Best analytics service

Add your telegram channel for

  • get advanced analytics
  • get more advertisers
  • find out the gender of subscriber
Гео и язык канала

статистика аудитории ዳጉ-ጆርናል/Dagu-Journal

The best fiction is far more true than any journalism 📢 ተዓማኒ የመረጃ ምንጭ ፤ ለሙያው ስነምግባር ተገዢ በሆኑ ጋዜጠኞች ብቻ 👉 በፌስቡክ ገፆቻችን  https://www.facebook.com/simon.dereje.56  👉  https://www.facebook.com/mik0Man  
Показать больше
40 690-8
~5 990
~18
19.62%
Общий рейтинг Telegram
В мире
29 690место
из 78 777
В стране, Эфиопия 
223место
из 396
В категории
1 938место
из 3 169

Пол подписчиков

Если это ваш канал, тогда можете узнать какое количество женщин и мужчин подписаны на канал.
?%
?%

Язык аудитории

Если это ваш канал, тогда можете узнать какое распределение подписчиков канала по языкам
Русский?%Английский?%Арабский?%
Количество подписчиков
ГрафикТаблица
Д
Н
М
Г
help

Идет загрузка данных

Время жизни пользователя на канале

Если это ваш канал, тогда можете узнать как надолго задерживаются подписчики на канале.
До недели?%Старожилы?%До месяца?%
Прирост подписчиков
ГрафикТаблица
Д
Н
М
Г
help

Идет загрузка данных

Since the beginning of the war, more than 2000 civilians have been killed by Russian missiles, according to official data. Help us protect Ukrainians from missiles - provide max military assisstance to Ukraine #Ukraine. #StandWithUkraine
ቀያይ ሰይጣኖቹ ነጥብ ተጋሩ በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ማንቼስተር ዩናይትድ እና ክሪስታል ፓላስ ያደረጉት ጨዋታ በአቻ ውጤት ተጠናቋል፡፡ በኳስ ቁጥጥር ማንቼስተር ዩናይትድ ተሽሎ በተገኘበት ጨዋታ ምንም ጎል ሳይቆጠር በአቻ ውጤት ተጠናቅቋል፡፡
3 492
1
Attention | በጊዜያዊነት አገልግሎት ይቋረጣል የተከበራቹሁ የባንካችን ደንበኞች ዛሬ ከለሊቱ 06፡00 ሰዓት እስከ ነገ ከጠዋቱ 12፡00 ሰዓት ድረስ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሲቢኢ ብር አገልግሎት በጊዜያዊነት አገልግሎት ይቋረጣል። ለሚፈጠረው የአገልግሎት መቋረጥ ከልብ ይቅርታ እንጠይቃለን። በዚህ ጊዜ ውስጥ ለሚኖርዎት ትዕግስት እያመሰገንን፤ በሎሎች የዲጂታል አማራጮች የሚፈልጉትን አገልግሎት ማግኘት የሚችሉ መሆኑን እናሳውቃለን።
4 714
11
የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ውጤቶች ጎሎች 👉
4 251
0
በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ውጤቶች ዌስትሀም 0-3 ቼልሲ ⚽️⚽️ኒኮላስ ጃክሰን ⚽️ኮል ፓልመር ቼልሲ ከሜዳ ውጪ ሶስት ጨዋታዎች ድል ማድረግ ችሏል 💪🔵 ሊቨርፑል 3-0 ቦርንመውዝ ⚽️⚽️ሉዊስ ዲያዝ ⚽️ዳርዊን ኑኔዝ ጎሎች 👉
5 117
3
በሀረር ከተማ ቁማር ሲጫወቱ የነበሩ 13 ግለሰቦች በሚስቶቻቸው ጥቆማ በቁጥጥር ስር ዋሉ በግሮሰሪ ቤት ውስጥ በር ዘግተው ቁማር ሲጫወቱ  የነበሩ ግለሰቦች የገዛ የትዳር አጋሮቻቸዉ እና ቤተሰቦቻቸዉ በሰጡት ጥቆማ በቁጥጥር  ስር መዋላቸው ተሰምቷል፡፡ በሀረር ከተማ ጀኒላ ወረዳ ቀበሌ 16 መጠጥ ቤት  በር ዘግተው ቁማር ሲጫወቱ የነበሩ 13 ግለሰቦች እጅ ከፍንጅ በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የጂኒላ ወረዳ ፖሊስ አዛዥ የሆኑት ኮማንደር ሙፍቲ  ከድር  በተለይም ለብስራት ሬዲዮ እና ቴሌቪዥን ተናግረዋል። ግለሰቦቹ ከፍተኛ ገንዘብ እያስያዙ ቁማር ሲጫወቱ የነበረ ሲሆን ባለቤቶቻቸው እንዲሁም ከቤተሰቦቻቸው ለፖሊስ በደረሰ ጥቆማ በቁጥጥር  ስር ሊውሉ መቻላቸው ተገልጿል ። በቁጥጥር ስር በዋሉበት ሰዓት ሰላሳ ሺህ ስምንት መቶ ብር እጅ ከፍንጅ  ተይዟል። ቁማር ከሚጫወቱት ግለሰቦች መካካል አብዛኛዎቹ ለፖሊስ የጠቆሙት የትዳር  አጋሮቻቸው ሲሆኑ ለቤተሰባቸው ትልቅ ችግር እንዲሁም ለኑሯቸው እንቅፋት  ሆኖባቸው እንደነበረ ተረጋግጧል። ይህንን ድርጊት ለመከላከል ፖሊስ ከማህበረሰቡ  ጋር በመተባበረ  እርምጃ የመውሰድ ስራ እንደሚሰራ ኮማንደር ሙፍቲ ከድር ጨምረው ለብስራት ሬዲዮ እና ቴሌቪዥን ተናግረዋል ። በኤደን ሽመልስ
Показать полностью ...
5 181
7
✅ በ አይነቱ ልዩ የሆነ በ ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ 4 ትልቅ ለውጥን መፍጠር የሚችሉ የ ስራ ዘርፎችን ልክ እንደ ግራፊክስ ዲዛይን ቪዲዮ ኤዲቲንግ ዲጂታል ማርኬቲንግ እና አኘ ወርክ በ አንድ ላይ ያካተተ ስልጠና ተጀመረ። 📌 ይሄ ስልጠና መቀመጫውን አሜሪካ አና አዚው ሀገራችን ላይ ባደረጉ ለውጥ ፈጣሪ ትውልደ ኢትዮጵያውያን የተቋቋመ ዘውድ ቴክ በተባለ ድርጅት የተዘጋጀ ነው። 📌 ባለፈው ሳምንት ቅዳሜ በማዶ ሆቴል የዘውድ ቴክ የስራ አጋሮች እና ታዋቂ የሚዲያ ሰዎች በተገኙበት መክፈቻ ፕሮግራምም ተካሂዱዋል። 📌 ዘዉድ ቴክ በኢትዮጵያ የመጀመሪያ ያስባለው የ 25/75% ክፍያ ያመቻቸ ሲሆን  አንድ ሰልጣኝ ለመመዝገብ ዘውድ ቴክ ከሚጠይቀው ክፍያ ላይ 25% ብቻ ከፍሎ ሙሉ የ 3ወሩን ስልጠና የሚወስድ ሲሆን የተቀረውን 75% የሚከፍለው በዘውድ ቴክ በኩል በሚመቻችለት የስራ እድል ከዛላ ከሚያገኘው ገቢ በ አመት ውስጥ እየከፈለ የሚጨርስ ይሆናል 📌ስልጠናውን ላጠናቀቀ certificate እንዲሁም ነፃ የ ኢንተርናሽናል ክፍያ መፈፀምያ ማስተር ካርድ የሚያገኝ ይሆናል 📌ስልጠናው ሙሉ በሙሉ ኦንላይን እንደመሆኑ ማንኛውም ሰው ከትምህርት እና ስራ ሰዓት በኋላ መማር ይችላል። ⚠️ያለው ቦታ ውስን ስለሆነ ከታች በተቀመጠው ሊንክ የዘውድ ቴክ ቻናልን ተቀላቅላችሁ እዛ ላይ የሚገኘውን የስልጠና ገለፃ ቪድዮ ተመልክታችሁ ባሉት ስልክ ቁጥሮች መደወል እና መልዕክት ማስቀመጥ ትችላላችሁ። 👇የዘውድ ቴክ ቻናልን ለመቀላቀል መልካም እድል!
Показать полностью ...
4 988
3
የ15 ዓመት ታዳጊን ለአራት በመሆን የአስገድዶ መድፈር ወንጀል የፈፀሙ ተከሳሾች በእስራት ተቀጡ በኮንታ ዞን አመያ ዙሪያ ወረዳ ኦፓላሼ ቀበሌ ለአራት በመሆን የ15 ዓመት ታዳጊን አስገድዶ መድፈር ወንጀል የፈፀሙ ተከሳሾች በእስራት ተቀጡ። ተከሳሾች በቁጥር አራት ሲሆን አስፋቸው አለሙ፣ አሻግሬ አበራ፤  ማቲዎስ ደዋና እና አስማማው አሉላ የተባሉ ግለሰቦች ናቸው። ግለሰቦቹ በአመያ ዙሪያ ወረዳ በግምት 8:00 አካባቢ  ጫሬ ዶቄ ቀበሌ ቤተሰብ ለመጠየቅ ወደ ኦፓላሼ ቀበሌ እየሄደች የምትገኝ የ15 አመት ታዳጊ አስገድደው መድፈራቸውን የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች  ክልል ፖሊስ ኮሚሽን የህዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር ኢንስፔክተር ደጀኔ አሰፋ ለብስራት ሬዲዮ  እና  ቴሌቪዥን ተናግረዋል ። በአስገድዶ መድፈር ወንጀል ጥፋተኛ ሆነው ክስ የቀረበባቸው ወንጀለኞች ጳግሜ 5 ቀን 2016 ዓ.ም  በዋለው ችሎት ከ1ኛ እስከ 3ኛ ተከሳሾች እያንዳንዳቸው 7 ዓመት ፅኑ እስራት  ተቀጥተዋል። አራተኛ ተከሳሽ ዕድሜው ከ10 እስከ 13 ዓመት በመሆኑ ተከሳሹ  መታሰር የማይችልና እንደዚህ ዓይነት ታዳጊ እስረኞችን ተቀብሎ   በማረምያ ተቋም በዞኑ ባለመኖሩ ምክንያት ቤተሰቡ ፈርሞ ወስዶት ክትትልና በቁጥጥር እንዲያደርግ በማለት ውሳኔ መሰጠቱን ኢንስፔክተር ደጀኔ አሰፋ ለብስራት ሬዲዮ  እና  ቴሌቪዥን ተናግረዋል ። በሳምራዊት ስዩም
Показать полностью ...
7 076
17
የደራሲ ሃዲስ አለማየሁ ወራሾች ለ"ፍቅር እስከ መቃብር" ፊልም ሥርጭት እግድ ለዋስትና የተጠየቁትን ገንዘብ ካልከፈሉ ድራማዉ አይቋረጥም የደራሲ ሃዲስ አለማየሁ ወራሾች ለ"ፍቅር እስከ መቃብር" ፊልም ሥርጭት እግድ ለዋስትና የተጠየቁትን ገንዘብ ካልከፈሉ በኢቢሲ የሚተላለፈው የፊልሙ ሥርጭት እንደማይታገድ ዋዜማ ተረድታለች። የፌደራሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ይህን ውሳኔ የሰጠው፣ የደራሲው ወራሾች የፊልሙ ሥርጭት ባስቸኳይ እንዲቆም ያቀረቡትን አቤቱታ ከመረመረና የኢቢሲንና ዋልታን ምላሽ ካዳመጠ በኋላ ነው። ፍርድ ቤቱ፣ በፊልሙ ሥርጭት ላይ እገዳ ሊጣል የሚችለው፣ ከሳሾች ፊልሙ በመቋረጡ ለሚደርሰው ኪሳራ ዋስትና የሚኾን ገንዘብ ገቢ ካደረጉ በኋላ እንደሚኾን ገልጧል።
8 342
16
ሸገር ከተማ መነ አቢቹና ሱሉልታ ክፍለ ከተሞች ለኮሪደር ልማት በርካታ የመኖሪያና ንግድ ቤቶች ያለምንም ካሳና ተለዋጭ ቦታ እንዲፈርሱ ተወስኗል ተባለ በኦሮሚያ ክልል ሸገር ከተማ መነ አቢቹና ሱሉልታ ክፍለ ከተሞች ለኮሪደር ልማት በርካታ የመኖሪያና ንግድ ቤቶች ያለምንም ካሳና ተለዋጭ ቦታ እንዲፈርሱ የተላለፈውን ውሳኔ ተከትሎ፣ ባለ ይዞታዎች ከፍተኛ ስጋት ላይ መውደቃቸውን ለዋዜማ ተናግረዋል። ከይዞታቸው እንደሚነሱ የተነገራቸው ነዋሪዎች፣ በቱፋ ሙና፣ ወሰርቢ እና አባገዳ ወረዳዎች የሚገኙ ናቸው። የክፍለ ከተሞቹ ሠራተኞችና ጸጥታ ኃይሎች ያለ ቅድመ ማስጠንቀቅያ፣ ምልክት ሲያደርጉ እንደሰነበቱና ትናንት በከፊል ማፍረስ እንደጀመሩ ዋዜማ ሰምታለች። ከሚፈርሱት ይዞታዎች መካከል፣ ነዳጅ ማደያዎች፣ ባንኮች፣ ግንባታ ላይ ያሉ ሕንጻዎችና ሆቴሎች ይገኙበታል ተብሏል።
8 177
20
ትራንስፖርት ቢሮው አዲስ የስምሪት ውሳኔውን እንዲቀር ማድረጉን ገለጸ ቢሮው ከትምህርት መከፈት ጋር ተያይዞ ሊፈጠሩ የሚችሉ መጨናነቆችን ለመቀነስ የተወሰኑ የከተማዋ መስመሮች ለብዙሀን ትራንስፖርት አግልግሎት ብቻ ክፍት እንዲሆኑ ወስኖ ነበር ትራንስፖርት ቢሮው አዲስ የስምሪት ውሳኔን እንዲቀር ማድረጉን ገለጸ። የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ ከትምህርት መከፈት ጋር ተያይዞ ሊፈጠሩ የሚችሉ የትራፊክ መጨናነቆችን ለመቀነስ የተወሰኑ የከተማዋ መስመሮች ለብዙሀን ትራንስፖርት አግልግሎት ብቻ ክፍት እንዲሆኑ ወስኖ ነበር። በአዲስ አበባ ለብዙሀን ትራንስፖርት ብቻ አገልግሎት የሚሰጡ 14 መስመሮች ይፋ ሆኑ ቢሮው አሁን ከመሸ ባወጣው መግለጫ ይህን ውሳኔውን እንዲቀር አድርጎታል። እቅዱ ከባለድርሻ አካለት ጋር ውይይት እስከሚደረግበት ድረስ የትራንስፖርት እንቅስቃሴው ባለበት ይቀጥላል ብሏል ቢሮው። ትራንስፖርት ቢሮው ቀደም ሲል ባወጣው መግለጫ የብዙሃን ትራንስፖርት አገልግሎት እንዲሰጡ 14 መስመሮችን ይፋ አድርጎ ነበር። ለብዙሃን ትራንስፖርት አገልግሎት እንዲሰጡ ተለይተው የነበሩት መስመሮች ከቦሌ- ፒያሳ፣ ከቦሌ- ሜክሲኮ፣ ከቦሌ- አራት ኪሎ፣ ከቦሌ አውቶቢስ ተራ፣ ከቦሌ- ሽሮሜዳ፣ ከጀሞ- ፒያሳ እና ከጀሞ- ሜክሲኮ፣ ከፒያሳ- ቦሌ፣ ከሜክሲኮ- ቦሌ፣ ከአራት ኪሎ- ቦሌ፣ ከአውቶቡስ ተራ- ቦሌ፣ ከሽሮ ሜዳ- ቦሌ፣ ከፒያሳ ጀሞ እና ከሜክሲኮ - ጀሞ ነበሩ። የብዙሃን ትራንስፖርት ከ8 ሰው በላይ መያዝ የሚችሉ ተሽከርካሪዎችን የሚያጠቃልል ነው።
Показать полностью ...
8 535
24
በሀረር ከተማ ወርቅ ሰርቀው ሲሸጡ በተፈጠረ አለመግባባት ፀብ ውስጥ የገቡ ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ዋሉ በሀረር ከተማ ሁለት ግለሰቦች ከድሬዳዋ ከተማ ወርቅ መሸጫ መደብር ዉስጥ ወርቅ ሰርቀው በመሸጥ በገንዘብ ክፍፍል በተፈጠረ አለመግባባት በተፈጠረ ፀብ ፖሊስ በቁጥጥር ስር ሊያውላቸው ችሏል። የሀረሪ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን የህዝብ ግንኙነት እና የኮሙኒኬሽን ፅህፈት ቤት ሀላፊ ኮማንደር ጣሰው ቻለው  እንደገለፁት በሀረር ከተማ አንደኛ መንገድ ተብሎ በሚጠራ ስፍራ ሁለት ግለሰቦች በፈጠሩት አለመግባባት ከፍተኛ ፀብ ፈጥረው ድብድብ ውስጥ በመግባታቸው በጥበቃ እንቅስቃሴ ላይ በነበሩ የፖሊስ አባላት ሁለቱን ግለሰቦች በማገላገል በቁጥጥር ስር አውለው ወደ ፖሊስ ጣቢያ ይዘዋቸው እንደሄዱ ገልፀዋል። ፖሊስም ሁለቱን ግለሰቦች በቁጥጥር ስር አውሎ ወደ ፖሊስ ጣቢያ ከወሰዳቸው በኋላ የፀባቸው መንስኤ ሲያጣራ እና የያዙት ቦርሳ ሲፈትሽ በቦርሳው ውስጥ ሰባ አራት ሺህ የኢትዮጵያ ብር ሊገኝ ችሏል።ፖሊስ ብሩን ከየት እንዳመጡት በምርመራ ሂደት ሲጠይቃቸው ከድሬዳዋ ከተማ 17.62 ግራም ወርቅ ከ አንድ የወርቅ መሸጫ መደብር ሰርቀው በመውሰድ ሀረር ከተማ አንደኛ መንገድ ከሚገኝ አንድ ወርቅ ቤት በ መቶ ሺህ የኢትዮጵያ ብር መሸጣቸው ሊያረጋግጥ ችሏል። ሁለቱም ግለሰቦች ከሽያጩ ላይ ሀያ ስድስት ሺህ ብር ደግሞ ማታ አብረዋቸው ሲዝናኑ እና ለሊቱን አብረዋቸው ካሳለፉ ሁለት የሆቴል ቤት እንስቶች እንደሰጧቸው ለፖሊስ ተናግረዋል። ፖሊስ ሁለቱን የሆቴል ቤት እንስቶች በቁጥጥር ስር አውሎ አስራ ሰባት ሺህ አምስት መቶ ብር ከደበቁበት በፍተሻ ማግኘት መቻሉን ገልፀዋል።በአጠቃላይ በሁለቱ ግለሰቦች እና ከሁለቱ እንስቶች ዘጠና አንድ ሺህ አምስት መቶ ብር ከተጠርጣሪዎቹ በቁጥጥር ስር የዋለ ሲሆን የስርቆት ወንጀሉን የፈፀሙት ከድሬደዋ ከተማ ፖሊስ ከሀረር ከተማ ፖሊስ ጋር በጥምረት በመሥራት በአስቸኳይ ለፍትህ እንደሚያቀርባቸው ኮማንደር ጣሰው   ቻለው ጨምረው ገልፀዋል።በሌላ በኩል በሀረር ከተማ ለኮሪደር ልማት ተብሎ በተቆፈረ ጉድጓድ ውስጥ ንብረት እየሰረቁ የሚያከማቹ ግለሰቦች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የጂኔላ ፖሊስ አስታውቋል። የጂኔላ ወረዳ ፖሊስ አዛዥ  ኮማንደር  መሱድ ከድር እንደገለፁት በሀረር ከተማ  ጂኔላ ወረዳ ቀበሌ 16 አካባቢ ሁለት ግለሰቦች ለኮሪደር ልማት ተብሎ የተቆፈረው ጉርጎድ ውስጥ ሁለት ባለ 43 ኢንች ፍላት ቴሌቭዥን ሁለት ባለ 32 ኢንች ቴሌቭዥን፣ ሁለት የዲሽ ሪሲቨር ዘርፈው በመውሰድ ሶፊ ወረዳ  ደከር ትምህርት ቤት በሚጠራው አካባቢ ለኮሪደር ልማት የተቆፈረ ጉድጎድ ውስጥ  እንደሚያጠራቅሙ በህብረተሠቡ በደረሰ ጥቆማ በቁጥጥር ስር ሊውሉ ችለዋል። ሁለቱ ግለሰቦች ለኮሪደር ልማት የተቆፈረውን ጉርጓድ ለስርቆት መጠቀሚያ በማድረግ በርካታ እቃዎችን በጨለማ እየሰረቁ በጉርጎድ ውስጥ እየደበቁ እያወጡ ሲሸጡ እንደነበረ የተናገሩት ኮማንደሩ ኮማንደር መሱድ ከድር  ህብረተሰቡ ለኮሪደር ልማት ተብሎ የተቆፈሩ ጉርጓዶችን በመጠበቅ የስርቆት ወንጀልን እንዲከላከል ኮማንደር  የሱፍ  ከድር ጨምረው ገልፀዋል። ሰመዓል አለባቸዉ
Показать полностью ...
7 863
7
በቦረና ዞን 99 ኪሎ ግራም አደንዛዥ እፅ በሞተር ብስክሌት ሲጓጓዝ በቁጥጥር ስር ዋለ በቦረና ዞን በጎምቦሌ ወረዳ በሞተር ብስክሌት ሲጓጓዝ የነበረ 99 ኪሎ ግራም አደንዛዥ እፅ በቁጥጥር ስር መዋሉን የወረዳዉ ፖሊስ ፅህፈት ቤት አስታዉቋል፡፡ የጎምቦሌ ወረዳ ፖሊስ አዛዥ ተወካይ ምክትል ኢንስፔክተር ዮናስ ዳሊስ ለብስራት እንደተናገሩት መስከረም 7 ቀን 2017 ዓ.ም ከለሊቱ 7 ሰአት ላይ ሞተር ብስክሌት በመጠቀም 99 ኪሎ ግራም ካናቢስ የተሰኘ አደንዛዥ እፅ ከምዕራብ ጉጂ ዞን ወደ ቦረና ዞን ጎምቦሌ ወረዳ ሲጓጓዝ ቱላ ዋዩ ቀበሌ በተደረገዉ ድንገተኛ ፍተሻ በቁጥጥር ስር መዋሉን ተናግረዋል፡፡ በቁጥጥር ስር የዋለዉ 99 ኪሎ ግራም ካናቢስ የተሰኘዉ እፅ በሞተር ብስክሌት በድብቅ ሲጓጓዝ ህብረተሰቡ ለፖሊስ በሰጠዉ ጥቆማ መሰረት በቁጥጥር ስር የዋሉ በመሆኑ ማህበረሰቡ የአደንዛዥ እፅ ዝዉዉር በሀገር ላይ የሚያስከትለዉን የወንጀል ቀዉስ ተረድቶ አዘዋዋሪዎችን አጋልጦ ለፀጥታ አካላት እየሰጠ እንደሚገኝ ምክትል ኢንስፔክተር ዮናስ ዳሊስ  ገልፀዋል፡፡  ካናቢስ የተሰኘዉን 99 ኪሎ ግራም አደንዛዥ እፅ በሞተር ብስክሌት ሲያጓጉዙ የነበሩ ግለሰቦች የምርመራ መዝገባቸዉ ተጣርቶ በቅርብ ቀን በአስቸካይ ለፍትህ እንደሚቀርብ ተመላክቷል፡፡ በመባ ወርቅነህ
Показать полностью ...
7 725
5
በ“ኬጂ” ደረጃ ተቋርጦ የነበረው የእንግሊዘኛ ቋንቋ ትምህርት በድጋሚ ሊሰጥ ነው! ባለፈው ዓመት ተቋርጦ የነበረው የቅድመ መደበኛ (ኬጂ) የእንግሊዘኛ ቋንቋ ትምህርት፤ በዚህ ሳምንት በተጀመረው የ2017 ዓ.ም. የትምህርት ዘመን በሳምንት ለአምስት ጊዜ ሊሰጥ ነው።የአዲስ አበባ ከተማ ትምህርት ቢሮ ለቅድመ መደበኛ ትምህርት ያዘጋጀው የእንግሊዘኛ ቋንቋ የተማሪዎች መፅሐፍ እና የመምህራን መምሪያ ለመንግሥት ትምህርት ቤቶች መሠራጨቱን ቢቢሲ ያነጋገራቸው ርዕሰ መምህራን እና መምህራን ገልጸዋል። ሕጻናት ወደ አንደኛ ክፍል ከመሸጋገራቸው አስቀድሞ ባለው ቅድመ መደበኛ ደረጃ ለሚማሩ ተማሪዎች ሲሰጥ የነበረው የእንግሊዘኛ ትምህርት የተቋረጠው፤ በ2016 ዓ.ም. አዲስ ሥርዓተ ትምህርት (ካሪኩለም) መተገበር በመጀመሩ ነበር።ለመጀመሪያ ጊዜ የተዘጋጀው የቅድመ መደበኛ ሥርዓተ ትምህርት፤ ከዚህ ቀደም ለ“ኬጂ” ተማሪዎች ትምህርት ሲሰጥ የነበረበትን መንገድ የቀየረ ነው።አዲሱ ሥርዓተ ትምህርት፤ የቅድመ መደበኛ ትምህርት በሌሎች ደረጃዎች እንደሚደረገው ሒሳብ፣ ሳይንስ፣ ቋንቋ በሚሉ የትምህርት ዓይነቶች እንዳይከፋፈል ያደረገ ነው።
Показать полностью ...
7 499
7
📱🌼Broz mobile and computer 🌼📱 🍏Original iPHONE, Samsung & Tab  አዳዲስ እንዲሁም ያገለገሉ ስልኮችን በተመጣጣኝ ዋጋ እና ያሎት ስልክ ላይ በመጨመር ከበቂ ዋስትና  እና ጥገና ጋር  እኛው  ጋር  ያገኛሉ ። Telegram Channel ቀድመው ይደውሉ 👇 Contact us ☎️      251911120707      251904818881 📍ቦሌ መድሃኒአለም
7 185
0
እስከ መስከረም 15 ሃብታቸውን ለማስመዝገብ ፈቃደኛ በማይሆኑ አመራርና ሰራተኞች ላይ እርምጃ  ይወሰዳል ተባለ በአዲስ አበባ የንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ሰራተኞች፣ ቡድን መሪዎችና አመራሮች በሙሉ ሃብታቸውን ማስመዝገብ እንዳለባቸው የክፍለ ከተማው የስነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ቡድን አስታውቋል ። የአዲስ አበባ ስነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን በሃብት ማሳወቂያና ማስመዝገቢያ አዋጅ ቁጥር 668/2002 የተዘጋጀ ማኑዋልን መሰረት በማድረግ በክፍለ ከተማው የሚገኙ  ሰራተኞች፣ ቡድን መሪዎችና አመራሮች እስከ መስከረም 15 ቀን 2017 ዓ.ም ድረስ ሃብታቸውን ማስመዝገብ እንዳለባቸው ተጠቁሟል። በተጠቀሰው የጊዜ ገደብ ውስጥ ሃብቱን ያላስመዘገበ አካል 1000 ብር ቅጣት ከፍሎ በ5 ቀናት ውስጥ ማስመዝገብ እንደሚቻል ተገልጿል ። ይሁን እንጂ ሃብቱን ለማስመዝገብ ፈቃደኛ ያልሆነ ሰው በወንጀል የሚጠየቅና እንደ መስሪያ ቤቱ አስተዳደር ውስጠ ደንብ መሰረት አስተዳደራዊ እርምጃ  እንደሚመወሰድ ተገልጿል ። ሰራተኞችና አመራሮች ለተጨማሪ ወጪ እንዲሁም ቅጣት እንዳይዳረጉ በተቀመጠው የጊዜ ገደብ በክፍለ ከተማው በሚገኘው የስነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ቡድን ክፍል በመገኘት ሃብታቸውን ማስመዝገብ እንደሚገባ ተገልጿል ።
Показать полностью ...
7 211
8
✅ በ አይነቱ ልዩ የሆነ በ ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ 4 ትልቅ ለውጥን መፍጠር የሚችሉ የ ስራ ዘርፎችን ልክ እንደ ግራፊክስ ዲዛይን ቪዲዮ ኤዲቲንግ ዲጂታል ማርኬቲንግ እና አኘ ወርክ በ አንድ ላይ ያካተተ ስልጠና ተጀመረ። 📌 ይሄ ስልጠና መቀመጫውን አሜሪካ አና አዚው ሀገራችን ላይ ባደረጉ ለውጥ ፈጣሪ ትውልደ ኢትዮጵያውያን የተቋቋመ ዘውድ ቴክ በተባለ ድርጅት የተዘጋጀ ነው። 📌 ባለፈው ሳምንት ቅዳሜ በማዶ ሆቴል የዘውድ ቴክ የስራ አጋሮች እና ታዋቂ የሚዲያ ሰዎች በተገኙበት መክፈቻ ፕሮግራምም ተካሂዱዋል። 📌 ዘዉድ ቴክ በኢትዮጵያ የመጀመሪያ ያስባለው የ 25/75% ክፍያ ያመቻቸ ሲሆን  አንድ ሰልጣኝ ለመመዝገብ ዘውድ ቴክ ከሚጠይቀው ክፍያ ላይ 25% ብቻ ከፍሎ ሙሉ የ 3ወሩን ስልጠና የሚወስድ ሲሆን የተቀረውን 75% የሚከፍለው በዘውድ ቴክ በኩል በሚመቻችለት የስራ እድል ከዛላ ከሚያገኘው ገቢ በ አመት ውስጥ እየከፈለ የሚጨርስ ይሆናል 📌ስልጠናውን ላጠናቀቀ certificate እንዲሁም ነፃ የ ኢንተርናሽናል ክፍያ መፈፀምያ ማስተር ካርድ የሚያገኝ ይሆናል 📌ስልጠናው ሙሉ በሙሉ ኦንላይን እንደመሆኑ ማንኛውም ሰው ከትምህርት እና ስራ ሰዓት በኋላ መማር ይችላል። ⚠️ያለው ቦታ ውስን ስለሆነ ከታች በተቀመጠው ሊንክ የዘውድ ቴክ ቻናልን ተቀላቅላችሁ እዛ ላይ የሚገኘውን የስልጠና ገለፃ ቪድዮ ተመልክታችሁ ባሉት ስልክ ቁጥሮች መደወል እና መልዕክት ማስቀመጥ ትችላላችሁ። 👇የዘውድ ቴክ ቻናልን ለመቀላቀል መልካም እድል!
Показать полностью ...
6 418
14
በአዲስ አበባ ለብዙሃን ትራንስፖርት ብቻ አገልግሎት የሚሰጡ መስመሮች ይፋ ሆኑ ከትምህርት ቤቶች መከፈት ጋር ተያይዞ የትራፊክ መጨናነቅ እንዳይፈጠር የብዙሃን ትራንስፖርት አገልግሎት ከመጪው እሑድ ጀምሮ በተመረጡ መስመሮች ላይ ተግባራዊ እንደሚደረግ የከተማዋ ትራንስፖርት ቢሮ አስታውቋል።መስመሮቹም ከቦሌ- ፒያሳ፣ ከቦሌ- ሜክሲኮ፣ ከቦሌ- አራት ኪሎ፣ ከቦሌ- አውቶቢስ ተራ፣ ከቦሌ- ሽሮሜዳ፣ ከጀሞ- ፒያሳ እና ከጀሞ- ሜክሲኮ መሆናቸው ተገልጿል፡፡ በተመሳሳይ ከፒያሳ- ቦሌ፣ ከሜክሲኮ- ቦሌ፣ ከአራት ኪሎ- ቦሌ፣ ከአውቶቡስ ተራ- ቦሌ፣ ከሽሮ ሜዳ- ቦሌ፣ ከፒያሳ ጀሞ እና ከሜክሲኮ - ጀሞ የብዙሃን ትራንስፖርት አገልግሎት ብቻ መሰጠት እንደሚጀምር ተመላክቷል፡፡ቢሮው " የአገልግሎቱ መጀመር የመንገድ መዘጋጋቱን ለመቀነስ እና ብዙ የሰው ቁጥር ያለው ተጓዥ በአንድ ጊዜ ማመላለስ ያስችላል " ብሏል። በዚህም ተማሪና መምህራን ብሎም ሌሎች ተገልጋዮች በሰዓታቸው ወደ ሚፈልጉት ቦታ በመንቀሳቀስ አገልግሎት እንዲያገኙ ያግዛል ተብሏል፡፡" በከተማዋ ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴው የተነቃቃ እንዲሆን ጉልህ አስተዋጽኦ ያበረክታል " ሲልም አክሏል። ዜጎች የሚያጋጥሟቸውንና የሚስተዋሉ ችግሮችን በአቅራቢያ ለሚገኙ የትራንስፖርት ቁጥጥር ሰራተኞች ወይም በ9417 ነፃ የስልክ መስመር ጥቆማ እንዲሰጡ ተጠይቋል፡፡
Показать полностью ...
7 164
13
በዩክሬን ጦርነት ከ70 ሺ በላይ የሩሲያ ወታደሮችና ወዶ ገብ ተዋጊዎች መገደላቸው ተሰማ በቢቢሲ የተተነተነ መረጃ እንደሚያሳየው ከ 70,000 በላይ ሰዎች በሩሲያ ጦር ውስጥ እየተዋጉ በዩክሬን መገደላቸውን አመላክቷል። በጎ ፈቃደኛ ተዋጊዎች እና ጦርነቱ ከተጀመረ ወዲህ ወደ ጦር ሰራዊቱ የተቀላቀሉ ሲቪሎች ላይ በ 2022 ሩሲያ ሙሉ ወረራ ከጀመረ ወዲህ ከፍተኛውን የሞት ቁጥር ተመዝግቧል ። በየእለቱ በዩክሬን የተገደሉት ሰዎች ስም፣ የቀብር ስነ ስርዓታቸው እና ፎቶግራፎች በመላው ሩሲያ በመገናኛ ብዙሃን እና በማህበራዊ አውታረመረቦች ላይ ይታተማሉ። ቢቢሲ ረስኪ እና ሚድያዞና የተባለው ገለልተኛ ድህረ ገጽ እነዚህን ይፋ የሚደረጉ ስሞች ከሌሎች ምንጮች ጋር በማከል መረጃ አጋርተዋል።መረጃው የሟቾችን ሪፖርት ወይም የሟች ዘመዶች ያካፈሉት መሆኑን እና በጦርነቱ ውስጥ እንደሞቱ የተረጋገጡ ናቸው። አዳዲስ መቃብሮች በዩክሬን የተገደሉትን ወታደሮች ስም ለማወቅ አግዘዋል። ብዙውን ጊዜ በመከላከያ ሚኒስቴር በተላኩ ባንዲራዎች እና የአበባ ጉንጉኖች በሟቾች ላይ ምልክት ይደረግባቸዋል ።በዩክሬን የተገደሉትን የ 70 ሺ 1 መቶ 12 የሩስያ ወታደሮችን ስም ለይተናል ነገር ግን ትክክለኛው ቁጥር ከተገለፀውም እጅግ ከፍ ያለ ነው ተብሎ ይታመናል። አንዳንድ ቤተሰቦች የዘመዶቻቸውን ሞት በአደባባይ ይፋ የማያደርጉ በመሆናቸው በትንታኔው የተገለፀው ቁጥር ከዚህ የላቀ ነው። ይህ የሟቾች ቁጥር በዩክሬን ምሥራቃዊ ክፍል በራሺያ የተያዙትን የዶኔትስክ እና ሉሃንስክ ግዛቶች ውስጥ የተገደሉትን የታጣቂዎች ቁጥር አያካትትም። ከሟቾቹ መካከል 13 ሺ 7 መቶ 81 ያህሉ ወይም 20 በመቶ ገደማ በጎ ፈቃደኛ ተዋጊዎች ናቸው። የበጎ ፈቃደኛ ተዋጊዎች ሞት ከሌሎች የውጊያ አውድማ ውስጥ ካሉት በልጧል። ለወንጀላቸው ይቅርታ እንዲደረግላቸው የተቀላቀሉት የቀድሞ እስረኞች ሞት ቀደም ሲል ከፍተኛው ነበር። ነገር ግን አሁን ከተረጋገጡት ሞት 19 በመቶ ያህል ድርሻ አላቸው። ከጦርነቱ በፊት ከሩሲያ ጦር የተቀነሱ ወታደሮች ዳግም ለመዋጋት ከተጠሩት መካከል ከሟቾች ድርሻ 13 በመቶ ይይዛሉ። ካለፈው አመት ጥቅምት ወር ጀምሮ በየሳምንቱ የበጎ ፈቃደኞች ሞት ከ100 በታች አልተመዘገበም። በአንዳንድ ሳምንታት ከ310 በላይ የሩሲያ ጦር የበጎ ፈቃደኞች ሞት ተመዝግቧል። በግንባር ቀደምትነት ከሚሞቱት አብዛኞቹ በጎ ፈቃደኞች መካከል እድሜያቸው ከ42 እስከ 50 ዓመት የሆኑ ሲሆን በተጠቀሰው የእድሜ ክልል ውስጥ ያሉ ቁጥራቸው 4,100 ያህል ወንዶች ህልፈት ተመዝግቧል። በጦርነቱ የተገደሉት አንጋፋው በጎ ፈቃደኛ የሩሲያ ጦር አባል የ71 ዓመት አዛውንት ሲሆኑ በአጠቃላይ ከ60 ዓመት በላይ የሆናቸው 250 በጎ ፈቃደኞች በጦርነቱ ተገድለዋል።ዩክሬን በጦር ሜዳ ላይ ስለሞቱባት ወታደሮች የሞት መጠን በይፋ አስተያየት አትሰጥንም ። በየካቲት ወር ፕሬዚዳንቱ ቮሎዲሚር ዘለንስኪ 31,000 የዩክሬን ወታደሮች መገደላቸውን ቢናገሩም በአሜሪካ የስለላ ድርጅት መረጃ ላይ የተመሰረቱ  ግምቶች ግን ከዚህ የበለጠ ኪሳራ ዩክሬን እንደደረሰባት ይጠቁማል። በስምኦን ደረጄ
Показать полностью ...
7 149
1
6 991
0
በ2016 ዓመት ብቻ በክፍያ መንገዶች ላይ 651 የትራፊክ አደጋዎች ደርሰዋል አደጋዎቹ የደረሱት ኢንተርፕራይዙ በሚያስተዳድራቸው የክፍያ መንገዶችን በሆኑ አዲስ አበባ-አዳማ ፣ ድሬደዋ-ደወሌ እና የሞጆ-ባቱ መንገዶች ላይ መሆኑን የኢትዮጵያ ክፍያ መንገዶች ኢንተርፕራይዝ አስታውቋል። የኢንተርፕራይዙ የኮሙኒኬሽን ባለሙያ አቶ ስንታየው መኮንን ለብስራት ሬዲዮ እና ቴሌቪዥን እንደተናገሩት ኢንተርፕራይዙ በሚያስተዳድራቸው ሶስቱ መንገዶች በደረሱት 651 የትራፊክ አደጋዎች 47 ሰዎች ሲሞቱ  169 ሰዎች ላይ ከባድ እና 352 ደግሞ ቀላል አደጋዎች ደርሰዋል። በደረሱት የትራፊክ አደጋዎቹ በሚሊየን የሚቆጠር ንብረት መውደሙ ታውቋል። ለአደጋዎቹ መከሰት ዋና ዋና ተብለው ከተቀመጡት ምክንያቶች መካከል የቴክኒክ ችግር ያለባቸው ተሽከርካሪዎች ፣ ከፍጥነት ወሰን በላይ ማሽከርከርና የአሽከርካሪዎች የስነምግባር ጉድለት ዋና ዋና መሆናቸው አቶ ስንታየው ጨምረው ነግረውናል ፡፡ አሁን ያለንበት የክረምት ወቅትም በመሆኑ ወደ ፈጣን መንገዶች የሚገቡ አሽከርካሪዎች የትራፊክ መመሪያዎችን ተግባራዊ እንዲያደርጉ እና ፍጥነታቸው እንዲቆጣጠሩ አሳስበዋል፡፡ በትግስት ላቀው
Показать полностью ...
7 718
2
ባለፈዉ ዓመት ህይወታቸዉ ባለፈዉ ቢሊየነሩ ሞሃመድ አል ፋይድ የአስገድዶ መደፈር ጥቃት ተፈጽሞብናል ያሉ ሴቶች ቅሬታ አቀረቡ አምስት ሴቶች በለንደን የቅንጦት ምርቶች መሸጫ መደብር ውስጥ ሲሰሩ በቀድሞው የሃሮድስ አለቃ መሀመድ አል ፋይድ እንደተደፈሩ ተናግረዋል ።ባለፈው አመት በ94 አመታቸው ከዚህ አለም በሞት የተለዩት ቢሊየነሩ አስገድዶ መድፈርን ጨምሮ ጾታዊ ጥቃት የፈጸሙባቸዉ ሴቶች ቁጥር ከ20 በላይ እንደሚደርስ የቀድሞ ሰራተኞች ምስክርነታቸውን ተሰምቷል። ከ 20 በላይ ጥቃት የደረሰባቸዉ ሴቶች ሁሉም የፋይድ የቀድሞ ሰራተኞች የነበሩ ሲሆን ወሲባዊ ጥቃት እና በደል እንዳይጋለጥ ተሸፋፍኖ መቆየቱን ተናግረዋል፡፡የቅንጡ መደብሩ የአሁን ባለቤቶች በክሱ "በጣም መደናገጣቸዉን በመግለጽ" ተጎጂዎችን ይቅርታ ጠይቀዋል። እ.ኤ.አ. በ2010 ሃሮድስን የሸጠው ፋይይድ ባለፈው አመት በ94 አመቱ ከዚህ አለም በሞት ተለይቷል። ዘ ጋርዲያን ላይ በሟች ህይወት ላይ በቀረበዉ መጽሃፍ በሴት ሰራተኞች ላይ የፆታዊ ትንኮሳ ተደጋጋሚ ክሶች እንደነበሩ ተናግሯል። በስምኦን ደረጄ
Показать полностью ...
7 321
4
የኢትዮጵያን የሻይ ቅጠል ምርት 99 በመቶ የምትገዛዉ እንግሊዝ መሆኗ ተነገረ ኢትዮጵያ በተጠናቀቀው የ2016 በጀት አመት 1ሺህ 1መቶ 42 ቶን  የሻይ ምርትን ለውጪ ገበያ በመላክ 2.3 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር ገቢ ማግኘት ችላለች ሲል የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታውቋል:: በባለስልጣኑ የህዝብ ግንኙነትና የኮሚኒኬሽን ስራ አስፈፃሚ አቶ ሳህለማርያም ገብረ መድህን ለብስራትu ሬዲዮና ቴሌቪዥን እንደተናገሩት አፈጻጸሙ ከባለፈው በጀት ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ከተላከው ጋር ሲነጻጸር የተሻለ ገቢ የተገኘበት ነው::በመጠን  ደረጃ 2መቶ 92.43 ቶን  እና በገቢ 0.33 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ጭማሪ ተመዝግቧል ያሉት አቶ ሳህለ ማርያም ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የ50 ሺህ ቶን ብልጫ እንዳለው ተናግረዋል:: ምንም እንኳን በበጀት አመቱ ከሻይ ምርት ወጪ ንግድ የተሻለ ገቢ  ማግኘት ቢቻልም ኢትዮጵያ  ካላት አቅም አንጻር  ግን ብዙ መሥራት የሚጠይቅ ነው ሲሉ ጨምረው ለጣቢያችን ተናግረዋል።ኢትዮጵያ ለሻይ ምርት ምቹ የሆነ የአየር ጸባይና የአፈር ሁኔታ ያላት አገር ብትሆንም ባለኃብቶች በዘርፉ በስፋት ባለመሳተፋቸው ማግኘት ያለባትን የውጭ ምንዛሬ እንዳታገኝ እንቅፋት ሆኖባታል ተብሏል። አያይዘዉም በአሁኑ ወቅት የሻይ ቅጠል ምርትን የማስፋት ሥራ በስፋት እየተከናወነ ይገኛል ብለዋል፡፡ምርቱን ለማስፋት 460 ሚሊዮን ችግኞችን በማባዛት በ2016 በጀት ዓመት 30 ሺህ ሄክታር የሚሸፍን የሻይ ቅጠል ምርት ተተክሏል፡፡ ቀደም ሲል በኢትዮጵያ በቀዳሚነት ተጠቃሽ የሆነው የውሽውሽና ጉመሮ ምርት በ5 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ ብቻ ያረፈ ነበር ሲሉ የገለፁት አቶ ሳህለ ማርያም በዚህም እስካሁን ከሻይ ቅጠል የሚገኘው የውጭ ምንዛሬ በዓመት ከ3 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር የሚበልጥ አልነበረም ነው ያሉት ። ከሻይ ምርት ወጪ ንግድ የሚገኘውን ገቢ ለማሳደግ በኦሮሚያ ክልል ቀደም ሲል በተበታተነ መልኩ ይካሄድ የነበረውን የሻይ ተከላ ስራ  ከ2014 በጀት ዓመት ጀምሮ በክላስተር ደረጃ ማምረት ተጀምሯል ሲል ባለስልጣኑ አስታውቋል፡፡ ኢትዮጵያ 99 በመቶ የሚሆነውን የሻይ ምርት ወደ እንግሊዝ ትልካለች፡፡ በቅድስት ደጀኔ
Показать полностью ...
7 797
3
ተወዳጇ ከያኒ አዜብ ወርቁ ከግማሽ ቀን እስር በኃላ ተፈታች አሁን በስልክ ደውዬ አጣርቻለሁ። ትላንት በቁጥጥር ስር ውላ የነበረችው አዜው ወርቁ ለግማሽ ቀን ያህል በእስር ከቆየች በኋላ ከጥቂት ደቂቃዎች በፊት መለቀቋን ከቤተሰቦቿ ለማረጋገጥ ችያለሁ። Via ያሬድ ሹመት
8 041
4
ዴቪድ ራያ በዚህ የቶማስ ፓርቴ ስህተት የተገኘውን የፍፁም ቅጣት ምት ፤  ሬቴጊዪ ቢመታትም ያውም ሁለቴ ማዳን ችሏል 🔥 ተመልከቱ 👉
8 305
2
ላሚን ያማል የመጀመሪያውን የሻምፒዮንስ ሊግ ጎሉ አስቆጥሯል 🌟 ይኸውም በሻምፒዮንስ ሊግ ታሪክ ከአንሱ ፋቲ በመቀጠል ሁለተኛው ወጣት ግብ አስቆጣሪ ያደርገዋል 👶 ጎሉን 👉
8 294
2
አንሄል ዲ ማሪያ በ15ኛ የሻምፒዮንስ ሊግ ተሳትፎው አሁንም የጨዋታው ኮከብ ሽልማቱን እየተቀበለ ይገኛል 👏
8 197
2
ኤሪክ ጋርሲያ ሚናሚኖ ላይ በሰራው ጥፋት በቀጥታ በቀይ ካርድ ወጥቷል 😳 ይህ የሆነው በጋርሲያ እና ግብ ጠባቂው ቴር ስቴገን መካከል ያለመግባባት በመፈጠሩ በተገኘ አጋጣሚ ነበር ... ግቦችን ለመከታተል 👉
7 767
2
✅ በ አይነቱ ልዩ የሆነ በ ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ 4 ትልቅ ለውጥን መፍጠር የሚችሉ የ ስራ ዘርፎችን ልክ እንደ ግራፊክስ ዲዛይን ቪዲዮ ኤዲቲንግ ዲጂታል ማርኬቲንግ እና አኘ ወርክ በ አንድ ላይ ያካተተ ስልጠና ተጀመረ። 📌 ይሄ ስልጠና መቀመጫውን አሜሪካ አና አዚው ሀገራችን ላይ ባደረጉ ለውጥ ፈጣሪ ትውልደ ኢትዮጵያውያን የተቋቋመ ዘውድ ቴክ በተባለ ድርጅት የተዘጋጀ ነው። 📌 ባለፈው ሳምንት ቅዳሜ በማዶ ሆቴል የዘውድ ቴክ የስራ አጋሮች እና ታዋቂ የሚዲያ ሰዎች በተገኙበት መክፈቻ ፕሮግራምም ተካሂዱዋል። 📌 ዘዉድ ቴክ በኢትዮጵያ የመጀመሪያ ያስባለው የ 25/75% ክፍያ ያመቻቸ ሲሆን  አንድ ሰልጣኝ ለመመዝገብ ዘውድ ቴክ ከሚጠይቀው ክፍያ ላይ 25% ብቻ ከፍሎ ሙሉ የ 3ወሩን ስልጠና የሚወስድ ሲሆን የተቀረውን 75% የሚከፍለው በዘውድ ቴክ በኩል በሚመቻችለት የስራ እድል ከዛላ ከሚያገኘው ገቢ በ አመት ውስጥ እየከፈለ የሚጨርስ ይሆናል 📌ስልጠናውን ላጠናቀቀ certificate እንዲሁም ነፃ የ ኢንተርናሽናል ክፍያ መፈፀምያ ማስተር ካርድ የሚያገኝ ይሆናል 📌ስልጠናው ሙሉ በሙሉ ኦንላይን እንደመሆኑ ማንኛውም ሰው ከትምህርት እና ስራ ሰዓት በኋላ መማር ይችላል። ⚠️ያለው ቦታ ውስን ስለሆነ ከታች በተቀመጠው ሊንክ የዘውድ ቴክ ቻናልን ተቀላቅላችሁ እዛ ላይ የሚገኘውን የስልጠና ገለፃ ቪድዮ ተመልክታችሁ ባሉት ስልክ ቁጥሮች መደወል እና መልዕክት ማስቀመጥ ትችላላችሁ። 👇የዘውድ ቴክ ቻናልን ለመቀላቀል መልካም እድል!
Показать полностью ...
7 301
42
Последнее обновление: 11.07.23
Политика конфиденциальности Telemetrio