ያማል. . .!
:
እንደ ጎርፍ የሚፈሰው የንፁሀኖች ደም ፡ የእናቶች እምባ፣ የህፃናት ለቅሶ ያማል!
የጭካኔ ጥግ ተድበስብሶ ሲያልፍ..፣ ፍትህ እንደ ሰማይ ሲርቅ ፡ ተበዳይ ሲያነባ እምባው በግፍ እጅ ለማድረቅ ሲጣር ሲታይ ያማል።
ሀዘንተኛው ከህመሙ ብዛት ጠብታን ማንባት ሲሳነው፡ ሟች ሬሳው ሲንገላታ . .ለህሊና ሚከብድ ጥልቅ ህመም አለ።
:
ለህፃናትና ለእናቶች እንጥፍጣፊ እዝነት ጠፍቶ ያለ ምንም ምክንያት ህይወታቸውን ሲነጠቁ ማየት ልብ ስር ዘልቆ ያደማል።
:
ስቃይን እያዩ መሰቃየት፡ የስቃይና መከራ ሀሩር ላይ ተሰጥቶ ነገን ማለም ያማል።
ሀዘን ልባችን ውስጥ ጠቅልሎ ገብቶ ፈገግ ለማለት ምክንያት ማጣት ፡ ከመኖርስ ምን ላገኝ? ምንስ ላስገኝ? ከመሞቴስ ምንን ላጣ? ብሎ ከራስ ጋር ሙግት መግጠም ይኖራል።
:
ምንም እንኳ. . .
ህመም ዙሪያችንን ቢከበንም ፡ ከድካምና ሁከት መሸሸግያ መስጂዶቻችንን ወደ ፍርስራሽነት ቢቀይሩትም! ዝም ቢሉት ማይሄድ ቢያወሩት ማይሽር ጠባሳን በልባችን ብንሸከምም!
ወህኒያችን በሆነው አለም ላይ ለሚደርስብን ግፍና መከራ ፀንተን እየታገልን ፣ እየታገስን ልባችንን ወደ ልብን ጠጋኙ ፡ ግፈኞችን ብርቱ አያያዝን ያዥ ወደሆነው አላህ... አቅመ ቢስነታችን አውጀን እንዋደቅ. . . ብርታት እንዲሆነን እንማፀነው። አላህን የያዘ ወድቆ አይወድቅም።
:
#ለጀባሩ_ድምፃችንን_እናሰማ! በእምባ እናውጋው። ተሰባስበን እየዘነበ ላለው በላዕ ዱዐ እናድርግ። ሰደቃ እናብዛ።
•[ አብዱ ሩሚ ]•
Ko'proq ko'rsatish ...