በእነ አቶ ዮሐንስ ቧያሌው መዝገብ፤ የቃሊቲ ማረሚያ ቤት ኃላፊ ለፍርድ ቤት ማብራሪያ እንዲሰጡ ታዘዙ‼️
በእነ አቶ ዮሐንስ ቧያሌው መዝገብ የእስረኞችን አያያዝ በተመለከተ የቃሊቲ ማረሚያ ቤት ኃላፊ ፍርድ ቤት ቀርበው ማብራሪያ እንዲሰጡ በፍርድ ቤት ታዘዘ።
አቶ ክርስቲያን ታደለ “ለቀናት” ምግብ አለመመገባቸውን ለፍርድ ቤቱ ዛሬ በዋለው ችሎት ገልጸዋል። ምግብ ያልተመገቡት፤ በማረሚያ ቤቱ “
#አማራ ተከሳሾች ስለሆናችሁ እንደሌሎቹ ተከሳሾች አትስተናገዱም” በሚል የቤተሰብ ጥየቃ ሰዓት ላይ ለውጥ በመደረጉ መሆኑን ለችሎቱ አስረድተዋል።
ዶ/ር ካሳ ተሻገርም በተመሳሳይ፤ “ የቀጠሮ እስረኞች ሆነን እያለ ነገር ግን ከፍርደኞች ጋር እንድንታሰር አድርጎናል” ሲሉ አቤቱታቸውን ለችሎቱ በቃል መግለጻቸውን ጠበቃቸው ሄኖክ አክሊሉ ለቢቢሲ ገልጸዋል።
ዶ/ር ካሳ “መንግሥት አላግባብ በተለያየ ሚዲያ ከሰራው ዘገባ ጋር በተገናኘ ፍርደኞች እኛ ላይ ዛቻ እና ማስፈራራት አድርሰውብናል” ማለታቸውን ሄኖክ ጠቅሰዋል።
በተከሳሾቹ የቀረቡ ሰብዓዊ መብት ጥሰቶችን በተመለከተ የ
#ኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን መርምሮ አጣርቶ ውጤቱን ለፍርድ ቤቱ እንዲያሳውቅ ችሎት ትዕዛዝ ሰጥቷል።
ከዚህ በተጨማሪም ተከሳሾች “ማረሚያ ቤቱ ከማንነታችን ጋር በተያያዘ በምሳ ሰዓት ብቻ እንድንጠየቅ ተደረግን” በሚል ላቀረቡት አቤቱታ ማረሚያ ቤቱ ምላሽ እንዲሰጥ እና የቃሊቲ ማረሚያ ቤት ኃላፊ በአካል ቀርበው እንዲያስረዱ መታዘዙንም ጠበቃ ሄኖክ አስረድተዋል።
Show more ...