#MoH
በተለያዩ የጤና ሙያዎች በመጀመሪያ ዲግሪ የተመረቁ የጤና ባለሙያዎች የብቃት ምዘና ፈተና
ግንቦት 15 እና 16/2016 ዓ.ም ይሰጣል።
በኮምፒውተር የሚሰጠው ፈተና ፕሮግራም እንደሚከተለው ይሆናል፡-
➧ Pharmacy, Public Health, Midwifery, Medical Laboratory
👉
ግንቦት 15/2016 ዓ.ም
➧ Nursing, Medicine, Dental Medicine, Pediatric Nursing, Psychiatric Nursing, Emergency & Critical Care Nursing, Medical Radiology Technology, Anesthesia and Environmental Health
👉
ግንቦት 16/2016 ዓ.ም
ተመዛኞች ግንቦት 14/2016 ዓ.ም ከጠዋቱ 3፡00 ሰዓት በመፈተኛ ጣቢያ በመገኘት ስለፈተናው አሰጣጥ ኦረንቴሽን መከታተል፣ የኮምፒውተር ቅድመ-ፈተና መለማመጃ ጥያቄዎችን መስራት፣ ወደ ፈተና የሚያስገባውን Username and Password ማወቅ እንዲሁም የመፈተኛ ክፍላችሁን መለየት ይኖርባችኋል ተብሏል።
በፈተናው ዕለት ማንነታችሁን የሚገልጽ መታወቂያ (የቀበሌ መታወቂያ፣ ፓስፖርት፣ መንጃ ፍቃድ ወይም ሌላ በግልጽ የሚታይ ህጋዊ መታወቂያ)፣ የፈተና መስሪያ ግብዓቶች (እርሳስ፣ ላጲስ፣ መቅረጫ) እና ስትመዘገቡ ሲስተሙ የሰጣችሁን ስሊፕ ይዛችሁ መገኘት ይኖርባችኋል፡፡
ምንም አይነት የኤሌክትሮኒክስ መሳሪያ (ስልክ፣ የእጅ ሰዓት፣ መነጽር (የተረጋገጠ የዕይታ ችግር ከሌለ በስተቀር)፣ ቦርሳ እና ሌሎች እቃዎች፣ ምንም አይነት ማጣቀሻዎች እንዲሁም ባዶ ወረቀቶች፣ ምግብ ወይም መጠጥ (የተረጋገጠ የጤና ችግር ከሌለ በስተቀር) ይዞ መግባት አይፈቀድም፡፡
የመፈተኛ ጣቢያ ኦንላይን በመረጣችሁት መሰረት ስም ዝርዝራችሁን ተከታዩን ሊንክ በመጫን መመልከት ይኖርባችኃል 👉
https://drive.google.com/drive/folders/1e329fbEYG-P2vT0WJ1uSlw1tVlgtEFg4?usp=sharing)
ለተጨማሪ መረጃ በስልክ ቁ.
0118275936 እንዲሁም
moh.gov.et ላይ EHPLE የሚለው ውስጥ በመግባት ማግኘት ይቻላል፡፡
@tikvahuniversityShow more ...