በፋኖ ስም…
"…አገዛዙ አሰልጥኖ ይላካቸው፣ ወይ ብአዴን ግንቦት 7 እና ወያኔም ያሰማሯቸው ብቻ በፋኖ ስም የተከበረውን፣ የፋኖ ትግል የሚያዋርዱ፣ የተቀደሰውን የፋኖን ትግል የሚያራክሱ ሰርጎ ገብ ፌካፌካም የቁጩ ዘራፊ ፋኖ አሰዳቢ ሌቦችን እንዲህ መንጥሮ በማውጣት እርምጃ መውሰድ ለትግሉ እጅግ ጠቃሚ ነው።
"…እነዚህን ብቻ ሳይሆን ቤተ ሰቦቻቸውን አዲስ አበባ ልከው፣ ቤትም ተከራይተውላቸው በዐማራ ፋኖ ስም ዐማራ እያገቱ በሚልዮን ብር የሚቀበሉ፣ የሚደበድቡ፣ ዐማራውን አማርረው ፋኖ መጣልኝ ሳይሆን ፋኖ መጣብኝ ብሎ ፋኖን እንደ ስጋት ምንጭ እንዲያይ እያደረጉ ያሉ፣ ወያኔ ማሪኝ፣ ብአዴን ይቅር በለኝ የሚያሰኙ አለሌ የማፍያ ጠባይ ያላቸውንም ፋኖ አሰዳቢዎች በድፍረት መጋፈጥ ያስፈልጋል።
"…የዐማራ ትግል የህልውና ትግል ነው። በዐማራ ትግል ውስጥ ተደብቆ አረመኔያዊ ተግባር መፈጸም የከፋ ወንጀልም ነው። የፋኖ ግምገማ መጀመር አለበት። የዐማራ ገበሬ መደመጥ አለበት። በነጩ ሸማ ላይ ያረፉ ነጠብጣብ ቆሻሾች የዐማራን ትግል ማቆሸሽ የለባቸውም።
"…በሸኔና በወያኔ የተማረረውን ሕዝብ በዐማራ ፋኖ ስም ማማረር ይቅር የማያስብል ወንጀል ተደርጎ መፈረጅ አለበት።
• በለው…!
Show more ...