በመቻል ስፖርት ክለብ ዋና አዘጋጅነት ፤ በኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን እና በድሬዳዋ ስፖርት ኮሚሽን አስተባባሪነት ከውጪ በመጡ የካፍ እና ፊፋ ኢንስትራክተሮች አማካኝነት ለግብ ጠባቂዎች አሰልጣኞች የተዘጋጀው ስልጠና በዛሬው ዕለት በድሬዳዋ ከተማ በኒው ሌቭል ሆቴል ተጀምሯል።
በዕለቱ የመክፈቻ መርሐግብር ላይ የመቻል ስፖርት ክለብ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ጄኔራል ኑር ሙዘይር ፣ የመቻል ስፖርት ክለብ የቦርድ ሰብሳቢ ዶ/ር ሰይፉ ፣ የሊግ ካምፓኒው ተወካይ አቶ ልዑል ፣ የካፍ ኤሊት ኢንስትራክተር አብርሃም መብራቱ ፣ የድሬዳዋ ከተማ ስፖርት ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር አቶ ኢብሳ ዱሪ እና የድሬዳዋ ከተማ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ተወካዩ አቶ ጉሌድ በክብር እንግድነት ተገኝተዋል።
በዕለቱ የመክፈቻ ፕሮግራም ንግግር ያደረጉት የመቻል ስፖርት ክለብ ተወካዮች “መቻል ይህን ስልጠና ያዘጋጀው ራሱ ተጠቅሞ እንደ ሀገር ሙያተኞችን ለመጥቀም" እንደሆነ እና የሚነሳውን የግብ ጠባቂዎች አቅም የማሳደግ ውስንነትን ለመቅረፍ በማለም ስልጠናው መዘጋጀቱን ገልፀው ስልጠናው በግብ ጠባቂዎች ይጀምር እንጂ በቀጣይነት በሌሎችም ዘርፎች እንደሚቀጥል አንስተው በሚኖራቸው ቆይታም ውጤታማ ስልጠና እንደሚሆን ምኞታቸውን ገልፀዋል።
የግብ ጠባቂዎች አሰልጣኞችን በመወከል ንግግር ያደረጉት ባለሙያ ሲናገሩ እንዲህ ያሉ ስልጠናዎችን መውሰድ ጠቀሜታው የጎላ እንደሆነ እና እንዲህ ያሉ ስልጠናን ከወሰዱ እጅግ ዓመታት ያስቆጠረ በመሆኑ "በቀጣይ ተከታታይ ስልጠና እንድናገኝ ዕገዛ እንፈልጋለን ራሳችንን ማሳደግ እንፈልጋለን ብለዋል።”
ለተከታታይ ስድስት ቀናት የሚቆየው ይህ ስልጠና መስከረም አስራ ስምንት የሚጠናቀቅ ይሆናል።
Ko'proq ko'rsatish ...