አንተ ብቻ ነህ!
፨፨፨/////፨፨፨
አዎ! ቀንህ ላይ የምትወስነው፣ ምስጋናን የምታስቀድመው፣ ተስፋን የምትሰንቀው፣ ህይወትህን በሙላትና በትጋት የምትኖረው፣ ከቀደመው ታሪክህ የምትማረው፣ ለመጪው ይበልጥ የምትጠነክረው፣ እራስህ ላይ የምትሰለጥነው አንተ ብቻ ነህ። የሚረብሹ ነገሮች ቢኖሩም የማትረበሸው፣ ተስፋ አስቆራጭ ተግባራትን ብትመለከትም ተስፋ የማትቆርጠው፣ ቢደክምህም የምትበረታም፣ ቢደብርህም የምትነቃቃው አንተ ነህ። በየእለቱ ለምታያቸው አዳዲስ ቀናቶች፣ አዳዲስ እድሎች ከምንም በላይ ማመስገንና በእነርሱ መደሰት ይገባሃል። በረከቶችህን ለመቁጠር ምን ነገር አድርገሃል? ፀጋህን ለማብዛት፣ ስጦታህን ለመጨመርስ የትኛውን መንገድ ተከትለሃል? አንሶኛል፤ አይበቃኝም፤ እኔ ተጎድቼያለሁ ጨምርልኝ? ወይስ ባለኝ ደስተኛ ነኝ፤ ያለኝ ይበቃኛል፤ የጎደለኝን አንተው አይተህ ሙላልኝ?
አዎ! ጀግናዬ..!
አንተ ብቻ ነህ! ምንም እንኳን አሁን ባለህበት ሁኔታ ደስታና እርካታ ባይሰማህ ከዚህ ለመውጣት ካንተ ውጪ ሊረዳህ የሚችል አካል የለም። እግዚአብሔርም የሚረዳህ፣ አምላካህም የሚያግዝህ በሃይል አምነህ፣ ከልብህ ተማምነህበት፣ እራስህን ሰጥተህ፣ ወደርሱ ቀርበህ መሻትህን ስታስረዳው፣ ጭንቀትህን ስታካፍለውና ምላሹን በተስፋ ስትጠብቅ ነው። ሃላፊነት የሚሰማህ ከሆነ በቅድሚያ አሁን ስላለህበት ሁኔታ ማስተዋልና ማጤን ጀምር፤ የት እንዳለህ ጠንቅቀህ እወቅ፤ በረከቶችህ ምን እንደሆኑ፣ ምን እንደተሰጠህ፣ ከምን ላይ ምንን ማግኘት እንደምትችል ተገንዘብ። በረከቶችህን እንድትመለከት አይንህን ይገልጡልህ ይሆናል እንጂ ማንም ይህን አለህ፣ ያንን አለህ የሚልህ ሰው እንደሌለ እወቅ።
አዎ! በሚታዩህ ብዙ ችግሮችና ክፍተቶች ልትሞላ ትችላል፣ ዘወትር ደካማ ጎንህ እየተገለጠም ያስቸግርህ ይሆናል። ነገር ግን የእይታህን አቅጣጫ ማስተካከል ከቻልክ፣ ማድረግ የሚገባህን ካስተዋልክ፣ ፍላጎትህን ከተረዳህ ህይወትህን ለማስተካከል በምታሳየው ቆራጥነት ካለህበት የዝቅታ ስፍራ ተነስተህ ከከፍታው መድረስ ትችላለህ፤ ካለህበት ክፍተት ተነስተህ የብዙዎችን ክፍተት መሙላት ትችላለህ፤ ከእራስህ የግል ችግር በመነሳት ለብዙዎች ችግር መፍትሔ መሆን ትችላለህ። ቆም ብለህ እራስህን ተመልከት። "አይዞህ፣ ትችላለህ፣ በርታ!" የሚልህን መስማት ያዋጣሃል ወይስ በችግር ላይ ችግርን እየደራረበ የሚተነትንልህን መስማት? ምርጫው ያንተና ያንተ ብቻ ነውና ለእራስህ ህይወት ሃላፊነት በመውሰድ ለእራስህ ተገን፣ ለእራስህ ድጋፍ መሆኑን እወቅበት።
ግሩም ድንቅ ቀን ይሁንልን!
✍
@abrish_9
Share
@JESUSlovingly142عرض المزيد ...