Best analytics service

Add your telegram channel for

  • get advanced analytics
  • get more advertisers
  • find out the gender of subscriber
CategoryNot specified
Channel location and language

audience statistics የግጥም ቃላቶች

ጥበብ እንደ ጥጥ ነው ለጉድ ተፈልቃቂ ሰው ጥሩ ፈታይ ነው ድር ማግ ግን አላቂ ስለ ግጥም ብላቹ ላይ አዋዩኝ የናንተ ድምፅ ነው ለኔ እውቀት የሆነኝ . . . 
67 6260
~0
~18
0
Telegram general rating
Globally
15 957place
of 78 777
115place
of 396

Subscribers gender

Find out how many male and female subscibers you have on the channel.
?%
?%

Audience language

Find out the distribution of channel subscribers by language
Russian?%English?%Arabic?%
Subscribers count
ChartTable
D
W
M
Y
help

Data loading is in progress

User lifetime on the channel

Find out how long subscribers stay on the channel.
Up to a week?%Old Timers?%Up to a month?%
Subscribers gain
ChartTable
D
W
M
Y
help

Data loading is in progress

Hourly Audience Growth

    Data loading is in progress

    Time
    Growth
    Total
    Events
    Reposts
    Mentions
    Posts
    Since the beginning of the war, more than 2000 civilians have been killed by Russian missiles, according to official data. Help us protect Ukrainians from missiles - provide max military assisstance to Ukraine #Ukraine. #StandWithUkraine
    🌼አደይ ምዕራፍ 2 ክፍል 4 📥 ትክክለኛው የአደይ ድራማ ቻናል               👇🏽👇🏽👇🏽 ━━━━━━━━━━

    @Adey_Dramaaa.mp4

    2 367
    19
    "በህይወቴ አንድ ግዜ ክፍለ ሀገር ብሄድ ከበውኝ Money Money አሉኝ" ብሎ Post አላደረገም n እና e መሃል K'ን ረስተሃል
    2 678
    0
    አደይ ምዕራፍ 2 ክፍል 3 ♨️ቻናላችንን በቅንነት share በማረግ ተባበሩን

    @Adey_dramaaa.mp4

    3 230
    9
    አደይ ምዕራፍ 2 ክፍል 3 ይለቀቃል ይጠብቁ ። ♨️ቻናላችንን በቅንነት share በማረግ ተባበሩን
    3 036
    1
    አደይ ምዕራፍ 2 ክፍል 3 አነስ ባለ Mb ♨️ቻናላችንን በቅንነት share በማረግ ተባበሩን

    ሙሉ_ክፍል_45_አደይ_ምዕራፍ_2_ክፍል_02_አቦል_ቲቪ_adeydrama_aboltv_abe_U7YLKektLRU.mp4

    3 604
    11
    በፈጠረክ ስትስቅልኝ ስትጫወት በእቅፎችህ ስታስገባኝ አጠገብህ ቁጭ ብዬ አይን ልብህ ሲሰስተኝ እንደምትወደኝ አስባለው ልቀርብህ ሞክራለው ያንተን ጠረን ለምጄ እዛው በዛው ስሽከረከር ይወደኛል አይወደኝም እያልኩ ከራሴ ጋር ስከራከር ያንን ስታውቅ... ቶሎ ብለህ መስመርህን ታሰምራለህ አይንህን ልብህን  አካልህን ታርቃለህ የሄድኩበት እንዳልመጣህ ስከተልህ ትሸሻለህ አንድ... ልመጣ ስል እየሸሸህ ስሄድ የምትመጣው እንደሚወድ እንደማይወድ እንደሁለቱም የምትሆነው መውደድን ነዉ መወደድን የትኛውን ነዉ የፈራኸው ሁለት ... እንዲ ስትሆን ይወደኛል እንዲያ ስትሆን አይወደኝም እያልኩ ከምጨነቅ  ትወደኛለህ አትወደኝም ንገረኝ በፈጠረክ
    3 385
    40
    መልካም ሚስት ደሀ የሆነ ባሏን ንጉስ መስሎ እዲኖር ታደርገዋለች፡፡
    3 197
    7
    ዝምታ እና ፈገግታ ሁለት ሃይለኛ መሳሪያዎች ናቸው ፈገግታ ብዙ ችግሮችን መፍታት ሲችል ዝምታ ደግሞ ብዙ ችግሮችን ማስወገድ ይችላል! #ፈገግ_ብላቹ_ዋሉልኝ😄
    3 032
    12
    አንዱ ምስኪን በፍቅር የጠነዘለ ላፈቀራት ሴት የጻፈው አጭር ትንሽ ገነን ያለ ምሬትን ያዘለ ደብዳቤ ነው። ማሳሰቢያ:የግጥሙ የመጀመሪያው አናት ላይ በውስጥ አዋቂነት "ይድረስ ለምወድሽ፤ቆይተሽ ለምትወጂኝ"የምትል ሀረግ አላት። እስከ ዛሬ ድረስ ባንቺ ትዝታ ልክ ደም እንባ ሳነባ (ሳጋን ነው😁) በዚህ ፍጥነት አለም የኋሊት ሳደባ ኖርኩ። ይብቃኝ በይ ከንግዲህ ያንቺ ሃሳብ ወዲያ የኔ ሃሳብ ወዲህ ጨረስኩ እሩጫዬን በይ አንቺ ተተኪ መንገዱን አወኩት ትዝታሽን ውሰጅልኝ ትዝታዬን ላንቺ ተውኩት። እስቲ ባንቺ ልዬው! ዮኒ ኣታን
    3 081
    1
    ሀገር ማለት ሰው ነው እያሉ በትውልድ እንቅልፍ ላይ ብርድልብስ ይደርባሉ። ሀገር ማለት አፈር ነው። ኢትዮጵያ ከተፈጠረች ጀምሮ የሞቱት ሰዎች ስጋና አጥንት ሆኖ ይኸው አሉና መሬቱን በጎራዴው ጫር ጫር አደረጉት። አየህ አሁን አፈር አደለም የጫርኩት የሰው ስጋ ነው ሲጫር የሚያመው ሲወጋ የሚያቃስት ሰው ነው።ይህንን ነው ቆርሰው የሚወስዱት። ሀገር ማለት ሰው ከሆነ ሰው አፈር ነውና አፈርህን ሲነኩ እምቢ ልትል ይገባል። ልጄ ህንፃ መንገድ አይግረምህ የሰው ልጅ የሚሰራው የእጅ ጥበብ ሁሉ አይድነቅህ ነገም ልጆችህ ከአንተ በተሻለ ይሰሩታልና። ልጆችህ ለማያገኙት ስንዝር መሬት ግን ያለህን ክፈል። ስንዝር መሬት ሰጥተህ ዘመናዊነት ከምታመጣ ቅንጣት አፈርህን ሳታስነካ እድሜ ልክህን በዘላንነት ኑር ለልጅህ መቀመጫውን ተውለት። ዛሬ ተሰርቶ ነገ ለሚፈርስ መንገድና ድልድይ ህንፃና ግድብ ለልጅህ ሀብት አደለም። መሬት መሬት መሬት ምንም ቃል ምንም ስምምነት መሬትህን ካሳጣህ የታሪክ ጉድፍ ነው። መሬትህም ሲነጠቅ አጨብጭብ የሚሉህ የታሪክ አተላ የማንነት ጉድፍ ናቸው። ያለህን ይባርከው ሲሉህ ምርቃት መስሎህ አሜን እንዳትል።ከዚህ የባሰ መርገምት የለም።የተሸረፈ ባርኮት ከእርግማን እኩል ነው። ምንጭ_ ዙቤይዳ በአሌክስ _አብረሃም
    Show more ...
    2 782
    5
    ስትገረሚ አየው ስትደነቂ አየው ዱብዳ ሆኖብሽ አማላይ ገላሽን ገፍቼ መሄዴ ያቺን ባላገር ልጅ    ከአንቺ በመልመዴ ግና  ልናገረው እንቺ የእውነት ቃል ያልተኳለው ፊትሽ አስደንግጦኝ ያቃል! ንጡህ ፊት እያለ ስተኛም የሚያምረኝ ስነሳም የሚያምረኝ ካንቺ እንግዳ ፊት ጋር ምን አደናበረኝ? *------------------*
    3 032
    16
    ​​​​​​                  "ሴትን አላምንም" ክፍል 8 Semir ami❤️               ✍  ……አህላምዬ ዛሬ አልመጣችም ማንን ልጠይቅ ለማን አቤት ልበል? አህላም ከሌለች መንገዱስ የት አለ? እረ እግሬስ እንዴት እሺ ብሎ ይራመድልኛል? … ስልኬን ስላልያዝኩኝ ያለኝ አማራጭ በፍጥነት እቤት ደርሼ መደወል ነው። ጥያት መሄዱ ቢያስከፋኝም አማራጭ አልነበረኝም። በአቅራብያዬ ባለ ታክሲ ገብቼ ተሰፋርኩኝ ታክሲው ሲንቀሳቀስ  ቅር ፣ ቅር ይለኝ ጀመር። ከት/ቤት እየራቅኩኝ ስመጣ በመስኮት ዞሬ ተመለከትኩኝ ለብዙ ደቂቃዎች ስፈልጋት የነበረችው አህላምዬ በር ላይ ቆማ ማያት መሰለኝ…… የለችም ባር ባር አለኝ ሳላየት ላድር ነው ላለፉት ቀናቶች አስለምዳኝ የሄደችውን ጨዋታና ሳቅ ዛሬ የለም መንገዱ ላይ ያሉ ሰዎች በፍጥነት ይራመዳሉ ፣ የንዴት እና የብስጭት ፊት የሚታይባቸው ሰዎች መንገዱ ላይ ቁመዋል ለምን ተቆጡ እነሱም  አህላምዬን ስላላዩ ይሆን? ታክሲ ውስጥ የተከፈተው ለስለስ ያለው ሙዚቃ ከሃሳቤ አባነነኝ…  የአህላምዬ ፈገግታ ፊቴ ድቅን   እያለ ያስቸግረኛል ምን አለ ሰዎች "የሳቅን ስልት" ከሷ ቢማሩ ሰው ለስልኩ ጥሪ ከሚቀያይር እያደር አዲስ ሚሆነውን የአህላምዬን ፈገግታ አንዴ ጥሪ ቢያደርግስ?  ታክሲው ጉዞውን ቀጥሎአል። እኔም ሙዚቃውን እየሰማሁኝ በሃሳቤ ገስግሻለው…  ለእኔ ከአህላምዬ ጋር ያሳለፍኳቸው አጭር ቀናቶች የራሳቸው ገፅ አላቸው ዛሬ ግን አህላም የለችም።  ትዝታዋ ግን አለ የረዥም ጊዜ ሳይሆን ሰሞኑ የሆነ ዛሬ ላይ ግን ትዝታ የሆነ እኔ በትዝታ ወደ ሁዋላ ተመልሻለው ፤ ታክሲው ግን ወደፊት ይገሰግሳል። አህላምዬ ከመጀመርያው እለት ጀምሮ በተፈቀደላት መሠረት ልቤ ውስጥ ገብታ ፤ እግሮቿን አኮራምታ ቁጢጥ አለች ፣ ውላ ስታድር ተንፈራጣ ተቀመጠች ፣ በቆይታዋ ደግሞ በጀርባዋ ጋደም አለች ስትከርም ጭራሹን ጓዟን ጠቅልላ ይሄ መከረኛው ልቤ ላይ ተኛችበት። እቤት ስገባ እናቴ የተለመደውን ፈገግታዋን አሳየችኝ ሳያት ድካሜ ይጠፋል የመኖር ፍላጐቴ ያይላል ፣ አንድ ልጇ ነኝ ለእኔ ብዙ ሁናለች። ከት/ቤት ስመጣ ውጊያ ሂጄ እንጂ ተምሬ የመጣሁኝ አይመስላትም ራበህ? ደከመህ? ምን አዲስ ነገር አለ? የዘወትር ጥያቄዎቿ ናቸው ማሚ ዛሬ እነዚህን ጥያቄዎችን ለማስተናገድ ፍቃደኛ አይደለሁም በልቤ አልኩኝ። ዛሬ ፀሀይ መች ወጣች ፣ ዛሬ ከተማው ላይስ መች ሴት ነበር ፣ ዛሬ ከተማው ላይ ማን የሳቀ አለ? ሴትም ፣ ሳቅም ፣ ፀሀይ አልነበሩም ስለዚህ ስለየትኛው ልንገራት ስልኬ ጋር ለመድረስ ጓግቼ ማሚን በቅጡም ሰላም ሳልላት ወደ ክፍሌ ገባሁኝ ምን ያረጋል አህላምዬ አልደወለችም። ጨካኝ😠 ደህና ነኝ ፤ በሰላም ነው ያልመጣሁት አትልም?  ይጨነቃል ያስባል ብላ አታስብም?  ደህና ባትሆንስ? የሆነ ነገር አጋጥሟት ቢሆንስ? "የመኝታ ቤቴ በር ተከፈተ እናቴ ናት ማሚ የድሮ አራዳ ነች ቀለል ሲላት ከትዝታዎቿ ማህደር ታገራኛለች ዛሬ ግን አንድ የፈለገችው ነገር እንዳለ ያስታውቅባታል። ሰኢዲዬ ስትጨርስ ሳሎን ና እየበላን ማወራህ ነገር አለህ አለችኝ  እሺ ብዬ ወደ ስልኬ ተመልሼ አህላም ጋር ደውልኩኝ ስልኳ አይነሳም ከአንድም ሶስቴ ደውዬ አታነሳውም።  ድንገት አንድ ነገር ትዝ አለኝ ወንድሟ ቀጣይ ለሶስት ሳምንት ከሄደበት በያዝነው ሳምንት ይመጣል ብላኝ ነበር ቁርጥ ቀነኑን ባትነግረኝም። ወንድሟ መጥቶ ይሆናል ብዬ እኔም ተረጋጋሁኝ ልብሴን ቀይሬ ሳሎን ገባሁኝ። ማሚ ሳሎን ላይ ባለው መጅሊስ እንደ ልእልት ተቀምጣለች፤ ዝምታዋን ለመስበር ማሚ" አንዳንዴ ትኩር ብዬ አይሽና ምን ያህል እድለኛ ብሆን ነዉ አንቺን እናቴ አርጐ የሰጠኝ ብዬ አስባለሁ " ብዬ ግንባሯን ሳምኳት። እናቴ ምንም ከመናገሯ በፊት ከጥያቄ ነው ምትነሳው ትምህርት እንዴት ነው? እና ተያያዥ ጥያቄዎች ? በተርታ ከመለስኩኝ በሗላ ። ሁሌም ስለ አባቴ ስታነሳ  እንደምትሆነው አንገቷን አቅርቅራ። ሰኢዲዬ? ወዬ ማማ ጠጋ ብዬ ታፋዋ ላይ ተኛው እሷም  ፤ ባባ ከሞተ በሗላ የስራው ሁኔታ መስመር ለማስያዝ ሞክርያለው አሁን እየደከመኝ ነው። ሃላፊነቱን እንድትረከበኝ እፈልጋለው ይህ የሚሆነው አሁን ሳይሆን የዚህን አመት ትምህርትን ስታጠናቅቅ ነው ፤ የኮሌጅ ትምህርቱንም በማታው ክፍለ ጊዜ ትቀጥላለህ ለዚህም እስከ ክረምቱ ረዥም የማሰብያ ጊዜ አለህ  እስከዛው ድረስ ግን ቅዳሜና እሁድ አብረን እንወጣለን አለችኝ። ባባ ጠንካራ ነጋዴ ነበር 9ኛ ክፍል እያለሁኝ ነበር ድንገት በተከሰተበት የልብ ህመም ነው ያረፈው  ። ባባ ተቆፍሮ የማይደርስበት ጥልቅ የሃሳብ ሃብት ፣ከሰማይ የራቀ ምልከታ የነበረው ነበር።  አላህ የጀነት ይበለውና ሁሌም ምክሩ እናትህን አደራ ነበር አደራዬን ማስቀየም አልፈልግም ዩንቨርስቲ ገብቼ መማር ብፈልግም የእርሷ ፍላጐት ከሆነ ከእሷ የሚበልጥ ነገር የለምና ሃሳቧን እንደምቀበል ነገረኳትና ግንባሯ ስሜ ወደ ክፍሌ አመራው። ፀሀይ ጠልቃለች ቢሆንም አሁንም አህላም ስልክ አታነሳም ልቤ ፍርሃት ፍርሃት አለው፣ ውጣና ብረር እቤታቸው ሂድ ሂድ አለኝ። የወጣችልኝ የህይወት ፀሃይ በደንብ ሳላያት የጠለቀችብኝ መሰለኝ ፤ ነገ ጠዋት የመጀመርያ ስራዬ ሰፈሯ ሂዶ መውጫዋ ጋር መከታተል ነው ቢያንስ ደህንነቷን አረጋግጬ እመለሳለው ብዬ ጋደም አልኩኝ በዛችው ቅፅበት ኬት መጣ የማይባል እንቅልፍ ጭልጥ አርጐኝ ይዞኝ  ሄደ አይነጋ የለ ነጋ የመጀመርያ ስራዬ ወደ አህላም ስልክ መደወል ነበር። ስልኳ ጥሪ አይቀበልም ፍርሃቴ ይበልጡኑ ጨመረ፣  ማታ አይነሳም አሁን ደግሞ ዝግ ነው ምን ሆና ይሆን? የዚህን ጥያቄ መልሱ ያለው እቤቷ ደጃፍ ስደርስ ነው።  ደህንነቷን አረጋግጬ ወደ ክላስ እገባለው ብዬ 1፡00 ከቤት ወጥቼ ላዳ ይዜ  ወደ ሰፈራቸው አቀናው። ወደ መንደራቸው መግቢያ ጋር የመኪና መጨናነቅ አለ እዛ ስደርሰወ 2:00 ሰዓት ሆኖዋል በዚህ ሰአት የመኪናው ግርግር ስላልገባኝ ባለላዳውን እዚህ ጋር አቁመውና እኔ ደርሼ ልምጣ ብዬው ወደ ሰፈራቸው ገባሁኝ። …… ድንኳን እግሬ ተንቀጠቀጠ ፣ ትንፋሽ አጠረኝ ፣ እይታዬ ተጋረደብኝ። ጥቁር ዩኒፎርም የለበሱ ሴት ተማሪዎች ከሩቅ ይታዩኛል አዎ ድንኳኑ እነ አህላም በር ላይ ነው ዙሪያውን ደግሞ የትምህርት ቤታችን ዩኒፎርም የለበሱ ተማሪዎች አሉ እየፈራሁኝ ወደ ድንኳኑ ተራመድኩኝ……         ክፍል ዘጠኝ ይቀጥላል……… #,yegetem kalate የወደዳችሁት በላይክ አሳዩን ፈጥነን እናደርሳለን
    Show more ...
    2 686
    1
    ።።።።።የፍቅርሽ ሃያልነትሽ።።።።። ~~~~~~~~~~~~~ ያኔ ስንገናኝ በጓደኝነታችን፤ ድንገት ሳናስበው በፍቅር መጥለቃችን፣ ወደታች እንደሚሠምጥ የባህር ድምፅ እንጉርጉሮ፤ የፍቅርሽ ሃያል በደሜ ውስጥ ገብቶ ልቤን ጎርጉሮ፤ መተንፈስ እስኪያቅተኝ መናገር ተቸግሬ፤ ለመናገር የፈራሁት አንቺን አፍቅሬ፤ -------ሁሌም እልሻለው------- --------እወድሻለው------ እና እምልሽ አንቺን ካገኘው ከወደድኩሽ በኅላ፤ ያለኝን ሁሉ አየው ተመልሼ ወደኅላ፤ አለም አንቺን ሰጠችኝ፤ ደስተኛ እንድሆን አደረገችኝ፤ ጥይት እንኳን ቢተኮስ የማይበሳውን ልቤ፤ በአንቺ ፍቅር ብቻ በአንቺ ፍቅር ተከፈተ ልቤ፤ --------ሁሌም እልሻለው---------- ✍️ባር
    3 813
    16
    ልማልብሽ ለማንም የማልሰንፍ ለአንቺ እጄን ምሠጥ ለሌላው ኮስታራ ለአንቺ ምቁነጠነጥ በጉልበት በሀይሉ የለም ከሡ በላይ .......................ተብሎ እየተወራ በአንቺ ሲመጡ ግን ልቤ የሚፈራ የሳምሶንን ጉልበት የሚያስንቀው ክንዴ ነገር ግን ደሊላ ሁነሺብኝ አንዴ እንዴት አልቸገር አልጨነቅ ውዴ ። ነገር ማበላሸት ከሄዋን ቢሆንም ታላቁ ዳዊትም ለአቢጊያ ብሎ አሽከሩን ቢገልም,ኦርዮን ቢሞትም የኔ ግን ከነሱ በምንም አያንስም እንደውም የኔ ውብ ሳይበልጥ እንዳልቀረ አንቺን ልጠይቅሽ። ነው! እንደ ውሻ እግርሽ ስር ልንሞሽሞሽ እንደ ሠለሞን ክጄ ጣኦቴ ላድርግሽ የሷ ነኝ እያልኩኝ በአንቺ ልማልብሽ። ፍፁም ለማፈቅርሽ ግን ለማላገኝሽ ✍️ ባር
    2 861
    15
    ​​​​​                   ሴትን አላምንም ክፍል 9 Semir ami እልፍ አእላፍ ሰዎች በድንኳኑ ዙሪያ ላይ ቁመዋል በሀዘን ልባቸው የተሰበረ ፣ ለእንባቸው ገደብ አላበጅ ያሉ ሴቶች ይታዩኛል። የማየው ነገር ህልም እንጂ እውን አይመስልም "እኔን ልጄ" የሚሉ የሲቃ ድምፆች ከትላልቅ እናቶች  ይሰማል። ውሃ ሆንኩኝ ፤ እየተርበተበትኩኝም ቢሆን ወደ ድንኳን ውስጥ ገባሁኝ ክፍት ወንበር ስቤ ተቀመጥኩኝ ማንን ልጠይቅ? አህላም የት ሄደች? ማንስ ነው የሞተው? መልስ የሚያስፈልጋቸው ጥያቄዎቼ የኔን የነገን ተስፋ በጉልህ የሚያሳዩ ወሳኝ ነጥቦች። ………" ልጇ ደህና ነው ሙቀት ክፍል ገብቷል ሚስኪን በወጣትነቷ ተቀጨች እስከ መቼ ድረስ ነው ግን በወሊድ ምክንያት የሚከሰት ሞት የሚያበቃው"የሚል ድምፅ ከወደ ጆሮዬ ዘልቆ ገባ … ልሳቅ ፣ ወይስ እልል ብዬ ድንኳኑን የሰርግ አዳራሽ ላስመስለው? የጐመዘዝው ህይወቴ ወደ ጣፋጭነት ሲቀየር ታየኝ ፣ የጠፋው ብርሃኔ ደምቆ ሲበራ ታየኝ። አህላም አልሞተችም እነሱ ጋር ግን የሆነ ሰው ሞትዋል ፤ ሞት ደሞ ለማንም አይቀርም መቅረት ያለበት ደግሞ ለአህላም ብቻ ነው አህላም አልሞተችም። ልቤ ተረጋጋ ፤ ሰው እንዴት ለቅሶ ላይ ሟችን ያማርጣል የዚህች ልጅ መሞት ህልሙን የሚያጨልምበት ስንት ሰው አለ ? ጨካኝ! አልኩት እራሴን… ለራሴ ደስታ ስል በሰዎች ሞት ላይ ምሳለቅ ፍቅር ወይስ እራስ ወዳድነት ብቻ አላውቅም የማውቀው አህላም አለመሞቷን ነው። …… ድንኳኑን ለቅቄ ስወጣ በአይን የማውቀው የግቢያችንን ተማሪ አየሁት ጠጋ ብዬ ሰላም እንዴት ነህ? የሚለው ጥያቄዬ አስቀደምኩኝ እሱም ሞቅ ያለ ሰላምታውን ከሰጠኝ በሗላ ማን ሞቶ ነው? አልኩት የሟችን ትክክለኛ ማንነት ለማረጋገጥ የክላሳችን ተማሪ እህት ነች ድንገት በወሊድ ምክንያት ነው የሞተችው አለኝ። oh የአህላም እህት አላህ "የጀነት" ይበላት አመሰግናለው ሰላም ሁን ብዬው አልፍኩኝ ማታ ደግሜ ስለመምጣ  ወደ ትምህርት ቤት መሄድ ነበረብኝ ላዳው ውስጥ ገብቼ ወደ ትምህርት ቤት አቀናሁኝ ፤ አነዛን አስጠሊታ እና አስቀያሚ ምሽቶችን አልፌ ዛሬን ደርሻለው።  አይ ፍቅር እስረኛ አድርጐኛል ያውም በአንድ ጠባብ ክፍል ውስጥ የሚያሳዝነው ያሰረችኝ መታሰሬን ፣ በእስሩ ውስጥ የሚደርስብኝን ስቃይ ምንም አታውቅም እሷም  ዛሬ የሀዘን እስር ቤት ላይ ነች። እኔም ጋር ድንኳን አልተደኮነም እንጂ የምወዳትን ልጅ ሳላይ 2 ቀን ሞልቶኛል ታድያ ከዚ በላይ ለእኔ ምን ዱብዳ አለ።  ምሽቱን እነ አህላምዬ ጋር ላሳልፍ ብዬ ከትምህርት ቤት መልስ መኪና አስፈቅጄ ለቅሶ ቤት ሄድኩኝ። ከቀኑ ቀለል ያለ ሰው ቢኖርም አሁንም ሰዎች ይታያሉ አህላምን ማግኝት አለብኝ ግን እንዴት? የቤተሰቡ አባል የሚመስል ሰው ውሃ ይዞልኝ መጣ እኔም "ይቅርታ" ወንድም አህላምን  ማግኝት እችላለው?  ከተረጋጋች አልኩት? ትኩር ብሎ አይቶኝ ይቻላል ማን ብዬ ልንገራት? ማን ይበላት? በመከራ ውስጥ ሆኖ ስለ አንቺ የሚያስበው  ፣ ጦርነትም ውስጥ ሆነ ስለ አንቺ ሰላም በብዙ የሚጨነቀው ፣ በመሞት ውስጥ ሆኖ ስለ አንቺ  በህይወት መኖር የሚያሳስበው፣ ወንጀለኛ ሆኖ ስለ አንቺ ፅድቅ ከእራሱ በላይ የሚያስጨንቀው  ሰኢድ ይበላት? ሰኢድ... ሰኢድ በላት አልኩት ከሃሳቤ መለስ ብዬ። …… ብዙ ሳይቆይ አህላምን ይዟት መጣ… ልጁንም  የመልካም ሰው መገለጫ አድርጌ አሰብኩት ፣ የፈረሰውን የፍቅር ድልድይ ገንቢ መሃንዲስ ነው ብዬ መሰከርኩለት ፣ የፍቅር ጥም ቆራጭ መልካም ሰው ከቶ ከሱ ውጪ እንዴት ይኖራል? አህላምዬ አዝናለች ቢሆንም ግን በመምጣቴ ደስ ሳትሰኝ አልቀረችም ያንን ከውሃ እና ከምግብ በላይ አስፈላጊ መስሎ የሚታየኝ ፈገግታዋን ቸረችኝ። ወደ መንገዱ እየተራመድን አህላምዬ? አቤት… እንዴት ነሽ በረታሽ? አልሃምዱሊላህ ምን ማድረግ ይቻላል አላህ ያመጣውን አምኖ መቀበል ግድ ይላል። "አብሽሪ አላህ ሶብር ይስጣቹ ከህይወት አስቀያሚ ነገር  ውስጥ የሚወዱትን ሰው ማጣት ነው። ሀዘንሽ ከልብ ይገባኛል ግን ሁሉም ወደ ማይቀረው ሀገር ተጓዥ ነው ፤ ሁሉም እንደ ታክሲ ሰልፍ በሞት መስመር ላይ ተሰልፎ ተራውን እየተጠባበቀ ነው ህይወቱን እየገፋ ያለው ፣ ተረኛ ሟችም በሰልፉ መስመር እስከቆመ ድረስ ጊዜው ሲደርስ መሞቱ አይቀርም። ዋናው ቁም ነገሩ መሞት አይደለም ከሞት በሗላ ያለ ህይወት ነው ሞትማ ለማን ይቀራል? ለዚህ አይደል የነገ ሟች የዛሬን ሟች ይሸኛል የሚባለው።  በርታ በይ ፤ በርትትሽ ቤተሰቦችሽን አበርቺ " ሰው ከሰው ሲለያይ አይደለም ወረቀትም ከወረቀት ላይ ሲቀደድ የስቃይ ድምፅ አለው" ሀዘንሽን እረዳለው እኔም አባቴን አጥቼ  በብዙ ተሰቃይቻለው። ግን መመለስ በማይቻል ነገር ላይ ቆዝሞ ማሳለፍ ትርፉ ሌላ ህመም ነው ትእግስት ፍሬዋ ጣፋጭ ነው ታገሺ።……… የገፋትን ሃይል ባላቅም እንባ እየተናነቃት እቅፌ ውስጥ ገባች  …… ከልብ አመሰግናለው  አውቃለው ለህይወትህ ትርጉም የነበረውን ሰው ካጣህ በኃላ የህይወትን ጠአም ማግኘት ከባድ ነው ። ግን ዛሬ አንተን በማወቄ እድለኛ እንደሆንኩኝ ተሰምቶኛል ፤ ብዙ ሰው ያቃተው በደስታህ ጊዜ አብሮ መኖርና ማሳለፍ ሳይሆን በችግርና በመከራ ጊዜ ከወዳጁ ጎን ሆኖ ሀዘኑንና ስቃዩን አብሮ መካፈል ነው ዋናዉ ይህ ነዉ ሰኢዲዬ በሀዘኔ በህመሜ ሰዐት ከጎኔ በመሆን እና ብርታትና  ጥንካሬ እንዳገኝ ስለመከርከኝ የዛሬዋን ምክር አልረሳም ብላኝ አይንዋ ላይ የቀረውን እንባ አፈሰሰችው። እኔ እንባ የለኝም ትላንት ማታ ስለ እርሷ እያሰብኩኝ እያለው አንዲት የእንባ ዘለላ ቁልቁል በጉንጮቼ ኮለል ብላ ወረዳለች። እኔም "ወዴት ነው የምትሄጂው?"  በማለት ስጠይቃት በአይንህ ውስጥ የምትወዳት ሴት አለች "ለእኔ የሚሆን ቦታ አላገኘውም"  ብላኝ ከሄደች ቆይታለች ታድያ አይኔ ውስጥ አህላም ገብታ ለቅሶዬ ኬት ይምጣ።… … አህላምዬ እራስሽን ጠብቂ ነገ እመጣለው ብዬ ተሰናብቻት ሄድኩኝ ፤ ባትሄድ ደስ ይለኛል የሚል ድምፅ ሰምቼ ቆምኩ ሰውነቴ አንዳች የፍቅር እና የመፈለግ ስሜት ወረረኝ እኮ አህላም እኔን እንዲ አለችኝ?  ፊቴን አዙሬ…  ልመለሳ? አልኳት…  አይ መሽቷል ቤት ማሚ ትጠብቅሃለች ስገባ ደውልልኝ አለችኝ። ልቤ ፈነደቀ አህላምን ያገኝሗት መሰለኝ።  መኪና ወዳቆምኩበት ስፍራ እየተራመድኩኝ አንዳች ስሜት ዙር አለኝ ፊቴን አዙሬ ስመለከት አህላም ቁማለች  ደነገጥኩኝ…  ቀድማኝ እጇን አንስታ ቻው አለችኝ እኔም ቻው ብዬ በእጄ እንድትገባ ምልክት ሰጠዋት።  በፍጥነት መኪናዋን አስነስቼ ወደ ቤት ገሰገስኩኝ ልቤ ሀሴት አርድጓል አዲስ እድል አዲስ ቀን አዲስ ህይወት … ድንገት አንድ ነገር ታወሰኝ እና ፈገግ አልኩኝ ማሚ ሁሌም አንድ የሚያስቃት ግጥም አለ እሱን ትልና ትስቃለች። ሚስቴና ሰበቧ · · ለስጋዋ ስትኖር ነፍሴን አሞኝታ አገኘኋትና ወንድ ጋር ተኝታ ምነው ምን በደልኩኝ? ብዬ ስጠይቃት እግሯ ስር ወድቄ በእንባ ስማፀናት እንደለመደችው ሰበብ አዘጋጅታ አንተ መስለኸኝ ነው አለችኝ ተነስታ።። ስልኬ ጮኸ የቴክስት ድምፅ ነው መኪናውን ዳር አቁሜ ሳየው አህላም ነች።             ክፍል አስር ይቀጥላል….......
    Show more ...
    2 922
    3
    . . . . . . ❤️ፍፃሜው የሚያምር ቅርብ ማንነት ግልፅነት ሚያስተምር .. .. .. ርህራሄ እና ለሰው ማዘንን በልብ የሚያኖር💗 ከፈጣሪ የሚገኝ ፀጋ ነው።💖 ❤️ፍቅር የሚመሠረተው . . . አንድ ነፍስ በሁለት. . . አካል ሲኖር💕 ነው፡፡ 💓 ምንጊዜም በቂ ነገር አሟጠን የማናገኝበት ነገር ፍቅር ነው፡፡ 💖 እውነተኛ ፍቅርን አግኝተህ ከተንከባከበው . . . እራስህን በምድር ላይ ካሉ ጥቂት እድለኞች💗 መሀል አንዱ ነህ፡፡ ❤️ፍቅር የተለየ ቀን ልዩ ቦታና ድርጊት አይፈልግም . . . በድንገት ሳይጠበቅ ይከሠታል፡፡💝 💞 💞 ✍️ባርሙራ
    4 024
    29
    Last updated: 11.07.23
    Privacy Policy Telemetrio