...┏━┅┅┄┄⟞ 😞 ⟝┄┄┉┉━┓...
".
#ሕያው_ነፍስ ".
ፀሀፊ | አብድልቃድር ኑር
...┗━┅┅┄┄⟞ 😔 ⟝┄┄┉┉━┛...
.┏─━─━─━∞🍂∞━─━─━─┓.
. በ
@tibebislam_nw የተዘጋጀ .
🍂. ልብ አንጠልጣይ ታሪክ.🍂
.┗─━─━─━∞🍂∞━─━─━─┛.
.┏━━━━ • 🥀 • ━━━━┓.
#ክፍል_አስራ_ዘጠኝ [◦⓳◦]
.┗━━━━ • 🥀 • ━━━━┛.
<በእንቅርት ላይ. .>
...
አንድ ሳምንት ደቂቃን መስሎ አለፈ፣ ዛሬ ዛሬን መስሎ ትናንት ሆነ።
ሰሚር አፈር ከዋጠው 5 ወር ሞላ፣ ከውሸተኛው አለም ለቆ ከወጣ ወራቶች በራሪ ሆኑ።
ባባና ማሒርም ሕይወት ያለዉ በድን ከሆኑ እነሆ አንድ አመት ከወራቶች ተቆጠሩ።
አንዳንድ ጊዜ ሕይወት እንደ ማዕበል ነው፤ በሰላም ይሄዱ የነበሩ ነገሮች ልክ የተመካከሩ ይመስል በአንድ ላይ ይናጋሉ፣ የሁኔታዎች አልሳካ ማለት፣ ድንገተኛ ወጪዎች፣ የገንዘብ እጥረት፣ የጉዳዮች መጥመም፣ ድንገተኛ ሞት፤ የሰዎች ክህደት፣ ስጋትን የሚፈጥሩ ሁኔታዎች መከሰት፣ የጤንነት መቃወስ የሚጠቁሙ ምልክቶች ልክ እንደ ማዕበል በአንድ ላይ ይመጣሉ፡፡
.
.
.
.
..
በወራቶች ልዩነት ባባም ሰሚርን ተከትሎ ሔደ፣ የልጁን እድል ወስዶ ያለምንም እረፍት እንዲሁ ሔዶ እሱም ቀረብን። አንድ እንኳን ቃል ሳይሰጠን እሱም እንደሰሚር አያገባኝም የራሳቹ ጉዳይ ያለ ይመስል ሐዘናችንን ባልሰማ አለፎ ሄደ፤
<በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ> እንዲሉ በሰሚር ሐዘን የልባችን ሕመምና ቁስል ሳይሽር ባባ አመረቀዘብን፤ እሱ መጥቶ በሱ እንረፍ ስንል አላህ ሳይፈቅድ የሱንም ሩሕ እንዲወጣ ፈለገ። የቤቶች ምሰሶ ባንዴ ተናዱ፣ ሰሚር ቤተሰቦቼ እያለ ባባም ቤተሰቤ እያለ ሁለቱም በቅፅበታት የጎማ እራት ሆነው አረፉት።
የሰሚር ቅፅበታዊ ሞት በመሆኑ ለቃሎቹና ማለት ስለፈለገው ነገር እድሉን አላገኘም፣ እንዲህ እንዲያ ብሎ የተናዘዘው አንድም ነገር የለም፤ ያ ነገር ቤተሰቤን አንገብግቦታል፣መመለስ የማይቻል ሆኖ አሳረረን፣ቃላትና አንደበትን ዘግቶ የማይወራ ቁስልን ፈጠረብን፣ ቢያንስ የመጨረሻ ቃሉንና ንግግሩን በሰማን ብለን ተመኘን፣ ከአንደበቱ የሚወጡት እያንዳንዷ ቃላቶችን መስማት ፈለግን፣ ድምፁን አልፎም ስስ ቁጣውን ናፈቅን ግን በጭራሽ የማይቻል ነገር ነውና እንዲሁ በሕይወት ያሉ ሟቾች እንደሆንን ተቀበልን።
ስለባባ ሞት ምንም ማለት አልችልም በቃ ከትልቅ አፋፍ ላይ የተወረወሩ ቤተሰቦች ነው የሆንነው፤ ግን አንድ ነገር ትዝ ይለኛል፣ አእምሮዬ ውስጥ ተቀርፆ የተቀመጠ አንድ ትዉስታ አለ፣ መቼም የማይወጣ አንድ ነገር አለ፤ ላውጣው ብል እንኳን የማልችለውና መቃብሬ ድረስ አብሮኝ የሚወርድ አንድ የማልረሳው ትውስታ አለ። ባባ ወደአኼራ የመሔጃው ቀን የደረሰ ሰሞን እንዲሁ በትንሹ ነቅቶ ያወራ ነበር እናም ማውራት ሲያቅተዉና አፉ ሲተሳሰር በአይኑ እንባ ነበር የሚገልፅልን፣ ትንሽ መለስ ሲል ያወራናል እናም አብሽር አለን <<ምንም አትዘኑ ምንም እንዳልተፈጠረ ለማስመሰል ቢከብድም ከባድ ጊዜ ለኛ አዲስ አይደለም፣ግን ከዚህ በኋላም ፈተና እናንተ ላይ ብርቱ ነው፣ያን በጥበብ የማለፍ ግዴታ አለባቹ ከስራችን የሚመጡ ብዙ የኛ ዘሮች ይኖራሉ፣ዛሬ በእኔ መሞት የሐዘን ድንኳን ቢጣልም ነገ ደግሞ የደስታ ድንኳን ይጣላል፣ዛሬ እኔ ብሰናበትም ነገ አዲስ ልጅ ሰላምታ ሰጥቶ ይመጣል፣ዛሬ በኔ ሐዘን አይናቹ ቢያነባም አላህ ብሎ ነገ የደስታን እንባ ታነባላቹ። ከችግር በኋላ ድሎት አለ ተብለንም የለ ይህ ቀን ትዉስታ ሆኖ የሚያልፍበትና ያ ቀን ብላቹ የምታወሱበት ቀን ይመጣል። ይህን ቀን ትናንት የምትሉት ነገ ይሆናል፣ባባ ወይም ሰሚር ብላቹ አንዲት ዘለላ እንባን እንድታነቡ አልፈልግም አልያ ግን አላህ ምስክሬ ነው አዝንባቹዋለው። ሞት ሐቅ ያለና ለማንም የማይቀር ነገር ነው ሞት ለመልዕክተኛውም አልቀረላቸውምና ይህን ክስተት አማና አታክብዱት!። ሁሉንም ነገር በስርዐቱ እንዲሁም ሐዘናችሁን በልክ አድርጉት፣ባለፉ ትውስታዎችም በጭራሽ ራሳችሁን እንዳታሳዝኑ፣እኔ ከእናንተ አልተለየሁም አለሁ ያለሁትም በልባቹና በዱአቹ ውስጥ ነው። ነገ በጀነቱ አላህ ይሰበስበን ዘንድ ጠንካራ ሁኑ፣ይህ ለኛ ገና መለያየት አይደለም እውነተኛ መለያየት ማለት የጀነትና የጀሐነም ተብለን የተለያየን ቀን ነው፣ያ እንዳይሆን የናንተ ትእግስት ያስፈልጋል፣ሁሌም እንደ ድሮአችን ነገሮችን በሶብር አሳልፉ። ትዝ ባልናችሁ ሰአት ከዱአ ዉጪ ምንም አታድርጉ>> ብሎን ባባ ላይ ጣዕረ ሞት መጣ፤ አይኖቹ ሊከደኑ፣ምላሶቹ ተሳስረው ከአንደበቱ ሚወጡት ቃላቶች ሊገቱ ሰአቱ ተቆረጠ፤ ዱንያ ላይ የተሰጠው የቆይታ ጊዜ ዛሬና አሁን ሆኖ ከች አለ፤ የሆስፒታሉ ክፍል በሐዘን ሲቃ አስተጋባ፣ የአይኖቻችን እንባ ሳይደርቁ ሌላ እንባ ያዘሉ አይኖች ሆነው መጡ።
ባባ ሰከራተል መውት ላይ መሆኑን ያወቅኩት ለኔ በኔ ደረጃ የመጀመሪያዬ ነበር፤ ያን እውነታ ባውቀውም ግን ባባ ሊሔድ እንደሆነ ሳስብ ውስጤ ተበጠበጠ፣ ከራሴ ጋር አይ አይሆንም እያልኩ ከሱ ጋር አወራለሁ፣ አይኖቹ ማየት ተስኗቸው ተከድነው እና ልሳኖቹ ተዘግተው ባባ እያልኩ እንደማይሰማኝ በመጠራጠር ባባ በአንደበትህ እንኳን ባይሆን በልብህ ሸሐዳን በል እያልኩት ላይመለስ ጥሎኝ ተሰናበተ።
⇊⇊⇊⇊⇊⇊⇊⇊⇊⇊⇊⇊⇊⇊⇊
.┏━━━━ • 🍂 • ━━━━┓.
#ክፍል_ሃያ [°⓴°] ይቀጥላል
.┗━━━━ • 🍂 • ━━━━┛.
ቻናላችንን ለውዳጅ ዘመዶ ሼር በማድረግ ስራዎቻችንን ያበረታቱ። ስለምትከታተሉን ከልብ እናመሰግናለን!
↴↴↴↴↴↴↴↴↴↴↴↴↴↴↴↴↴↴↴↴↴↴↴
╔╦══• •😞•🍂•😔 • •══╦╗
@tibebislam_nw
🍁
@tibebislam_nw 🍁
╚╩══• •😞•🍂•😔 • •══╩╝
.↴↴↴↴↴↴↴↴↴↴↴↴↴↴↴↴.
የኛን ግሩፕ ለመቀላቀል👇
.
@tibeb_Group .
የ ዩቲዩብ ቻናላችንን 👇👇ሰብስክራይብ ያድርጉ
https://www.youtube.com/channel/UCDcX9sbuS4bhYuv3mfygPEg
↴↴↴↴↴↴↴↴↴↴↴↴↴↴↴↴↴↴↴↴↴↴↴↴↴↴↴↴↴↴↴
ይቀላቀሉን⇊ ይቀላቀሉን⇊
@tibebislam_nw @tibebislam_nw
. ↴↴↴↴↴↴↴↴↴↴↴↴↴↴↴.
For any comment👇
@tibeb_botKo'proq ko'rsatish ...