ኢና ሊላህ ወኢና ኢለይሂ ራጂዑን !
ከጎንደር ከተማ ወደ መተማ ስንሄድ በማእከላዊ ጎንደር ደንቢያ ወረዳ አየንባ ቀበሌ ሸኽ ሲራጅ የመስጅዱ ኢማም መግሪብ ሰላት ሰግደዉ ሲወጡ በታጣቂዎች ተይዘዉ ከሄዱ በሃላ በአሰቃቂ ሁኔታ በጥይት ደብድበዉ ገድለዋቸዋል ።
ሸኽ ሲራጅ በዛዉ መስጅ ለረጅም አመት ደረሳዎችን እስከዛሬዋ እለት ያቀሩ የነበሩ ሲሆን መግሪብን አሰግደዉ ሲወጡ ታጣቂዎቹ እየጎተቱ የወሰዷቸዉ መሆኑና ይህን የሀገር ሽማግሌ የሁሉ አባት የሆኑት የመስጅድ ታላቁን ሸኽ ገድለዉ ጥለዋቸዉ እንደሄዱ ሰማን ።
በተፈጠረዉ ነገር በጣም እያዘንኩ ሸኻችን አሏህ ከሸሂዶች ተርታ እንዲያደርጋቸዉ እየለመንኩ ለቤተሰቦቻቸዉ መፅናናትን እመኛለሁ ።