የዕለተ ማክሰኞ የተመረጡ ዜናዎች!
▪ማዕከላዊ ጎንደር ምዕራብ በለሳ ወረዳ ከጠንገዝ ቤተመንግስት አቅራቢያ በሚገኘው በተለምዶ ፈንጠሪሃ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ትላንት ቀኑን ሙሉ በተደረገ ውጊያ በርካታ የሚሊሻ አባላት መገደላቸውን ያገኘነው መረጃ ያመላክታል። ዛሬ ደግሞ ውጊያው ወደ ጎንደር ዙሪያ እየተስፋፋ መጥቶ ደንጎላ አካባቢ በከባድ መሳሪያ የታገዘ ውጊያ እንዳለም ለማወቅ ችለናል።
▪በእስቴ ወረዳ አካባቢ ሁለት የብልፅግና አመራሮችና ተጨማሪ የፖሊስ አባላት በፋኖ አባላት ተማርከው መወሰዳቸውን ከአካባቢው ነዋሪዎች ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።
▪የደብረታቦር የፖለቲካ አመራሮችና ቤተሰቦቻቸው ምንም አይነት የመንግስት ትራንስፖርት እንዳይጠቀሙ መመሪያ ወርዷል ተብሏል። ይህ መመሪያ የወረደው የፋኖን ጥቃት ፍራቻ ነው ተብሏል። በዚህ ምክንያት አመራሩም ሆነ የአመራሩ ቤተሰቦች የህዝብ ትራንስፖርቶችን እንዲጠቀሙ በሁሉም የአማራ ክልል አካባቢዎች መመሪያ ወርዷል ተብሏል።
▪በሰሜን ሸዋ ዞን
#በረኸት ወረዳ መተህብላ ከተማ ትላንት የጀመረው ውጊያ ዛሬም እንደቀጠለ ነው። ከተማ ውስጥ ምንም አይነት እንቅስቃሴ የለም።
▪በምዕራብ ጎጃም ዞን
#በቁጭ ከተማ በነበረው ውጊያ የጥላት ኃይል ሁለት መኪና አስከሬኑን ጭኖ ወደ ቡሬ የሸሸ ቢሆንም ዛሬ ኃይሉን አሰባስቦ ከቡሬ ወደ ቁጭ እያንቀሳቀሰ ይገኛል። ትላንት ከቁጭ ወደ ቡሬ ሲሸሽ ቡሬ ከተማ ሁለት ቦታዎች ላይ በደረሰበት የደፈጣ ጥቃት ሰራዊቱ ላይ ጉዳት የደረሰ ሲሆን ተሽከርካሪዎችም የመገልበጥ አደጋ ደርሶ ነበር ተብሏል። አብዛኛው የከተማዋ ህዝብ (ሴት፣ህፃናትና አዛውኝቶች) ከተማዋን ለቆ ሸሽቷል። ቁጭ ከተማ አሁን ስልክ ተቋርጧል።
▪ምዕራብ ጎጃም ዞን ጅጋ ከተማ ውጥረት ነግሷል። ውጥረቱ የነገሰው ከደንበጫ እና ከፍኖተሰላም አቅጣጫ በርካታ ብረት ለበስ ተሽከርካሪዎች ወደ ከተማዋ መግባታቸውን ተከትሎ ነው። በርካታ የአካባቢው ነዋሪዎች ከተማዋን ለቀው እየሸሹ ነው።
▪አዲስአበባ ከተማን ከረፋዱ 5:30 ሰዓት ጀምሮ የጦር በጀት ዝቅ ብለው ከተማዋን እየዞሩ ናቸው። የጦር ጀቶቹ ቅኝት ምናልባት ለሀሙሱ ወታደራዊ ትርዒት ልምምድ ሳይሆን እንደማይቀር ከነዋሪዎች ያገኘየው መረጃ ያመላክታል። በርካታ ቤቶችና የንግድ ተቋማት እየተሰበሩ በመከላከያ ሰራዊቱ እንዲዘረፉ ተደርጓል።
▪አዴት ከተማ የፀደይ ባንክ ጥበቃ የነበሩት አቶ ኢብራሄም የሚባሉ ሰው “መሳሪያ ታጥቀሀል” በሚል በመከላከያ መረሸናቸው ከአካባቢው ያገኘየው መረጃ ያመላክታል። የሚገርመው ልጃቸው በአማራ ክልሉ ግዳጅ ላይ ያለ የመከላከያ ሰራዊት መኮነን ሲሆን አባቱን የሚሰራበት ተቋም ገሎበታል ተብሏል። አሁንም መከላከያ በሞሶቦ ፋብሪካ ውስጥ ካምፕ አድርጎ ተቀምጧል።
ለትኩስ መረጃዎችን የቴሌግራም ገፃችንን ይመልከቱ!👇
https://t.me/GionamharaПоказати повністю ...