Best analytics service

Add your telegram channel for

  • get advanced analytics
  • get more advertisers
  • find out the gender of subscriber
Channel location and language

audience statistics Zemedkun Bekele (ዘመዴ)

"ይህ የቴሌግራም ቻናሌ ግንቦት1/2011ዓም የተከፈተ ነው። የእኔን የስልክ ወጪ ጨምሮ አገልግሎቴን መደገፍ የምትፈቅዱ ጓደኞቼ በ 👉🏿  https://donorbox.org/zemedemedia  እና 👉🏿  https://www.paypal.com/paypalme/ZemedkunB  በኩል ማገዝ ትችላላችሁ። በተረፈ ለቤተ ክርስቲያኔና ለኢትዮጵያ ሀገሬ የሚጠቅመውን ሁሉ አበረክት ዘንድ አብዝታችሁ ጸልዩልኝ። 
Show more
398 614+127
~116 042
~15
33.62%
Telegram general rating
Globally
1 990place
of 78 777
3place
of 396
In category
107place
of 2 793

Subscribers gender

Find out how many male and female subscibers you have on the channel.
?%
?%

Audience language

Find out the distribution of channel subscribers by language
Russian?%English?%Arabic?%
Subscribers count
ChartTable
D
W
M
Y
help

Data loading is in progress

User lifetime on the channel

Find out how long subscribers stay on the channel.
Up to a week?%Old Timers?%Up to a month?%
Subscribers gain
ChartTable
D
W
M
Y
help

Data loading is in progress

Since the beginning of the war, more than 2000 civilians have been killed by Russian missiles, according to official data. Help us protect Ukrainians from missiles - provide max military assisstance to Ukraine #Ukraine. #StandWithUkraine
በፋኖ ስም… "…አገዛዙ አሰልጥኖ ይላካቸው፣ ወይ ብአዴን ግንቦት 7 እና ወያኔም ያሰማሯቸው ብቻ በፋኖ ስም የተከበረውን፣ የፋኖ ትግል የሚያዋርዱ፣ የተቀደሰውን የፋኖን ትግል የሚያራክሱ ሰርጎ ገብ ፌካፌካም የቁጩ ዘራፊ ፋኖ አሰዳቢ ሌቦችን እንዲህ መንጥሮ በማውጣት እርምጃ መውሰድ ለትግሉ እጅግ ጠቃሚ ነው። "…እነዚህን ብቻ ሳይሆን ቤተ ሰቦቻቸውን አዲስ አበባ ልከው፣ ቤትም ተከራይተውላቸው በዐማራ ፋኖ ስም ዐማራ እያገቱ በሚልዮን ብር የሚቀበሉ፣ የሚደበድቡ፣ ዐማራውን አማርረው ፋኖ መጣልኝ ሳይሆን ፋኖ መጣብኝ ብሎ ፋኖን እንደ ስጋት ምንጭ እንዲያይ እያደረጉ ያሉ፣ ወያኔ ማሪኝ፣ ብአዴን ይቅር በለኝ የሚያሰኙ አለሌ የማፍያ ጠባይ ያላቸውንም ፋኖ አሰዳቢዎች በድፍረት መጋፈጥ ያስፈልጋል። "…የዐማራ ትግል የህልውና ትግል ነው። በዐማራ ትግል ውስጥ ተደብቆ አረመኔያዊ ተግባር መፈጸም የከፋ ወንጀልም ነው። የፋኖ ግምገማ መጀመር አለበት። የዐማራ ገበሬ መደመጥ አለበት። በነጩ ሸማ ላይ ያረፉ ነጠብጣብ ቆሻሾች የዐማራን ትግል ማቆሸሽ የለባቸውም። "…በሸኔና በወያኔ የተማረረውን ሕዝብ በዐማራ ፋኖ ስም ማማረር ይቅር የማያስብል ወንጀል ተደርጎ መፈረጅ አለበት። • በለው…!
Show more ...

file

8 547
12
"…እዚህ አዲስ አበባ አፍንጫ ስር የሚገኘው የዐማራ ፋኖ የሸዋ ጠቅላይ ዕዝ ይወጉት ዘንድ አቢይ አህመድ የላካቸውን እና ከሞት የተረፉትን የፌደራል ፖሊስ አባላት የተሃድሶ ሥልጠና እየሰጣቸው ነው። • ትገባለህ መውጣት ኢንጂሩ። ቤርሙዳ ነው ስልህ… "…ወንድ ከወንድ እንዲህ ገጥሞ ሲሸናነፍ እኮ በጣም ደስ ይላል። የእንጭቅ ልጅ ወንድ መግጠም ትቶ በድሮን ገበያተኛ እና ትምህርት ቤት ይደበድባል። • ብልቅጥና መውደቁ፣ መደምሰሱ እንደሁ አይቀር… ማርያምን እውነቴን ነው።

file

13 805
21
"…በትግራይ ምድር እንኳን በአምስት መቶኛው ክፍለ ዘመን የነበረው ማኅሌታይ ቅዱስ ያሬድን የመሰለ ጻድቅ ይቅርና በ1977 ም በራብ በጠኔው አስከፊ ዘመን እንደዚህ አጽሙ የገጠጠ ትግሬም አልነበረም። "…ደብረ ጽዮን እንኳ ሥጋ ቅብ መባሉ ቀርቶለት ኡሙንዱኖኢሹ ዱንቡሽቡሽ ቦንቦሊኖ በመሰለበት በዚህ ዘመን ማኅሌታይ ቅዱስ ያሬድ ነው ብለው ዛሬ በአክሱም አደባባይ አንድ ገመምተኛ ቁስለኛ ታጋይ የላብራቶሪ አፅምም የመሰ ነገር አምጥቶ በአንድ ነጥብ ምናምን ሚልዮን ብር ወጪ ቅዱስ ያሬድ ነው ብሎ እዩልኝ ማለት ፈጽሞ ነውር ነው። "…ይኸውልህ በኢትዮጵያ በጀት መንቀሳቀስና በራስ አቅም መንቀሳቀስ ልዩነቱ እዚህ ላይ ነው። ሁልጊዜ ከኢትዮጵያ ሲለዩ እጅም ዕውቀትም ያጥራል። ኮቴ መናና፣ አቅለቢስ፣ ውቃቢ የራቀህ ነው የምትሆነው። ይሄ በኤርትራም የታየ ነገር ነው። "…ለማንኛውም ገንዘብም፣ ዕውቀትም ከሌለህ በአደባባይ እንዲህ ከመዋረድ፣ ለአህዛብም ሁሉ መሳቂያ መሳለቂያ ከመሆን ቢቀርስ? ያው ልትመርቁት ወጥታችሁ ከሕዝቡ በተነሣ ተቃውሞ ሃውልቱን አፍርሱና ሌላ ታጋይ ያልመሰለ ጻድቅ ካህን ሥሩ ተባላችሁ አይደል? አባ ሠረቀ ግን ፈጣሪ ይይልህ። በአንተ ቤት… ብቻ ይቅር… ምን ክፉ አናገረኝ። • የጥዑመ ልሳን፣ የካህነ ስብሐት የሊቁ ማኅሌታይ የቅዱስ ያሬድ በረከቱ ይደርብን። አሜን።
Show more ...

file

13 923
1
"…ለሀበሻ እንኳ ችግር የለውም። ነገር ግን ይሄን የአሜሪካ አምባሳደር የማሲንጋን ፎቶ የሀገሩ የአማሪካ ሰዎች፣ ጓደኞቹ፣ ቤተሰቦቹ ይሄን ፎቶ ቢያዩ ሊሰማቸው የሚችለውን ስሜት አስባችሁታልን…?
25 910
7
መልካም… "…አሁን ደግሞ እስቲ የእናንተን ብሉኝ ብሉኝ የሚል የሚያስጎመዠውን የበሰለ አስተያየት እንኮምኩም። • ጀምሩ እስቲ…!
36 469
3
👆ከላይኛው የቀጠለ…✍✍✍ … ከቀና አስተሳሰብ ጎን ለጎን በጥላቻ አንዱ አንዱን ዘርጥጦ ለመጣል፣ አንዱ አንዱ ላይ ሽብልቅ ለመክተት የሚደረግ የቴክቶክም ሆነ የዙም ውይይት ለማንም አይጠቅምም። በዚህ በኩል ገና ከአሁኑ እገሌ ወደፊት ከመጣ የእነ እገሌ ቡድን ሥልጣን ከያዘ ለእኛ ለእነ እገሌዎች አደገኛ ነው፣ ስለዚህ እነ እገሌን እና እገሌን ከወዲሁ ማግለል ይገባናል የሚል ንትርክ መፍጠር በፍጹም ዐማራ ነኝ ብሎ ለዐማራ ከሚታገል ድርጅትም ሆነ ግለሰብ የሚጠበቅ አይደለም። በአስቸኳይ ሊታረም ይገባዋል። "…የፋኖ ትግል በነፍጥ ታጅቦ ከተጀመረ ገና አንድ ዓመቱ ነው። በዚህ አንድ ዓመት ውስጥ የተፈጠረውን የፋኖ ትግል የአካሄድ ትግል ስህተት ያለበትን አካሄድ  በግምገማ ገምግሞ ማስተካከያ ሰጥቶ፣ ብዙሃኑ ወደ ትግሉ የመጡቱ ዐማራ ቢሆኑም የተለያየ ርዕዮተ ዓለም ከሚከተሉ የፖለቲካ ግሩፖች የመጡ ጭምር መሆናቸው ታውቆ ወደ አንድ ወጥ አስተሳሰብ ለማምጣት ከወዲሁ መጣር ይገባል። ሽፍታ የነበሩና በዚያው የህልውና ትግሉን የተቀላቀሉ አሉ። እነዚህን ከጫካቸው፣ ከሰፈራቸውና ከመንደራቸው የወጣ አስተሳሰብ እንዲኖራቸውና ሀገራዊ አስተሳሰብ እንዲላበሱ ማድረግም ይገባል። ከአብን የመጡ የፋኖ መሪዎች አሉ። ከብአዴን የመጡ የዐማራ ፋኖ መሪዎች አሉ። ከመኢአድ የመጡም አሉ። ከአርበኞች ግንቦት 7 የመጡ የፋኖ አመራሮች እና ታጋዮች አሉ። ለኢዜማ ተወዳድረው ከምርጫው በኋላ የመጡ ፋኖን የተቀላቀሉ አሉ። በኢትዮጵያዊነት የሚታገሉ፣ መነሻዬ ዐማራ መድረሻዬም ዐማራ የሚሉ አሉ። መነሻዬ ዐማራ፣ መድረሻዬ ኢትዮጵያ የሚሉ አሉ። የግንባሩ ነኝ፣ የእዙ ነኝ፣ የፋፍዴን ነኝ የሚሉም አሉ። እነዚህን ሁሉ ወደ አንድ አስተሳሰብ ለማምጣት ድርድሩ፣ ፍትጊያው፣ ውይይቱ መፍጠን አለበት። ትግሉ ሳይቋረጥ ምክክሩ፣ ውይይቱ በስፋት መቀጠል አለበት። "…ደቡብ ወሎ ደርሶ የመጣ አንድ ሰው እንዲህ አለ። የፋኖ ታጋዮቹ ቀለባቸውን በለስ እና ቀጋ ለቅመው ሲበሉ ያያል። ጥቂቶችም ቆሎ እየበሉ ነበር። እናም ጠየቃቸው። ሜዳው ሙሉ የገበሬ ከብት ነው። ለምን ገበሬው እንዲረዳችሁ አታደርጉም? ለምን ይሄ ሁሉ ከብት እያለ እናንተ ትራባላችሁ? በማለት ሓሳብ ያቀርብላቸዋል። መለሱለታ። እኛ ወደ ትግል ሜዳ የወጣነው የዚህን ምስኪን ሕዝብ መከራ ለማስቀረት ነው። እናስ መከራውን ለማስወገድ ወጥተን ስናበቃ ከብቱን እየበላን መከራውን ልንጨምርበት አይገባም። ይህን ካደረግንማ ከትግሬ እና ከኦሮሞ ነፃ አውጪዎች በምን ተሻልን? አይሆንም፣ አናደርገውም እንዳሉት ሲናገር ሰምቻለሁ። የዐማራ ትግል በዚህ መልክ ጥራት ባለው ከፍ ባለ ሞራል እና ስብእና መመራቱ የሚጠበቅ ነው። "…ከዚህ በተጨማሪ ግን ዘግይተው አገዛዙ መውደቁ አይቀርም ብለው የዐማራ ፋኖን የተቀላቀሉ አንዳንድ የቀድሞ የአድማ ብተና አባላት፣ የሚሊሻ አባላት፣ የግምቦት 7 እና የኢዜማ፣ የአብንም አባላት ደርሰው መጥተው በፋኖ አመራር ላይ ከመሰየማቸው በአንድ አንድ አካባቢዎች በሕዝቡ ላይ እያፈጸሙ ያሉት ሰቆቃና ግፍ ህወሓትን የሚያስናፍቅ እንደሆነ ከሚደርሱኝ መረጃዎች እያየሁ ነው። የሸኔን መንገድ ተከትሎ ዐማራውን እያገቱ ሚልዮን ብር ክፈሉ ማለት እጅግ አስነዋሪ፣ አንገት ሰባሪ ድርጊትም ነው። ብአዴን በነበሩ ጊዜ ይታገሉአቸው የነበሩትን በአንድ ጊዜ የፋኖ አመራር በማድረግ መልሰው እነዚያኑ ብአዴን ሳሉ የሚያሳዱአቸው የፋኖ አለቆች አድርጎ መሾሙም ትክክል አይመጣም። የፋኖ አመራር ሆነው እነርሱ ቤተሰቦቻቸውን ክፉ እንዳያገኛቸው ወደ አዲስ አበባ ልከው ሲያበቁ ከሀገሩ መውጫ፣ መሸሻ የሌለውን ምስኪን የዐማራ ሕዝብ እንደ ሸኔ እያገቱ በረሀ ተቀምጠው ጮማ እየቆረጡ ዝንጥ ብሎ የማፍያ ኑሮ መኖር እጅግ አስነዋሪ ድርጊት ነው። ቆይቶም መዘዙ ከባድ ነው። "…እንዴት ሰው ከደሀ ገበሬ ላይ ብር ተቀብሎ አዲስ አበባ ለላካቸው ቤተሰቦቹ ከደሀ ገበሬው ላይ በእገታ የተቀበለውን ብር ለቤት ኪራይ፣ ለትምህርት ቤትና ለቀለብ እየላከ ለዐማራ ነው የምታገለው ይላል? አገዛዙ ዝረፉ ብሎ አሰልጥኖ የላካቸውን በፋኖ ስም የሚነግዱትን በተለያየ ጊዜ እውነተኛ ፋኖዎቹ እያጋለጡ በአደባባይ እየገረፉ ሲያዋርዷቸው ባየንበት ዓይናችን ፋኖ ነን ብለው በሚዲያ የሚቀርቡ፣ ሕዝቡም በፋኖነት አምኖ የተቀበላቸው የሚታወቁ የፋኖ አካላት ግን በእንደዚህ ዓይነት ነውር ውስጥ መግባታቸው እጅግ ፀያፍ ነገር ነው። ይሄ ነገር ከአሁኑ በእንጭጩ ካልተቀጨ በቀር ወደፊት የሚያመጣው አደጋ ከባድ ነው ብቻ ሳይሆን የከፋም ጭምር ነው። መቼም ተጨባጭና ዘግናኝ መረጃ ሳልይዝ እንደማላወራ ይታወቃል። "…ያም ሆነ ይህ የዐማራ ፋኖ ትግል ሃላል ነው። የዐማራ ትግል መቅደሱ ክፍት ነው። መንበሩን እያየህ በክብር፣ በፍርሃት የምትመለከተው ነው። ቆሻሻ ሰገራም በረገጥክበት ጫማህ ዘው ብለህ የምትቀላቀልበት አይደለም የዐማራ ትግል። ነጭ ሽንኩርት በልተህ አፍህን፣ ምላስህንም ሳትታጠብ ከነ ክርፋታም፣ ግማታም፣ ጥንባታም አፍህ ዘው ብለህ ገብተህ የምታግማማውም አይደለም የዐማራ ትግል። እጅህንም፣ መላ አካላትህንም ታጥበህ፣ ነጭ በነጭ ሸማህን ለብሰህ የምትገባበት ትግል ነው የዐማራው ትግል። ታጠብ አልኩህ። "…ከዚህ በፊት እንዳልኩት የትግሬና የኦሮሞ ነፃ አውጪዎች ትግል ጨለማ ነው። ጥቁር ነው። ጨለማና ጥቁር ደግሞ ነገሮችን ይሰውራል፣ ይሸሽጋል፣ ይደብቃል። ለዚህ ነው የትግሬ ነጻ አውጪዎች ሚልዮን ትግሬ አስፈጅተው ምንም እንዳልተነካባቸው አሁንም እየሳቁ የሚሽለጠለጡት። የኦሮሞውም እንደዚያው ነው። የዐማራ ትግል ግን ነጭ ወረቀት ነው። ፀአዳ ፏ ያለ ሃጫ በረዶ የመሰለ ትግል ነው። መንገደኛ ሁሉ ሲያየው ፐ ብሎ የሚያደንቀው። በዚህ ነጭ ፀአዳ ሃጫ በረዶ በመሰለ ትግል ላይ የፈለገ ዶክተር፣ ፕሮፌሰር፣ ኢንጂነር፣ ቄስም ሆነ ሼክ፣ ጋዜጠኛም ሆነ ኢንቬስተር፣ ወላ ያፈለገው ይሁን ትግሉን ቢቀላቀል መደበቅም፣ መሸሸግ አይችልም። እንደ ትግሬና ኦሮሞ በሀሰት ትርክት፣ በቀይ እና በጥቁር ከለር ውስጥ ለመደበቅ አይመችም። ነጭ ወረቀት ነው የዐማራ ትግል። ጥቁር ነጥብ ይዘህ ብትመጣበት ጎልጉሎ ያወጣሃል። ስህተትህ ነጥብ ቢያክልም አገልቶ ያወጣሃል። የዐማራ ትግል ቆሻሾችን አይደብቅም። መደበቅም የለበትም። • ድል ለዐማራ ፋኖ…! • ድል ለተገፋው ለዐማራ ሕዝብ…! • ድርጅቱ ዘመዴ ነኝ አሸበርቲው ከራየን ወንዝ ማዶ…!
Show more ...
37 511
7
"ርዕሰ አንቀጽ” "…በፕሪቶሪያው ውል ስምምነት መሠረት ህወሓት የአፍሪካ ኅብረት ታዛቢዎች ባሉበት ከከባድ እስከ ቀላል የጦር መሳሪያ ለሀገር መከላከያ ሠራዊት አስረከበች፣ ህወሓት ወደ 50 ሺ የሚጠጉ ወታደሮቿን ትጥቅ አስፈትታ ወደ ኅብረተሰቡ ቀላቀለች ብላ ብላ የሚል እንኩቶ ዜና በአማርኛ ለቅቀው አየር ምድሩን ሲያጨናንቁ ይከርሙና ድንገት ከትግሬ ዳያስጶራ ለምን? የሚል ጥያቄ በትግርኛ ቋንቋ ሲዥጎደጎድባቸው ደግሞ ያንኑ ዜና የሠሩት እነ ጌታቸው ረዳ፣ እነ ጻድቃንና ደብረጽዮን ገጭ ብለው ይመጡና በትግርኛ ቋንቋቸው "የምንፈታው ትጥቅ፣ የምናስረክበው መሣርያ፣ የምንበትነው ሠራዊት የለም" ብለው እርፍ ይላሉ። ወዲያው ደግሞ የሆነ ቀን ለገሰ ቱሉ ይወጣና ህወሓት የፕሪቶሪያውን ስምምነት እየጣሰ ነው ሲል ጌታቸው ረዳ ደግሞ ብቅ ብሎ ከፌደራል መንግሥቱ ጋር በቀና ልብ አብረን እየሠራን ነው። መሳሪያም አስረክበናል፣ መሬታችንን ልንረከብ ነው ብሎ መግለጫ ይሰጣል። "…በመሃል ቱጂው የአረጋ ከበደ የብላኔ የብአዴን አገዛዝ ደግሞ ይመጣና "ህወሓትን ጠብ አጫሪ፣ ፀረ ሰላም፣ ወራሪ" አድርጎ ይከስሳታል፣ ህወሓት ራያን የወረረችው እኛ ከፋኖ ጋር እየተዋጋን ስለሆነ ነው ብሎ መግለጫም ይሰጣል። ለዚህ መግለጫ ህወሓትም መልሶ ሌላ ድራማ ይሠራል። ብልፅግናም እንደዚሁ፣ እንግዲህ ይህ አስቀድሞ መሳሪያ አስረከበ የተባለው ዜና ነው አሁን ደግሞ ከትናንት ጀምሮ እንደ አዲስ ህወሓት መሳሪያ ሊያስረክብ ነው፣ ሠራዊቱን ሊበትን ነው የሚል ወሬ በዜና መልክ ቀሽሮ እየቀረበ ያለው። በእኔ ግምገማ የተፈታ ትጥቅ፣ ያስረከቡት መሣሪያ፣ የበተኑት ሠራዊትም የለም። አለቀ። "…ከልምድ እንደታየው ህውሓት ዐማራን ለመውረር ሲያስብ መጀመሪያ ዐማራን የሚያጃጃል፣ የሚያዘገይ፣ የሚያደነዝዝ ዜና ይዞ ይወጣል። የትኩረት አቅጣጫን የሚሰርቅ፣ አስቀያሽ፣ ላቦሮ የሆነ ዜና ሠርቶ ያሠራጫል። ከዚያ ሕዝቤ በዚያ ዜና ላይ ሲነታረክ እርሱ በጓሮ በኩል ወረራውን ይፈጽማል። እንበልና እሺ መሣሪያ አስረከበ እንበል መሣሪያውን የሚያስረክበው ለማነው? ብልፅግናም ጠላቱ ነው። ለብልፅግና አብዶ ነው የሚያስረክበው? ደግሞስ የትስ ነው የሚያስረክበው? በጎረቤት ሀገር በሱዳን የእርስ በእርስ ጦርነት ላይ የትግሬን ጦር ለአማጽያኑ ልኮ የሚያዋጋ ድንበር ተሻጋሪ አሸባሪ ድርጅት፣ ያለ ጦርነት፣ የለውጊያ ህይወቱን መምራት የማይችል ድርጅት ለማን ብሎ ነው መሳሪያ የሚያስረክበው? "…ይልቅ ህወሓትና ኦሮሙማውን የሚያስማማቸው ነገር ሁለቱም በቅርቡ ሀገር የሚያስደርጋቸውን ህልም እያለሙ መሆኑ ላይ ብቻ ነው። በተለይ ትግራይ ሀገር የሚያሰኛትን መስፈርት በሙሉ ለማሟላት እየደከመች ነው። በተለይ ወልቃይትንና ራያን በጨበጣም፣ በጓዳ ውልና በሴራም፣ በሥራም በእጇ ካስገባች በኋላ ለመገንጠል እንደምትፈልግ ምሑራኖቿ በአደባባይ ወጥተው በቴሌቭዥን በይፋ እየተናገሩ ነው። ለዚህም ሲባል ኦሮሞም የሚፈልገው ካለ እናግዘው፣ እሱም እኛ የምንፈልገውን ያግዘን በማለት በዐማራ ርስትና በኢትዮጵያ ህልውና ላይ እየተደራደሩ ነው። አሁን እኮ እነ እስታሊን የፋኖ ቁጥር እለት ከእለት እየጨመረ ነው፣ የመከላከያ ሠራዊቱም በዐማራ ክልል እያለቀ ነው የሚል ዜና የሚሠሩት እኮ ዐማራን ለማጀገን ፈልገው የሚመስለው ዐማራ አይጠፋም። እንደዚያ የሚያስብ ዐማራ ካለ ተሳስቷል። እነ እስታሊን በፈረንሳይኛ እያሉ ያሉት "እናንተ የወልቃይትንና የራያን ጉዳይ በቶሎ አመቻቹልን። እኛም የቅዱስ ፓትርያርክነቱን ጉዳይ በቶሎ እንጨርስላችኋለን" ነው። ፈረንሳይኛው ይሄው ነው። "…አቢይ አሕመድም ተጨንቋል። አዎ ተጨንቋል። መንታ መንገድ ላይ ነው ቆሞ ያለው። ህወሓትን እንዳያምናት አምኖም ወልቃይትን እንዳያስረክበት ከዚያ በኋላ አይደለም አገዛዙ ራሱ ኦሮሙማው ያልቅለታል። ወልቃይትን ሙሉ በሙሉ እንዳያስረክባት ደግሞ የወልቃይትን ፖታሽ የሚፈልጉት ምዕራባውያን ወልቃይትን ለትግሬ ካላስረከበ ምንም ዓይነት ብድር፣ ፈረንካ፣ ዱዲ፣ ጢና አምስት ሳንቲም አንሰጥህም ብለው በዶላር ድርቅ መትተውታል። ወያኔ በጓሮ በር በነጮቹ እጁን እያስጠመዘዘችው ነው። ካልሆነ ዐማራ ተመልሶ መጥቶ ሥልጣን ላይ ከሚወጣና የሁለታችንም ጨፍልቀን የመግዛት ህልማችን ከሚያከትም ያለንን ኃይላችንን አንድ አድርገን፣ ዐማራን በሻሻ የማድረጉን ጉዳይ አብረን እንጨርስ እና በቶሎ እንስማማ። ወደ ሥራም እንግባ ነው እያሉ ያሉት። ኃይል ካነሰን ሸኔን እና ኦነግን በአየር አምጥተህ መቀሌ ታራግፋለህ ከዚያ አለቀ ነው የሚሉት። ጌታቸው ጉዲና አስቀድሞ አቢይ አህመድን ካልበላው ነው ይሄም የሚሆነው። ይሄን ቃሌን መዝግቡልኝ።                 "…ዐማራስ አሁን ምን እያደረገ ነው? አዎ ዐማራ በምድር ያለው ፋኖ ድምፁን አጥፍቶ እየሠራ ነው። በሥራው ውስጥ ሴራና ሸውክ የለም ማለት አይደለም። ድብን አድርጎ አለ። ግን እሱንም ቢሆን በኃይለኛው እየታገለ ለመፍታት እየሞከረ ነው። የምድሩ ፋኖ ከባድ የውስጥ ሽኩቻዎችን እየተጋፈጠ፣ ሌት ተቀን ያለመሰልቸት እየተመካከረ፣ እየተወያየም፣ በቶሎ የሚፈታውን ወዲያው እየፈታ፣ በጊዜ የማይፈታውን ደግሞ ያለመሰልቸት እያዋለ እያሰደረ እየተመካከረበት ነው። "…ፌክ ፋኖዎች ሕዝቡን እያማረሩት፣ ትግሉን ለመጥለፍ የብአዴንና የውጭ ኃይሎች ኢንቨስት ያደረጉባቸው ኃይሎች እየተሟሟቱበት እንደሆነም እያየን ነው። የዐማራ ፋኖን አሁን አሁን የተማረው ኃይል ማለትም ፕሮፌሰሮች፣ ዶክተሮች፣ ኢንጂነሮች፣ የፖለቲካ ጠበብቶች ሁሉ በረሀ ድረስ እየወረዱ በገፍ እየተቀላቀሏቸው ነው። ወታደራዊ ሥልጠናውም ደረጃው ከፍ ብሏል። የዐማራ አድማ ብተና፣ የዐማራ ሚሊሻ፣ የብአዴን ካድሬ፣ ባለ ሥልጣን የነበሩ ግለሰቦች ሁሉ ፋኖን እየተቀላቀሉት ነው። በዚህ ሁሉ ታዲያ ጥርጣሬ፣ ሙግት፣ ክርክሩ እየቀጠለ በመመካከርና በንግግር የሚጠሩ ጉዳዮቸረ እያጠሩ እየመጡ የተሻለ ቁመና ላይ ይደርሳሉ ተብሎም ይጠበቃል። አዎ ፋኖ ግምገማ የግድ ያስፈልገዋል። በቀጣይ መደረግ ስላለበት፣ ስላሳለፈውም ትግል ግምገማ ያስፈልገዋል። ግምገማ ግድ ነው። ደካማ ጎኑን አርሞ፣ ጠንካራ ጎኑን አጎልብቶ ወደፊት ለመስፈንጠር፣ ክፍተቱን ለመሙላት፣ ስህተቱን ለማረም ግምገማ ግድ ነው። "…በዚያው ልክ ደግሞ በአንጻሩ መቼ እንደሆነ አይታወቅም እንጂ በእርግጠኝነት የዐማራ ፋኖ ማሸነፉ አይቀርም በሚል ከወዲሁ ዐማሮቹ ለሥልጣን ፉክክሩ መንደፋደፍ የጀመሩም አሉ። ይሄም ቢሆን ለክፉ የሚሰጥ አይደለም። ጤናማም ተፈጥሮአዊም ነው። ደግሞም የሚጠበቅም ነው። ውጊያ ብቻ ሳይሆን ከውጊያው በኋላ ሀገረ መንግሥቱን የሚመሩ አካላት የግድ ያስፈልጋሉ። በዚህ ጉዳይም ከወዲሁ መመካከሩ ክፉ አይደለም። እንዲየውም ዘግይተዋል። በዚህ ወቅት እንዲህ ማሰባቸው እንዲያውም ልበ ሙሉነታቸውን፣ አገዛዙን ለመገርሰስ እርግጠኛ መሆናቸውን፣ ወኔያቸውን እና በራስ መተማመናቸውን የሚያሳይ ነው። "…በሀገር ውስጥም ሆነ በውጭ ሀገራት የሚገኙ ዐማራ ነን የሚሉ ኃይሎች በሙሉ ያለ ሴራ፣ ያለ መጠላለፍ፣ የለ ሸውክ በጀርባ ከሚያደርጉት እንደ ተማረ እንደሰለጠነ ሰው ዓለምአቀፍ የዐማራ ጉባኤ ጠርተው ምክክር፣ ጭቅጭቅ፣ ክርክር ቢያደርጉ፣ በጤናማ መልኩ ሸጋ ነው። ከአቢይ መውደቅ በኋላ ስለምትኖረው ኢትዮጵያ ጉዳይ ሀገሪቷ ምን መምሰል አለባት ብሎ ከወዲሁ መወያየት ቢጀምሩ ክፋቱ አይታየኝም። ሰርገኛ መጣ በርበሬ ቀንጥሱ እንዳይሆን ከወዲሁ እንዲህ ማድረግ ይሄም ጤናማ ነው። ነገር ግን … ከታች ይቀጥላል…✍✍✍
Show more ...
34 357
7
መልካም… "…ዘወትር ያመሰግን ዘንድ፣ የትንሣኤውንም ዐዋጅ ያውጅ ዘንድ የሚፈለገው የአመስጋኝ ቆጥር ሞልቷል። ከምስጋናውና ከክርስቶስ ትንሣኤ ዐዋጅ በመቀጠል በቀጥታ የምናመራው ወደ ርዕሰ አንቀጻችን ነው። "…የዛሬው ርዕሰ አንቀጻችን ደግሞ አንድ ጊዜ ትጥቅ ፈታ፣ ሌላ ጊዜ ሊፈታ ነው፣ አሁን ደግሞ ሊፈታ ነው፣ ወደፊት ይፈታል 😂 እየተባለ በፈረንጅ አፍ፣ በትግርኛና በአማርኛ ጭምር ዜና ስለሚሠራለት እባብ ለመደ ተብሎ በኪስ አይያዝም ስለሚባለው ስለ ወያኔ ሠራዊት ጉዳይ በስሱ እናወራለን። "…የፋኖስ ጉዳይ ትግሉ እንዴት እየሄደ ነው? የሚለውንም በስሱ እንመለከትና ከዚያ ደግሞ የእናንተ ሓሳብ ይከተልና ስንወያይ እንውላለን። "…አይታችሁ፣ ተመልክታችሁ እንደሆነ በፔጄ ላይ ኮተታም አስተያየቶች ቀርተው አንጀት የሚያርሱ፣ ዕውቀት የሚጨምሩ፣ ብሉኝ፣ ብሉኝ፣ ጠጡኝም የሚያሰኙ ግሩም ግሩም የሆኑ በምርጥ ባለሙያ የሚዘጋጁ ሓሳቦች በገበታው ላይ በነፃ እየቀረቡ ነው። ጣታቸውን ቁርጥማት አይንካው። ብዕራቸው ይለምልም። "…ይህ በሆነ ጊዜ ባለጌ፣ ተሳዳቢውን ጣቴን ሳይደክመኝ እያጸዳሁት ነው። ረባሽ ካለ ማን ጥሩ ይጠጣል እንዲሉ ሰካራሞች ረባሽ፣ አለሌ፣ የሓሳብ ድርቅ ያጠቃውን በማስወገድ ስድብ ፈርተው፣ ሓሳባቸውን መሸጥ፣ ዕውቀታቸውን ማካፈል የሚፈልጉትን ወደፊት እናመጣቸዋለን። • ርዕሰ አንቀጹን ለማንበብ ዝግጁ ናችሁ…?
Show more ...
36 538
3
“…ኢየሱስም፦ ትንሣኤና ሕይወት እኔ ነኝ፤ የሚያምንብኝ ቢሞት እንኳ ሕያው ይሆናል፤” ዮሐ 11፥25 • ክርስቶስ ተንሥአ እሙታን ~በዐቢይ ኀይል ወሥልጣን • አሰሮ ለሰይጣን ~አግአዞ ለአዳም • ሰላም ~እምይእዜሰ • ኮነ ~ፍስሐ ወሰላም።
45 198
11
"ኢትዮጵያዊው ጳጳስ እንዲህ ነው የሚሉት" "…ሀገራችን ኦሮሚያ ነው፣ እምነታችን ተዋሕዶ ነው። ፓትሪያሪካችን አንድ ነው። ተሥሎ አለ ነገ ከመጣችሁ ትጎበኙታላችሁ። 1 • ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ባስልዮስ 2• ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ቴዎፍሎስ 3• ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ተክለሃይማኖት 4• ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ 5• ይዘሉታል፣ አይጠሩአቸውም 6• ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ናቸው። "…7 ተኛው ደግሞ ለኦሮሞ ይገባል። አዎ ይገባል። ሥልጣን ላይ ያለው ኦሮሞ አይደል? አዎ 7ተኛ ፓትርያርክ ለኦሮሞ ይገባል። የኦሮሞ ፓትርያርክ አያስፈልገንም ወይ? ባርነትን መቃወም፣ መዋጋት እዚህ ላይ ነው እንጂ መንደር ለመንደር እየዘሮ ከበደ እርዳኝ፣ አለሚቱ እርጂኝ፣ ትግል ላይ ነንና ቲሸርቲ እርዱን እያሉ ሰው ማታለል እይደለም፣ የሚታለልም የለም። "…ትግሉ ያለው 7ተኛ ፓትርያርክነት ላይ ነው። መታገል ከፈለግክ ከእኔ ጋር 4ኪሎ ናና ኦሮሞ ፓትርያርክ ይኑረው እያልክ ጩህ። ትግል ማለት ይህ ነው። ይህ ነው እንጂ ትግል ማለት፣ ያ ቁልቢ ገብርኤል ያለውንና በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሚገኝውን ብርና ወርቃችንን ትተን እዚህ ተገንጥለን ብንቀር ወደ ድህነት ልንገባ ነው አይደል እንዴ? ለማን ልነተወው ነው? እሱም እኮ የእኛ ነው። እሱን እየተካፈልን እኖራለን እንጂ እዚህ ተገንጥለን ወደ መንደር ገብተን ከድሆች ላይ ገንዘብ ለመዝረፍ አይሆንም። "……እንደከዚህ ቀደሙ ከዚህ ከአጥቢያ ወደ 4 ኪሎና 5 ኪሎ የሚሄድ ብር የለም። ከ4 ኪሎና 5 ኪሎ ወደ ታች የሚመጣ ነው እንደ ድሮው ወደ ላይ ማገዝ አይቻልም። 👏👏👏👏 እዚህ ላይ ነው እንግዲህ ለኦሮሞነት መቆም፣ ለዚህ ሕዝብ መቆም። ደግሞም በወሬ አይደለም። በፕሮፓጋንዳም አይደለም። በሥራ ነው እንጂ። ይላሉ 7ተኛው የኦሮጵያ ዕጩ ፓትርያርክ። • እስቲ አስተያየት ስጡበት።
Show more ...

file

60 086
129
ግፍ ከወዲሁ ያቆማሉ ብዬም ተስፋ አደርጋለሁ። "…አገዛዙም የይድረስ ይደረስ ለብለብ ኮማንዶና አየር ወለድ ማስመረቁን ቀጥሏል። የዐማራ ሚሊሻም ፋኖን እየተቀላቀለ ሲሆን፣ መዋጋት የሰለቸው፣ የመረረውም የጁላ ሠራዊት ለኦነግ ሸኔና ለዐማራ ፋኖ እጁን በሀላል እየሰጠም ይገኛል። አሜሪካም ለፉገራም ይሁን ለፉከራ የሚመስል ጓ ያለ መግለጫም አውጥታ ከአገዛዙ ጋር የባልና ሚስት ዓይነት ጭቅጭቅ ሲፈጠር ታይቷል። "…እኔ ግን እላለሁ… የሁሉ ነገር ማስተካከያው መፍትሄው በዐማራ ፋኖ እጅ ውስጥ ነው ያለው። የቤተ ክርስቲያንም ሆነ የቤተ መስጊድ ችግር የሚፈታው በዐማራ ፋኖ እጅ ነው። ቀጣዮቹ ቀናት፣ ሳምንታትና ወራት ወራት በተለይ ደግሞ መጪው ክረምት ፋኖ የውስጥ አካሄዱን ገምግሞ፣ ፈትሾ፣ በድፍረት ወደፊት ከመጣ ብዙው ውስብስብ የሀገሪቱ ችግርና ሰቆቃ መፍትሄ ያገኛል ብዬም ተስፋ አደርጋለሁ። አሁን አሁን ለፓትርያርክነት ለሚሻኮቱት ሙዳየ ምጽዋቱን ከመሙላት ይልቅ ለዐማራ ፋኖ ቀለብና ስንቅ ቢመጸውቱት፣ ቢራዱት ሳያጸድቅ አይቀርም የሚሉ መተርጉማንም አሉ። "…እንደ ሁል ጊዜው ዛሬም እንዲህ ብዬ እጮሃለሁ… • ኧረ ጎበዝ… "…ገንዘብ ባለበት ስፍራ ሁሉ የማይጠፉትን፤ እንደ ጥንብ አንሳ፣ እንደ ጆፌ አሞራ ተወርውረው መጥተው የሚሰፍሩትን፣ ግንቦቴ እና ግንባሮችን ከዶላር ቅርምቱ ላይ እሽሽሽ ብለን እያባረርን የዐማራ ፋኖ አመራሮች በወከሏቸው ሰዎች በኩል ብቻ የዐማራ ፋኖ በተቆጣጠራቸው ግዛቶች ውስጥ ለሰብአዊ ጉዳት የሚውል ገንዘብ እና ዶላር መሰብሰቡ ተጠናክሮ ይቀጥል። • ጆፌ አሞሮቹን በጋራ እንከላከል። • የጥንብ አንሳ ፖለቲከኞች ይውደሙ…! • ድርጅቱ ዘመዴ ነኝ አሸበርቲው ከራየን ወንዝ ማዶ።
Show more ...
62 769
26
"ርዕሰ አንቀጽ" "…ህወሓት እና ብልፅግና ተስማምተው ህወሓት ወደ ማዕከላዊው መንግሥት ቀርባ ቁልፍ ቁልፍ የወሳኝነት የሥልጣን ሥፍራዎችን የምታገኝ ከሆነ አሁን በፓትርያርክነት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን እየመሩ ያሉት ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ በዕድሜ ምክንያት እንደራሴ ተሹሞላቸው አረፍተ ዘመን እስኪገታቸው ድረስ ወደመረጡትና ወደ ወደዱት ገዳም ገብተው ቀሪ ዘመናቸውን በዚያ ሊያሳልፉ እንደሚችሉ እንደተስማሙ ጭምር ያልተጣራ ያልተፈተገ ገብስ ወሬ እየተሰማ ነው። "…ከዚያ በፊት በኢትዮጵያ የተሾሙት ቅዱሳን ፓትርያርኮች ከዐማራና ከትግሬ ስለነበር አሁን ግን ከብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀጥሎ የኦሮሙማው መንግሥት 7ተኛውን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ ነገዱ ከኦሮሞ ለሆነ ወገን የግድ እንዲሰጥ መግባባት ላይ መደረሱም ነው የሚነገረው። ይሄን ጉዳይ ሊቃወሙ ይችላሉ ተብለው የተጠረጠሩና ለምን ሊሉ ይችላሉ ብለው ያሰቧቸውን የማኅበራት መሪዎች እና ግለሰቦች ጭምር በሙሉ ከወዲሁ ወደ ማጎሪያ ጣቢያና ወደ ዘብጥያ እንዲወርዱ የተወሰነ ሲሆን ከዘብጥያ መውረዱ በተጨማሪ ተቃውሞ የሚያስነሣ ካለ ለማስደንገጥ ያህል እንደ ቀልድ የሚገደሉም ይኖራሉ እየተባለም ነው። "…በተለይ ከካቶሊካዊት ቤተ ክርስቲያን በቀር በኢትዮጵያ በአሁኑ ጊዜ መንግሥታዊም ሆነ ሃይማኖታዊ ተቋማት በሙሉ ለምሳሌ የፕሮቴስታንትና የእስልምናው መጀልስን ጨምሮ ሙሉ በሙሉ በኦሮሞ ነገድ ተወላጆች ተይዞ ከእነዚህ ውስጥ በማይታወቅ ኃይል ያም ኃይል  እግዚአብሔር ነው ብለን በምናምን በእኛ በእርሱ ፈቃድ ሳይሳካ ቀርቷል። ጨፍጭፈውም አልተሳካም። እናም ይሄን በቁጥጥራችን ስር ሳናስገባ የቀረነውን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በኦሮሞ ነገድ አባል ለመምራት የተፈለገው ዓይነት ዋጋ መከፈል እንዳለበትና በዘመነ ብልፅግና ይሄን ታሪክ ሳናሳካ ከሥልጣን መውረድም፣ መወገድም የለብንም መባሉ ነው የተሰማው። ይሄንንም ለማሳካት የኦሮሙማው አገዛዝ እስከአሁን በታማኝነት ሲያገለግለው በኖረው በዳንኤል ክብረት ላይ ሸክሙን መጣሉ ነው የሚሰማው። በዳንኤል የውስጥ አዋቂነትና መሪነት 7ተኛው የኢትዮጵያ ፓትርያርክ ነገዱ ከኦሮሞ ወገን የሆነ ለመሾም ከጫፍ መድረሳቸው እና የምረጡኝ ዘመቻ መጀመሩም ነው እየተነገረ ያለው። "…አምሳሉ ፍሬንዳችን አባ ተክሌ ኋላ አቡነ ሩፋኤል አባታችን በአገዛዙ ለኦሮሙማው ፓትርያርክነት የታጩ ሲሆን አፍቃሬ ኦሮሞነታቸው እንጂ አቡነ ሩፋኤል በአባታቸው ጎንደሬ፣ በእናታቸው ትግሬ መሆናቸው አልሸሹም ዞር አሉ አሁንም ዐማራና ትግሬ ነው ፓትርያርክ የሚሆነው እኮ የሚሉ ጓ እያሉ ያሉ ኦሮሞዎች ከወዲሁ መከሰታቸው እየተነገረም ነው። "ንፁሕ" ኦሮሞ ናቸው ተብለው ለፓትርያርክነት በስም ዝርዝር የተዘረዘሩ ናቸው ተብለው የተጠቀሱት በሙሉ ወይ በእናታቸው አልያም በአባታቸው በኩል ወይም ደግሞ ሙሉ ለሙሉ ዐማራ ሆነው በመገኘታቸው ኦሮሙማው በጣም ግራ እንደተጋባ ነው የሚነገረው። ጉዲ ሰዲ… "…7ተኛው ዕጩ ፓትርያርክ እንዲሆኑ ፓትርያርክ መራጩ ዳንኤል ዓይኑን የጣለው ዕጩ ፓትርያርኩ ምንም እንኳ ነገዳቸው ከትግሬና ከዐማራ ቢሆንም በኦሮሚያ መወለዳቸው፣ የኦሮሚኛ ቋንቋንም ቢሆን በስሱ ለመናገር መሞከራቸው፣ በዚያ ላይ በጫካ ላለውም፣ በቤተ መንግሥት ላለውም የኦነግ አገዛዝ ታማኝ አገልጋይ መሆናቸው፣ በቤተ ክርስቲያኒቱም ትምህርት የገፉ ባለመሆናቸው ለመታዘዝ አረጋ ከበደን በመሆናቸው፣ የቀደመው የጵጵስና ሹመታቸውም በጋምቤላ ይኖሩ ለነበሩ ለትግራይ ባለሀብቶች አስተማማኝ ሃይማኖታዊ ከለላ እንዲሰጡ ታስቦ የነበረ መሆኑ፣ በዚያ ላይ እንደነ ብፁዕ አቡነ ናትናኤል በቄሮ፣ እንደነ ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ በሁሉም ነገድ የተጠሉ፣ እንደነ ብፁዕ አቡነ ኤውስጣቴዎስ በዝሙት ምክንያት የተጻፈ የተገለጠ መረጃ የለሌባቸው፣ ሳይነገራቸው፣ ሳይለመኑ ለአገዛዙ በፈቃዳቸው ገሌ መሆናቸው፣ ከሁሉም በላይ በዋናነት ትምሮ ላይ 0 መሆናቸው ተመራጭ እንዲሆኑ አድርጓቸዋል ነው የሚባለው። "…ለዚህም ሲባል ከወዲሁ እነ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ በራሳቸው ስህተትና ፍላጎት አሜሪካዊ ዜግነታቸውን መቀየር ባለመፈለጋቸው ምክንያት ወደ ሀገር እንዳይገቡ ከተከለከሉት አንሥቶ ዳንኤል ክብረት የሲኖዶሱ ጸሐፊ የነበረውና ወደ ደቡብ አፍሪካ በዋና ሥራ አስኪያጅነት ተመድቦ የነበረው መሪጌታ ጋዜጠኛ ብርሃኑ ተክለ ያሬድን ወደ ዘብጥያ በማውረድ አፋር ሰመራ በረሃ ወርዶ እንዲታሰር በማድረግ፣ ዳንኤል እግረ መንገዱንም የማኅበረ ቅዱሳንን የልብ ትርታ ለማዳመጥ የማኅበሩን የሥራ አመራሮች አሳስሮ የነበረ ሲሆን የማኅበሩን ሙቀት ከለካ በኋላ ግን ሌሎቹን በዘብጥያ እንዲቆዩ በማድረግ እነሱ እንዲፈቱ አድርጓል ነው የሚባለው። "…የሆነው ሆኖ አገዛዙ ዳንኤል ክብረትን ከተጠቀመበት በኋላ ጋርቤጅ ውስጥ እንደሚወረውረው ቢያውቅም ቂም ያለበት በሚመስል መልኩ ባሳደገችው፣ ለክብርም ባበቃችው ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ላይ በዚህ መልኩ መነሣቱ ግን በቤተ ክርስቲያን ልጆች ዘንድ አነጋጋሪ እየሆነ መጥቷል። እናም እንደተለመደው የቤተ ክርስቲያኒቱ ራስ ኢየሱስ ክርስቶስ፣ የቅዱስ ሲኖዶሱ መሪ እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ መለኮታዊ ጣልቃ ገብነት ኖሮ የታሰበው ሁሉ ካልተሻረ በቀር ከፊታችን የምንሻገረው ነገር ግን የሚያንገራግጭ ፈተና እንደ አማኝ የሚጠብቀን መሆኑም ይሰማል። ከእስር፣ ከድብደባም አልፎ እስከ ሰማእትነት የሚያደርስ ፈተና እንደተዘጋጀልን ነው የሚሰማው። "…የአሁኑ ፈተና እምብዛም ወደ ምእመናን ዘንድ የማይወርድ እንደሆነ ቢገመትም ቤተ ክህነቱ አካባቢ ግን ጽዳት እንደሚኖርም እየተሰማ ነው። በተለምዶ ጳጳሳቱ በቡድን በቡድን ተቧድነው ወደ ቅዱስ ሲኖዶስ ስብሰባም ገብተው በቡድን ተቧድነው የመከሩትን ሳይሆን የጉባኤው መሪ እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ እሱ ባወቀ ፊታቸውን ፀፍቶ፣ አንደበታቸውን ከፍቶ ኋላ ላይ ምን ሆነን፣ ምንስ ነክቶን ነው በማለት እስኪገረሙ ድረስ ሓሳባቸውን እያስቀየረ እርሱ እግዚአብሔር የወደደውንና የፈቀደውን ይሠራባቸው እንደነበር ይታወቃል። አሁንም ካልተወን በቀር እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ካልተለየን በቀር የእነ ዳንኤል ክብረት ቡድን ምንም ያህል ሴራ ቢያሴር ሊሳካለት አይችልም ነው የሚሉት አስተያየት ሰጨዎቹ። "…መቼም የዘንድሮው ክረምት የሞት ሽረት ክረምት ነው። ፋኖም ሥልጠናውን አጠናቆ የዋንጫ ጨዋታውን እየጠበቀ ነው። በተለይ በአንዳንድ ቦታዎች ያሉ የፋኖ አመራሮች ጥልቅ ተሃድሶና ግምገማ አካሂደው እንደ ንስር ታድሰው ከተነሡ ትንሣኤ ኢትዮጵያ መቅረቡ ነው። ከቀናት በኋላ እኔ ራሴ ዘመዴ ከአየር ላይ ውጊያው ወደ ተዝረከረከ የፋኖ አማራሮች ውጊያ ሙሉ መንፈሳዊ ትጥቅ ታጥቄ መክተቴ አይቀርም። ያበጠውን አፈንድቶ ልክ እንደ አየር ላይ ውጊያው መሬት ላይም የተበላሸ፣ የተግማማ፣ የከረፋውን፣ ሕዝብን እያስመረረ ያለውን፣ በጊዜ ካልታከሙት ሕይወት የሚያጠፋውን የፋኖ አመራሮችን እና አካሄዶችን ስህተት ወደ መዋጋቱ እገባለሁ። ዐማራ ፋኖ ያሸንፋል። ነገር ግን እታገልለታለሁ የሚለውን ሕዝብ ከወያኔና ከደርግ በከፋ መልኩ የመከራ ዶፍ አውርዶ ከወዲሁ ሥልጣን ላይ ሳይወጣ የሚያሰቃይ ስመ ፋኖ ጭምብላም በመረጃና በማስረጃ በሙሉ ኃይሌ እጋፈጠዋለሁ። እኔ ብቻዬን የማይነካ ነክቼ ለመዝመት ዝግጁ ነኝ። አንድም የሚያግዘኝ ሰው አልፈልግም። ይሄን መልእክቴን የሚያነቡ የማከብራቸው ፋኖዎች በሕዝብ ላይ የሚሠሩትን
Show more ...
58 457
25
"…መልካም… "…ዘወትር እግዚአብሔርን ያመሰግን የክርስቶስን ትንሣኤ ያውጅ ዘንድ፣ የሚጠበቀው 1ሺ ሰው ሞልቷል። ቀጥሎ የምንሄደው ወደ ርዕሰ አንቀጻችን ነው። "…በዛሬው ርዕሰ አንቀጻችን ያፋኖ ተጋድሎ ሳይረሳ ስለ 7 ተኛው ዕጩ የኦሮጵያ ፓትርያርክ ቀኝ ትከሻይን ሸክኮኝ ጻፍ ጻፍ ስላለኝ ልጽፍነኝና እናንተስ ለማንበብ ዝግጁ ናችሁ? • እደግመዋለሁ ዝግጁ ናችሁ ወይ…? እንዲህ ብዬ ስጠይቅ ቤቴ አዎ ዝግጁ ነነ በሚል ቃል ሲሞላ፣ ሲጥለቀለቅ ሠራዊት ያሰለፈ ጀነራል የሆንክ ያህል ነው የሚሰማኝ። 😂😂😂 • ዝግጁ ናችሁ…?
56 025
15
“…ሞቱንም በሚመስል ሞት ከእርሱ ጋር ከተባበርን ትንሣኤውን በሚመስል ትንሣኤ ደግሞ ከእርሱ ጋር እንተባበራለን፤” ሮሜ 6፥5 • ክርስቶስ ተንሥአ እሙታን ~በዐቢይ ኀይል ወሥልጣን • አሰሮ ለሰይጣን ~አግአዞ ለአዳም • ሰላም ~እምይእዜሰ • ኮነ ~ፍስሐ ወሰላም።
60 458
30
ኮመንቱና ኮማቾቹ…! "…ምን ሆነው ነው ለመቀሌ ዜና ኦሮሞ ኮማቾች ብቻ ዋይ ዋይ የሚሉት። 1 ሚልዮን ትግሬ የጨፈጨፈባትን የኦሮሞ ብልጽግናን እንደሁ የቀን ጉዳይ እንጂ ሂዊ እንደሁ አትረሳ። ኧረ ቀስ እነ መገርሳ… "…አይ ኦሮሞ አለ አራጅ አቢይ አሕመድ። ደግሞ እኮ አማርኛ አጣጣላቸው ሲያምር። ቁቤን ውኃ በላት አላለም ጉማ ሳቀታ…😂😂😂
59 948
20
1
0
Last updated: 11.07.23
Privacy Policy Telemetrio