1 ሚሊየን ዜጎችን በመመዝገብ እስከ 2018 ዓ.ም ለ90 ሚሊየን ዜጎች አገልግሎቱን ለመስጠት መታቀዱ ተመላክቷል፡፡ የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈፃሚ ፍሬህይወት ታምሩ፤ ዲጂታል ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ አስቻይ ከሆኑ ጉዳዮች አንዱ ተዓማኒነት ያለው የማንነት መለያ ዲጂታል መታወቂያ ነው ብለዋል።ዲጂታል መታወቂያ አካታች ዲጂታል ኢኮኖሚን ለመገንባትና ዜጎች በኢኮኖሚው ዕኩል ተጠቃሚ እንዲሆኑ ዕድል ይፈጥራል ነው ያሉት፡፡ የብሔራዊ ዲጅታል መታወቂያ ምዝገባው አዲስ አበባን ጨምሮ በ29 ከተሞች ዛሬ በይፋ የተጀመረ ሲሆን፥ ዜጎች ባሉበት ቦታ ሆነው በቴሌብር ሱፐርአፕ መመዝገብ ይችላሉ መባሉን ፋና ዘግቧል፡፡
Mostrar más ...
8 347
20
ትውልደ ኢትዮጵያውያኑ የተሳተፉበት የነፍስ አድን ጥረት በአሜሪካ 👏 አሜሪካ ውስጥ በድንገት በደረሰ አደጋ ምክንያት ከመንገድ ወጥቶ በእሳት በተያያዘ መኪና ውስጥ የነበረ ግለሰብን ሕይወት ያተረፉ ሁለት ትውልደ ኢትዮጵያውያን እና ሌሎችም አድናቆት እየተቸራቸው ነው። መኪና ላይ በተገጠመ ካሜራ የተቀረጸው ቪዲዮ እንደሚያሳየው ትውልደ ኢትዮጵያዊያኑ እና ሌሎችም በመንገዱ ላይ ሲያልፉ የነበሩ ሰዎች በእሳት ከተያያዘው መኪና አንድን ግለሰብ ለመታደርግ ያደረጉትን አስደናቂ ጥረት አሳይቷል። ይህን ቪዲዮ የቀረጸው እና አሸከርካሪውን ከመኪናው ለማውጣት ከፍተኛ ትግል ሲያደርግ የነበረው ትውልደ ኢትዮጵያዊው ከድር ቶላ ግለሰቡ ከባድ አደጋ ውስጥ እንደነበር ገልጿል። ከድር እንዳለው “ከሚነደው መኪና ውስጥ የነበረውን ሹፌር ልናወጣ ስንታገል ዐይን ዐይናችንን ይመለከት ነበር” ሲል ክስተቱን በተመለከተ የፌስቡክ ገጹ ላይ ጽፏል። በሴንት ፖል ሚኒሶታ ባጋጠመው በዚህ ክስተት ከሚነድ መኪና ውስጥ በሰዎች ጥረት ሕይወቱ የተረፈው ግሰለብ ከባድ ጉዳት አልደረሰበትም ተብሏል። ይህን ትውልደ ኢትዮጵያውያኑ የተሳተፉበት የነፍስ አድን ጥረትን የሚያሳየው ቪዲዮ በተለያዩ የአሜሪካ እና ኣለም አቀፍ የቴሌቪዢን ጣቢያዎች በስፋት እየታየ ነው።(BBC)
Mostrar más ...
8 299
9
ሐዋሳ‼️ ሀዋሳ ከተማ ከምሽት 3:00 በኋላ ባለ ሦሰት እግር ተሽከርካሪ (ባጃጅ) እና የሁለት እግር ሞተር ሳይክል ማሽከርከር ተከለከለ። ሰሞኑን በሀዋሳ ከመዝናኛ መልስ እየደረሰ ያለውን የመንገድ ላይ የትራፊክ አደጋን ለመከላከል ሲባል ከምሽቱ 3:00 በኃላ ባለሦሰት እግር ተሽከርካሪ (ባጃጅ) እና ባለ ሁለት እግር ሞተር ሳይክል ማሽከርከር የተከለከለ መሆኑን የሀዋሳ ከተማ ትራፊክ ፖሊስ አስተባባሪው ኢንስፔክተር ተስፋዬ ደምሴ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ላይ አሳውቀዋል።
8 343
7
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ቀብሪደሃር በሣምንት 2 ቀን ለመብረር ዝግጅቱን አጠናቀቀ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከሚያዝያ 25 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ ወደ ሶማሌ ክልል ቀብሪደሃር ከተማ በሣምንት ሁለት ቀን የበረራ አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችለውን ዝግጅት ማጠናቀቁን አስታወቀ፡፡ የሀገር ውስጥ የበረራ አድማሱን እያስፋፋ መሆኑን ያስታወቀው የኢትዮጵያ አየር መንገድ÷ በሶማሌ ክልል ብቻ ቀብሪደሃር ከጂግጂጋ እና ጎዴ ቀጥሎ ሦስትኛ መዳረሻው መሆኗን ገልጿል፡፡
8 135
7
#ይቅርታ🙏 ምክትል ሳጂን ታመነ ዱባለ "ያደኩበት ቤተክርስትያን ተገንብቶ በማለቁ የተሰማኝ ደስታን ለመግለፅ ሀላፊዎችን አስፈቅጄ ነው ጥይት የተኮስኩት በዚህም ያስከፋዋችሁ ካለ ይቅርታ አድርጉልኝ" ብሏል።
8 103
8
ታዋቂው የቱርክ ተዋናይ ትምህርት ቤቱን ወደፍርስራሽነት ለውጦታል ቻላር አርቱግሩል የተባለው ተዋናይ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤቱን ገዝቶ ያወደመው ይገርፉኝ የነበሩ መምህራንን ለመበቀል ነው ብሏል።🤯 አል ዐይን
8 350
62
በኢትዮጵያ የሚገኙ ባንኮች ከ 1 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ አድርገዉበታል የተባለውና ለ ዲጅታል መታወቂያ የሚያገለግለዉ የግዢ ዉል ስምምነት ተደርጓል። በኢትዮጵያ ባንኮች ማህበር አማካኝነት ተደርጓል በተባለው በዚህ የግዢ ዉል 6 ሺህ የዲጅታል መታወቂያ ቁሳቁሶችን ለመግዛት እንደሆነ ተጠቁሟል ። ላሚኖ ኢንጂነሪንግ የተሰኘዉ ድርጅት ለግዢ የወጣዉን ጨረታ በማሸነፍ ተደርጎል በተባለው ዉል ቁሳቁሶችን በወቅቱ የማቅረብ ኃላፊነት አለበት ተብሏል። 32 ባንኮች በጋራ በመሆን ከ አንድ ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ በማድረግ 6ሺህ የምዝገባ ቁሳቁሶች የግዢ ዉል ስምምነት ነዉ ማድረጋቸው የተገለፀው ።(capital)
7 772
7
የናይጄሪያ ትምህርት ቤት በተማሪዎች ብሽሽቅ እና የጉልበተኞች ጥቃት የተነሳ መዘጋቱ ተሰማ🤔 የናይጄሪያ ባለስልጣናት በዋና ከተማይቱ አቡጃ የሚገኘውን በአንዳንድ ተማሪዎቹ ላይ በተፈፀመው የጉልበተኝነት ድርጊት ከፍተኛ ደረጃ ያለው ትምህርት ቤት እንዲዘጋ መደረጉን የሀገር ውስጥ መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል።በሊድ ብሪቲሽ ኢንተርናሽናል ትምህርት ቤት ተማሪዎች እኩዮቻቸውን ሲያጠቁ የሚያሳዩ በርካታ ቪዲዮዎች በማህበራዊ ሚዲያ ተሰራጭተዋል። ቪዲዮዎቹ መጋራታቸዉን ተከትሎ የሰላ ትችት የፈጠረ ሲሆን የተናደዱ ወላጆች ትምህርት ቤቱን ማክሰኞ እለት ሲወረሩ ታይተዋል።የትምህርት ቤቱ ባለስልጣናት ጉዳዩን ለመመርመር ለማስቻል ለሶስት ቀን መዘጋቱን አስታዉቀዋል፡፡የትምህርት ከፍተኛ ባለስልጣን የሆኑት ካቢሩ ሙሳ ለፓንች የዜና ድረ-ገጽ እንደተናገሩት የሀገሪቱ የሴቶች ጉዳይ ሚኒስትር ኡጁ ኬኔዲ-ኦሀኔዬ ትምህርት ቤቱ እንዲዘጋ ትዕዛዝ ሰጥተዋል። ትምህርት ቤቱ ባወጣዉ መግለጫ ላይ የጉልበተኝነት ድርጊት "በጥልቅ አሳስቦኛል" በማለት በጉዳዩ ላይ ጥልቅ ምርመራ ለማድረግ ቃል ገብቷል።እ.ኤ.አ በ2007 የተቋቋመው ትምህርት ቤት ከናይጄሪያ የትምህርት ስርዓት ጋር የተዋሃደ የብሪቲሽ ስርዓተ ትምህርት ይሰጣል።በናይጄሪያ ውስጥ በጣም ውድ ከሚባሉት ትምህርት ቤቶች አንዱ እንደሆነ የሀገር ውስጥ መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል።
Mostrar más ...
7 755
5
በሀሰተኛ የክፍያ ሰነድ 6 ሚሊየን 50 ሺህ ዶላር ዝውውር ወንጀል ተጠርጥረው ለእስር የተዳረጉት ቀሲስ በላይ ለሁለተኛ ጊዜ ፍርድ ቤት ቀረቡ መርማሪ ፖሊስ በተሰጠው የ7 ቀን ጊዜ ውስጥ የምስክሮችን ቃል መቀበሉን፣ በተጠርጣሪዎች እጅ ላይ የተገኘ ኤሌክትሮኒክስ ምርመራ እንዲደረግ ለሚመለከተው ተቋም መጠየቁን፣ የቴክኒክ ምርመራ እንዲሰጠው በደብዳቤ መጠየቁን አስታውቋል። በተጨማሪም በቀሲስ በላይ ሁለት መኖሪያ ቤቶች ላይ ብርበራ ማድረጉንና በብርበራ የተገኘ የጦር መሳሪያ ህጋዊነት የማረጋገጥ ስራ እየሰራ መሆኑን ገልጿል፤ ተጨማሪ ጊዜ እንደሚያስፈልገው ገልጾ መርማሪ ፖሊስ የ14 ቀን ጊዜ ቀጠሮ ጠይቋል። ቀሲስ በላይ መኮንንን ጨምሮ ሌሎቹም ተጠርጣሪዎች በ6 ጠበቆች ተወክለው ችሎት የቀረቡ ሲሆን ደንበኞቻቸውን ተጨማሪ በእስር ለማቆየት የሚያስችል አይደለም በማለት ተከራክረዋል። የግራ ቀኝ ክርክሩን የተመለከተው ጊዜ ቀጠሮ ችሎቱ ተጠርጣሪው ያቀረቡትን የዋስትና ጥያቄ ለጊዜው በማለፍ ለፖሊስ የ8 ቀን የምርመራ ማጣሪያ ጊዜ ፈቅዷል።
Mostrar más ...
8 021
5
ስለ ጊዜ..... ኒዉዬርክ ከካሊፎርኒያ በ 3 ሰዓት ትቀድማለች ነገር ግን ይህ ካሊፎርኒያን ቀርፋፋ አያደርጋትም ምክንያቱም የራሷ ጊዜ አላትና ፡፡ አንዳንድ ሰዉ በ22 አመቱ ይመረቃል ነገር ግን ጥሩ ስራ ለመያዝ 5 አመት ይፈጅበታል፡፡ አንዳንዱ በ25 አመቱ የድርጅት ሃላፊ ሆኖ በ5ዐ አመቱ ሲሞት ሌላዉ በ50 ዓመቱ ሃላፊ ሆኖ እስከ 9ዐ ዓመት ይኖራል፡፡ ኦባማ በ55 ዓመቱ ኘሬዝዳንትነቱን ጨረሰ ነገር ግን ትራምፕ በ7ዐ ዓመቱ ኘሬዝዳንትነቱን ጀመረ! ይሄ ትራምፕን ኀላ ቀር አያደርገዉም፡፡ ጊዜ በሕይወታችን ወሳኝ ነገር ነዉ ፡፡ ፈጣሪ በጊዜዉ ሁሉን ነገር ዉብ ያደርጋል ስለዚህ.... ከሁሉ በኋላ የቀረን ወይም ወደፊት የቀደምን አይምሰለን ሁሉም ሰዉ የራሱ የሆነ የኑሮ ሩጫና የተፈጠረበት አላማ አለዉ! ሁላችንም የራሳችን የሆነ የጊዜ ክልል አለን! Dr. Mihret Debebe
8 125
101
በኢትዮጵያ የሚገኝ አንድ ቄራ ለመጀመሪያ ጊዜ የግመል ስጋ ወደ ሣውዲ አረቢያ መላክ ጀምሪያለሁ አለ። ቄራው በወር በአማካይ እስከ ስልሣ ሺህ ኪሎ ግራም የግመል ስጋ ሣውዲ አረቢያ እየላከ እንደሚገኝ ሠምተናል። shegerfm
8 073
15
በአዲስ አበባ የመኖሪያ ቤት ተደርምሶ በደረሰ አደጋ የ7 ሰዎች ሕይወት አለፈ በአዲስ አበባ ከተማ አዲስ ክፍለ ከተማ ወረዳ 12 ልዩ ስሙ ጠሮ መስጊድ ተብሎ በሚጠራ አካባቢ የመኖሪያ ቤት ተደርምሶ በደረሰ አደጋ የ7 ሰዎች ሕይወት አለፈ፡፡ የክፍለ ከተማው ሥራ አስፈጻሚ ወ/ሮ አይዳ አወል እንዳሉት÷አደጋው የግለሰብ መኖሪያ ቤት ተደርምሶ በጀርባ በሚገኝ ሌላ መኖሪያ ቤት ላይ በማረፉ ነው የተከሰተው፡፡ ሌሊት 11 ሰዓት ላይ በደረሰው አደጋም እስካሁን የሰባት ሰዎች ሕይወት ማለፉን ነው ሥራ አስፈጻሚዋ የተናገሩት ሲል ፋና ነው የዘገበው።
7 874
21
አርቲስት አማኑኤል ሀብታሙም በቁጥጥር ስር ውሏል😳 አርቲስት አማኑኤል ሀብታሙ ትናንት ሚያዚያ 15ቀን 2016ዓ.ም ዓመሻሽ ወደ እስራኤል ለመጓዝ ኤርፖርት በተገኘበት መያዙ ተሰምቷል። የእስራኤል ጉዞው "ዕብደት በሕብረት" የተሰኘውን አዲሱን ትያትር ለማሳየት እንደነበር ታውቋል። ከኤርፖርት ተይዞ ወደ አዲስ አበባ ፖሊስ መወሰዱን ምንጮች አረጋግጠዋል።
7 859
22
ከሰሞኑ በቤተክርስቲያን ዉስጥ ሲተኩስ የታየዉን የፌዴራል ፖሊስ አባል ተከትሎ ኮሚሽኑ ከመተዳደሪያ ህግና አሠራር ውጭ ነዉ ሲል ኮነነ 👉🏼 የፖሊስ አባሉም ይህንን ተግባር እንደፈፀመ ወዲያውኑ በቁጥጥር ሥር ዉሏል ተብሏል የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ በማህበራዊ የትስስር ገጹ ላይ ካሰራጨዉ መግለጫ ዳጉ ጆርናል እንደተመለከተው ፖሊስ ከየትኛውም ሃይማኖት፣ ብሄር እና ፖለቲካ  ወገንተኝነት የፀዳ እና ብዛህነትን እሴቱ ያደረገ ሕዝባዊ ተቋም መሆኑን ገልጿል። የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ የሃይማኖቶች ብዛህነትን የሚያከብርና የሚያስከብር በእኩልነት ለሁሉም ሙያዊ አገልግሎት የእየሰጠ ያለ ተቋም ሆኖ ሳለ ከኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርስቲ አዲስ የፖሊስ አባላትን ለመመልመል ወደ ደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጎፋ ዞን ገዜ ጎፋ ወረዳ የተላከ የፖሊስ አባል ምክትል ሳጂን ታመነ ዱባለ ጥር 5 ቀን 2016 ዓ.ም ኬቾ ወዜ ቅዱስ ባለወልድ ቤተክርስቲያን  በመገኘት የደንብ ልብሱን እንደለበሰ ሃይማኖታዊ መዝሙር በመዘመር እና በሕዝብ ፊት ጥይት እየተኮሰ በማህበራዊ ሚዲያ ሰሞኑን የሚሰራጨው ቪዲዮ ከተቋሙ መተዳደሪያ ህግና አሠራር ውጭ እንደሆነ መግለጫው ወቅሷል። አባሉም ይህንን ተግባር እንደፈፀመ ወዲያውኑ የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ   በቁጥጥር ሥር አውሎት የፈፀመው ድርጊት በተቋሙ ሕገ ደንብ መሠረት በሕግ አግባብ እያጣራ እንደሚገኝ መግለጫው አመላክቷል። ፖሊስ የሁሉም አገልጋይ ሆኖ ሳላ አባሉ እምነቱን በግል መከተል እየቻለ ነገር ግን መንግስት ፀጥታ እንዲያስከብር ያስታጠቀውን የጦር መሣሪያ ከፍተኛ ሕዝብ በተሰበሰበበት ቦታ ፍፁም የፖሊስን ዲሲፕሊን በጣሰ መልኩ የፈፀመው ተግባር በሕግ የሚያስጠይቅ ስለሆነ ተቋሙ ሕግ ፊት እንደሚያቀርበው በመግለጫው መጥቀሱን ዳጉ ጆርናል ተመልክቷል። ዳጉ_ጆርናል
Mostrar más ...
8 130
9
አርሰናል ቼልሲን እንደጉድ ሲሸምነው አምሽቷል! የአርቴታ ወጣት ሰራዊት ለሰማያዊዎቹ ርህራሄ ሳያስመለክቱ ደቁሰዋቸዋል! መድፈኞቹ ወደ ዋንጫው መመልከቱን አላቆሙም! 5-0 ጣፍጭ ድል አስመስግበዋል አርሰናል የሊጉን መሪነት አጠናክሩዋል
8 758
22
የሀገሪቱ የገበያ ስርአት ያለተወዳዳሪ ተዘግቶ የቆየ ነው አሉ የምጣኔ ሀብት ባለሙያዎች ለተከታታይ አመታት የሀገሪቱ ገበያ ለውጭ ባለሀብቶች ተዘግቶ የቆየና ተወዳዳሪ አልባ በመሆኑ ለዋጋ ንረት ምክንያት ሆኖ ቆይቷል ያሉት ከአራዳ ጋር ቆይታ ያደረጉ የምኔ ሀብት ባለሙያዎች ናቸው፡፡ የምጣኔ ሀብት ባለሙያው አቶ ዳዊት ስለሺ የሀገሪቱ የህዝብ ቁጥርና የገበያ አቅርቦቱ የሚመጣጠን አይደለም ያሉ ሲሆን ለዚህ ምክንያቱ በገበያ ያሉ የሀገር ውስጥ ባለሀብቶች አቅም የጎለበተ ባለመሆኑ ነው ተብሏል፡፡ የኢንቨስትመንት ኮሚሽን ለውጭ ባለሀብቶች ክፍት ያደረጋቸው አራቱ የንግድ ዘርፎች የሀገሪቱን የመሸጥና የመለወጥ አቅም ከፍ ያደርገዋለል ያሉት ደግሞ ሌላኛው የምጣኔ ሀብት ባለሙያ አቶ መቆያ ከበደ ናቸው፡፡ የንገድ ስርአትን ዝግ ማድረግ በአለም ገበያ ሆነ በሀገር ውስጥ ተወዳዳሪ እንዳንሆን የሚያደርግ አሰራር መሆኑን ባለሙያዎቹ ለጣቢያችን ገልጸዋል፡፡ በተጨማሪም ጥራታቸውን የጠበቁ ምርቶችን በተሻለ ዋጋና አማራጭ ለማግኘትም ሁሉን አካታች የሆነ የገበያ ስርአት ሊኖር እደሚገባ ጠቁመዋል፡፡ የኢንቨስትመንት ኮሚሽን ከሰሞኑ ከነዳጅና ከማዳበሪያ ገቢ ንግድ በስተቀር የውጭ ባለሀብቶች በወጪ፣በገቢ ፣በጅምላና በችርቻሮ የንግድ ዘርፎች እንዲሳተፉ ፖሊሲየን አሻሽያለሁ ማለቱን መዘገባችን ይታወሳል፡፡ አራዳ ኤፍኤም
Mostrar más ...
8 955
6
በሰሜን ሸዋ ዞን ደብረ ሊባኖስ ወረዳ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የ4 ሰዎች ሕይወት አለፈ። አደጋው ከአዲስ አበባ ወደ ደብረ ሊባኖስ ገዳም እየተጓዘ የነበረ የቤት አውቶሞቢል ከኮሶበር ወደ አዲስ አበባ ሲጓዝ ከነበር የህዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪ ጋር ቀሲም በተባለ ልዩ ቦታ በመጋጨቱ የደረሰ ነው። በአደጋው የአራት ሰዎች ሕይወት ወዲያውኑ ሲያልፈ በ14 ሰዎች ላይ ከባድ የአካል ጉዳት፤ በስምንት ሰዎች ላይ ደግሞ ቀላል ጉዳት ደርሶባቸዋል። የደብረ ሊባኖስ ወረዳ ትራፊክ ደህንነት አስተባባሪ ረዳት ኢንስፔክተር ኃይለማርያም ደባሌ የአደጋው መንስኤ በፍጥነት ማሽከርከር እና ቅድሚያ አለመሰጠት መሆኑን መናገራቸዉን ከወረደዉ ኮሙኒኬሽን የተገኘው መረጃ ያመላክታል፡፡
8 543
3
በጀልባ መገልበጥ አደጋ የ16 ኢትዮጵያውያን ሕይወት አለፈ በጀልባ መገልበጥ አደጋ የ16 ኢትዮጵያውያን ሕይወት ሲያልፍ በጀልባዋ የነበሩ ሌሎች 28 ዜጎችን እስካሁን ማግኘት አለመቻሉ ተገለጸ፡፡ ትላንት ምሽቱን ከየመን የባህር ዳርቻ ልዩ ስሙ አራ ከሚባል ስፍራ 77 ኢትዮጵያውያን ሕገ ወጥ ፍልሰተኞችን አሳፍራ ወደ ጅቡቲ ስትጓዝ የነበረች ጀልባ ጎዶሪያ በሚባል አካባቢ በደረሰባት የመገልበጥ አደጋ እስካሁን የ5 ሕፃናት እና ሴቶችን ሕይወት ጨምሮ 16 ዜጎቻችን ሕይወታቸውን አጥተዋል። ምንጭ:- FBC
8 393
4
የላሊበላ ከተማ በሰላም ማጣት ምክንያት ከጎብኚዎች ያገኝ የነበረውን 78 ሚሊየን ብር አጥቻለሁ አለ በሰሜን ወሎ የቅርስ ጥበቃና ቱሪዝም ልማት ቡድን መሪ ጥላሁን አባተ እንደተናገሩት በ6 ወሩ 3 ሺህ 834 የውጭ ሀገር ጎብኚዎች ወደ ስፍራው ያቀናሉ ተብሎ ቢጠበቅም መምጣት የቻሉት ግን 1 ሺህ 486 ብቻ ናቸው ብለዋል። በእቅዳችን መሰረት ወደ 60ሺ ጎብኚዎች ይመጣሉ ተብሎ ታቅዶ እንደነበር እና 90ሚሊየን ገቢ ለማስገባት ቢታቀድም በሰላም እጦት ማሳካት እንዳልቻለ ተናግረዋል። በሌላ በኩል 1 ሚሊየን የሚጠጉ የሃገር ውስጥ ጎብኚዎችን ለማስተናገድ ታቅዶ 512 ሺህ ጎብኚዎችን ማስተናገድ ተችሏል ብለዋል። በሰላም እጦቱ ምክንያት ቤተ-ክርስቲያን ሆቴሎች አስጎብኚዎች፣ ትራንስፖርት ሰጪዎች፣ በጎብኚዎች ቁጥር ማነስ የሚያገኙት ገቢ መቀነሱም ተጠቁሟል። በዚህም የላሊበላ ከተማ በሰላም እጦት ምክንያት ከጎብኚዎች ያገኝ የነበረውን ገቢ በተጠቀሰው ልክ ማጣቱ ተሰምቷል። ኢትዮ ኤፍ ኤም
Mostrar más ...
7 842
2
የባቡር ሀዲዲ ስርቆት… የባቡር ሐዲድ ብረት ስርቆት የፈፀሙ ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራ እያጣራ መሆኑን የመልካ ጀብዱ ፖሊስ ጣቢያ ገለፀ፡፡ የስርቆት ድርጊቱ የተፈፀመው በቀድሞ ከድሬዳዋ ወደ አዲስ አበባ በተዘረጋው የባቡር ሀዲድ ብረት ላይ ሲሆን ከጉዳዩ ጋር በተያያዘ ሁለት ተጠርጣሪዎች በፖሊስ ቁጥጥር ስር ያዋለ ሲሆን ለጊዜው ያልተያዙ ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር ለማዋል ምርመራው ተጠናክሮ መቀጠሉን ፖሊስ ጨምሮ ገልጿል ። በሀሰሊሶ ክላስተር በገደንሳር ቀበሌ ልዩ ቦታው ቦሬ ተብሎ ከሚጠራው አካባቢ ሚያዚያ 9 ቀን 2016 ዓ.ም ከሌሊቱ አስር ሰአት ገደማ የቀድሞውን ከአዲስ አበባ ወደ ድሬዳዋ የተዘረጋውን የባቡር ሀዲድ ብረት ፈትተው 47 ፍሬ በአይሱዙ መኪና በማጫን ሰርቀው ለመሰወር ሲሞክሩ የአካባቢው ሚሊሻ ባደረገው ብርቱ ጥረት የተሰረቀውን ብረት ከአንድ ተጠርጣሪ ግለሰብ ጋር በቁጥጥር ስር በማዋል ለመልካ ጀብዱ ፖሊስ ጣቢያ ማስረከባቸውን የመልካ ጅብዱ ፖሊስ ጣቢያ አዛዥ ም/ኮ/ር ሻንበል ተካኝ ተናግረዋል ። ፖሊስ በወቅቱ ባደረገው ማጣራት እና በህብረተሰቡ ጥቆማ ተሰርቆ በሌላ አካባቢ ተሸሽጎ የነበረ ከሶስት መቶ ፍሬ በላይ የሀዲድ ብረት ከቦታው ላይ ተነቅሎ ለመጓጓዝ የተዘጋጀውን በቁጥጥር ስር አውሎ ተጨማሪ ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር ለማዋል ባደረገው ጥረት ሁለተኛውን ተጠርጣሪ በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራውን በተጠናከረ መልኩ መቀጠሉን የመልካ ጅብዱ ፖሊስ ጣቢያ አዛዥ ም/ኮ/ር ሻንበል ተካኝ ጨምረው ተናግረዋል ። (ድሬ ዳዋ ፖሊስ)
Mostrar más ...
6 845
3
የሪያል ማድሪዱ ኮኮብ ጁድ ቤሊንገሃም የላውረንስ የ2024 ምርጥ ስፖርተኛ ተባለ በየዓመቱ የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ ስፖርተኞን በመምረጥ እውቅና የሚሰጠው የላውረንስ ስፖርት ለበጎ ተቋም ትላንት በስፔን ማድሪድ በ8 ዘርፎች የዘንድሮውን አሸናፊ ስፖርተኞችን በመምረጥ እውቅና ሰጥቷል፡፡ ላሊጋውን በአስር ነጥብ ልዩነት እያመራ የሚገኘው ሪያል ማድሪድ በአውሮፓ ሻምፒንስ ሊግ ለግማሽ ፍፃሜ እንዲደርስ ገንቢ ሚና የተጫወተው ጁድ ቤሊንገሃም በዓመቱ ባሳየው ምርጥ ብቃት “Laureus World Breakthrough of the Year Award” ሽልማትን አሸንፏል፡፡
7 702
4
በኢትዮጵያ በግማሽ አመት ብቻ 1ሺህ 358 ሰዎች በትራፊክ አደጋ ህይወታቸው እንዳለፈ ተነገረ። በ2016 አመት በባለፊት ስድስት ወራቶች በደረሱ የትራፊክ አደጋዎች ምክንያት 1ሺህ 358 ዜጎች ለሞት መዳረጋቸው ተነግሯል። በደረሱ አደጋዎች ምክንያትም ከ 1 ቢሊዮን ብር በላይ የሚሆን ንብረት እንደወደመ ነው የተገለጸው። ባለፉት 6 ወራት ከ2.5 ሚሊዮን በላይ ህግ የተላለፉ ተሽከርካሪዎችን በመቅጣት ከ 1.8 ቢሊዮን ብር በላይ ለመንግስት ገቢ መደረጉም ተጠቁሟል፡፡ የመንገድ ደህንነትና መድህን ፍንድ አገልግሎት ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ጀማል አባሶ የመንገድ ትራፊክ አደጋን ለመከላከልና ሕግ ተላልፈው የሚገኙ አሽከርካሪዎች ላይ ተገቢውን የቅጣት ዕርምት ለመውስድ ቴክኖሎጅን በመጠቀም ላይ እንደሚገኝ ገልጸዋል። ሃላፊው አክለው እንደተናገሩት ከ 1ኛ እስከ 8ኛ ክፍል ለሚገኙ ተማሪዎች የመንገድ ደኀንነት ትምህርቶች በካሪኩለም ውስጥ ለማካተት እየተሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል። የአሽከርካሪዎች ማሰልጠኛ እና የተሽከርካሪዎች ቴክኒክ ብቃት ማረጋገጫ ተቋማት ያልተገቡ ማስረጃዎችን እንደሚሰጡ የገለፁት  ሥራ አስፈጻሚው ተገቢውን ክትትል በማድረግ ላይ እንገኛለ ብለዋል። ለአደጋ አጋልጭ የሆኑ መንገዶች ተለይተው የማሻሻያ ሥራዎች መከናወናቸውና የሞተር አልባ ትራንስፖርትንም ለማስፋፋት በ13 ከተሞች የመንገድና መሰል መሰረተ ልማቶችን የማልማት ሥራዎች እየተከናወኑ እንደሚገኙ ገልጸዋል። ተደጋጋሚ ጥፋት የሚያጠፉ አሽከርካሪዎች ላይ መንጃ ፈቃድ እስከመንጠቅ የሚያደርስ እርምጃ እየተወሰደ እንደሚገኝ የገለጹት ሃላፊው አገልግሎቱ በአዲስ አበባና ሸገር ከተሞች ተግባራዊ በመደረግ ላይ እንደሚገኝ ተናግረዋል። Ethiofm
Mostrar más ...
7 377
3
ታይዋን በድጋሚ በተከታታይ ከባድ ርዕደ መሬት ተመታች ታይዋን 17 ሰዎችን ለህልፈት ከዳረገው ርዕደ መሬት አደጋ ከሦስት ሳምንታት በኋላ ከትናንት ምሽት እስከ ዛሬ ጠዋት ድረስ በድጋሚ ለሰዓታት ከባድ በሆነ ተከታታይ ርዕደ መሬት መመታቷ ተገልጿል፡፡ በመጀመሪያ በሬክተር ስኬል 5 ነጥብ 5 ሆኖ የተመዘገበ ሰኞ ምሽት በደሴቲቱ ምስራቃዊ ሁዋሊን ግዛት የደረሰውን ርዕደ መሬት ተከትሎ አነስተኛ መንቀጥቀጥ መከሰቱ ተመላክቷል፡፡ ይህንንም ተከትሎ ከተወሰኑ ሰዓታት በኋላ በሬክተር ስኬል 6 ነጥብ 0 እንዲሁም 6 ነጥብ 3 ሆነው የተመዘገቡ የርዕደ መሬት አደጋዎች መከሰታቸውን የደሴቲቱ የአየር ሁኔታ አስተዳደር የርዕደ መሬት ማዕከል አስታውቋል፡፡ በፈረንጆቹ ሚያዝያ 3 በደረሰው ርዕደ መሬት ከባድ ጉዳት የደረሰባቸው ሁለት ሕንፃዎችም ከዛሬ ጠዋቱ ክሰተት በኋላ በከፊል መውደቃቸውን የሁዋሊን ግዛት ባለስልጣናት ተናግረዋል። የማዕከላዊ የአየር ንብረት አስተዳደር የርዕደ መሬት ማዕከል በአደጋው የተጎዱ ሰዎች እንደሌሉና በሁዋሊን ትምህርት ቤቶች እንዲዘጉ ትዕዛዝ እንደተላለፈ ማስታወቁን ቪኦኤ ዘግቧል፡፡ ቀደም ሲል የደረሰው የርዕደ መሬት አደጋ በታይዋን ከ25 ዓመታት በፊት በሬክተር ስኬል 7 ነጥብ 7 ሆኖ ከተመዘገበውና 2 ሺህ 400 ሰዎችን ለህልፈት በመዳረግ በሺዎች የሚቆጠሩ ህንፃዎችን ካወደመው ርዕደ መሬት በኋላ ከባዱ መሆኑ ተጠቁሟል፡፡
Mostrar más ...
7 874
2
የኢትዮጵያ እና የኬኒያ የአገር ውስጥ አጠቃላይ ምርት (GDP) ንጽጽር በዓለም ባንክ እና በአይ ኤም ኤፍ ዕይታ‼️ ኢፕድ
7 948
23
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን የቀሲስ በላይ ጉዳይ ከቤተክርስቲያኗ ጋር የሚያገናኘው ነገር እንደሌለ አስታወቀች‼️ ከሰሞኑ ቀሲስ በላይ መኮንን በሀተኛ ሰነድ 6 ሚሊዮን 50 ሺህ የአሜሪካን ዶላር ገንዘብ ለማዘዋወር ሞክረዋል በሚል ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር የዋሉበት ጉዳይ ከቤተክርትያኗ ጋር የሚያገናኘው ምንም ነገር እንደሌለ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ማስታወቋን ዶቸቬለ ዘግቧል። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ግለሰቡ በቤተክርስቲያኗ በከፍተኛ ኃላፊነት የሚያገለግሉ ቢሆንም፤ ተጭበርብሯል ከተባለው ሰነድ ጋር ግን ቤተክርስቲያኗን የሚያገናኛት ምንም ነገር እንደሌለ አስታውቃለች፡፡ መምህር ዶ/ር አካለወልድ ተሰማ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን የመንበረ ፓትሪያርክ ህዝብ ግንኙነት የሚዲያ ክፍል ዋና ኃላፊ “ሊቀ አዕላፍ በላይ መኮንን በህግ ጥላ ስር በዋሉበት ጉዳይ ላይ ቤተክርስቲያን ጉዳዩን የመከታተል ጥረት ላይ ትገኛለች ማለታቸውን  ሸገር ታይምስ ሚዲያ ከዜና ምንጩ ዘገባ ለመመልከት ችሏል። ኃላፊው “እስካሁን በተደረገው ክትትል “ሊቀ አዕላፍ በላይ መኮንን በህግ ጥላ ስር የዋሉበት ጉዳይ ከቤተክርስቲያናችን ጋር የሚያገናኘው ምንም ጉዳይ እንደሌለና በግል ህይወታቸው ውስጥ የገጠማቸው ነገር እንደሆነ ነው የተረዳነው” ብለዋል። መምህር ዶ/ር አካለወልድ አክለውም በቀጣይ ጉዳዩ ቤተክርስቲያንን የሚጎዳ ነገር አለው ወይ? የሚለው በህግ ክፍል በኩል ማጣራት እንዲደረግ ትዕዛዝ መተላለፉንም አመልክተዋል፡፡
Mostrar más ...
8 184
5
የፈረሱት ሰፈሮች ለጨረታ ቀረቡ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ፣ በአራዳ ክፍለ ከተማ ፒያሳ ለኮሪደር ልማት ሲል ያፈረሳቸውን ሠፈሮች ጨምሮ በ250 በላይ ቦታዎች ላይ የሊዝ ጨረታ ማውጣቱን ተሰምቷል። የሊዝ ጨረታው የወጣባቸው ቦታዎች በአስር ክፍለ ከተሞች የሚገኙ ናቸው። በፈረሰው ፒያሳ አካባቢ 2 ሺህ 179 ካሬ ሜትር ስፋት ካለው ቦታ ጀምሮ እስከ ዝቅተኛው 650 ካሬ ሜትር ድረስ የሚገኙ 22 ቦታዎች የሊዝ ጨረታ ወጥቶባቸዋል። አስተዳደሩ ለ22ቱም ቦታዎች ያቀረበው የሊዝ መነሻ ዋጋ በካሬ 2 ሺህ 213 ብር ከ25 ሳንቲም ነው። የአኹኑ የሊዝ ጨረታ፣ የከተማ አስተዳደሩ ባለፈው ዓመት መጨረሻ ካወጣው የሊዝ ጨረታ በኋላ ለኹለተኛ ጊዜ የወጣ ነው። ዋዜማ
8 217
33
Última actualización: 11.07.23
Política de privacidad Telemetrio