'
•••✿ ❒ ነብዩሏህ አደም ዐለይሂ ሰላም ❒✿•••
#ክፍል 2
አደምም እማያውቀው ቦታ ላይ አንድ አጫዋች በሌለበት ቁጭ ብሎ የድብርት ስሜት ተሰማው። ከዝያም ጋደም ባለበት ድንገት እንቅልፍ ሸለብ አደረገው። ልክ ከእንቅልፉ ሲነቃ እራስጌው ላይ አንዲት ሴት ተመለከት ከአይኖቿ ፍቅር እና እዝነት ይነበብባታል።
አደም፦"ከመተኛቴ በፊት እዚህ አልነበርሽም"
ሀዋ፦"አዎ"
አደም፦"በተኘሁበት ነው የመጣሽው ማለት ነዋ!!!"
ሀዋ፦"አዎ"
አደም፦"ኬት ነው የመጣሽው"
ሀዋ፦"ካንተ ውስጥ ነው የመጣሁት።አንተ በተኛህበት ነው አላህ ካንተ የፈጠረኝ።
አደም፦"ለምንድነው አላህ የፈጠረሽ?"
ሀዋ፦"አንተ እኔ ላይ ልትረጋ"
አደም አላህን አመሰገነ'ና፦'ብቸኝነት እየተሰማኝ ነበር" አለ።
ከዚያም መላዕክት መጡ'ና፦"ስሟ ማን ነው?" አሉት።
አደምም፦"ሀዋ" አለ።
መላዕክትም፦"ለምንድነው ሀዋ ተብላ የተሰየመችው" ብለው ሲጠይቁት
አደምም፦'እሷ ከኔ ነው የተፈጠረችው እኔ ደግም ህያው ነኝ ለዛ ነው ሀዋ ያልኳት"ብሎ መለሰላቸው።
ከዚያም አድም እና ሀዋ በጀነት ውስጥ ሳሉ አላህ አደምን እንዲህም አለው፦"አንተ አደም ጀነት ውስጥ ላንተ ሁሉ ነገር ሀላል ሲሆን ይህችን ቅጠል ላንተም ለሚስትህም ሀራም አድርጌያለሁ'ና እንዳትቀርቧት"
ከዚያም ሁለቱም በጀነት እየተዝናኑ ሳለ ኢብሊስ መጣ'ና አጠገባቸው ማልቀስ ጀመረ። ፦"ምን ሁነሀል?" ብለው ሲጠይቁት እንዲህ በማለት መለሰላቸው፦
"እንዲህ ስትዝናኑ በጣም ታምራላችሁ ግን በጣም እኔ ሚያሳዝነኝ ይሄ ደስታችሁ ዘለቄታ አይኖረውም።ግን ይህ ደስታችሁ ዘላለማዊ እንዲሆን ምትፈልጉ እንደሆን ይህችን ቅጠል ብሏት።ምክንያቱም አላህ ጌታችሁም መልኣኮች እንዳትኾኑ ወይም ከዘላለም ነዋሪዎች እንዳትኾኑ እንጂ ከዚህች ዛፍ አልከለከላችሁም" ብሎ በመወስወስ አሳስቶ ቅጠሏን አበላቸው።
(በነገራችን ላይ አንዳንድ ሰዎች በውድቅ ንግግሮቻቸው ሴቶችን መውቀስ ሲፈልጉ ፨ሀዋ ናት አደምን ያሳሳተችው፨ ይላሉ ይህ ከእውነት የራቀ ነው ሀዋ አይደለችም ቅጠሉን እንዲበሉ የገፋፋችው።ሁሉቱም ናቸው ተሳስተው የበሉት።)
አደም በስህተት የቀመሳትን ቅጠል መብላት ሲጀምር ልቡን እያመመው መጣ...ፍርሀት እና አለመረጋጋት ነገሰበት።
ዞር ብሎ ሚስቱን ሲያይ እርቃኗን ናት። እራሱንም ሲመለከት እርቃኑን መሆኑ ታወቀው። ከዚያም ቅጠል በመበጠስ ሀፍረተ ገላዎቻቸውን መሸፈን ጀመሩ። በፈፀሙትም ሀፅያትም ተፀፅተው እንዲህ በማለት አላህን ይማፀኑ ጀመር፦" ጌታችን ሆይ! ነፍሶቻችንን በደልን፡፡ አንተ ለእኛ ባትምር ባታዝንልንም በእርግጥ ከከሳሪዎቹ እንኾናለን"
አላህም ወደ ምድር እንዲወርዱትዕዛዙን አስተላለፈ እንዲህም አላቸው፦" ከፊላችሁ ለከፊሉ ጠላት ሲኾን ውረዱ፡፡ ለእናንተም በምድር ላይ እስከ ተወሰነ ጊዜ ድረስ መርጊያና መጠቀሚያ አላችሁ።
በእርሷ/በምድር ላይ ትኖራላችሁ፡፡ በእርሷም ላይ ትሞታላችሁ፡፡ ከእርሷም ውስጥ ትወጣላችሁ" አሁን አደም እና ሀዋም ጉዞ ወደ ምድር....
አላህ ሁለቱንም ወደ ምድር ሲያወርዳቸው አደም ትካዜ ተቆጣጠረው፣ እጅጉን ሀሳብ ገባው...ሀዋ ደሞ ማልቀስ የሌት ተቀን ተግባሯ ሆነ።
ከዚያም አላህ ለሁለቱም፦"ምድር እኮ እናንተ የመጣችሁበት ምንጫችሁ ናት።ከአፈር ነው የተፈጠራችሁት ወደአፈር ነው ምትመለሱት...ከአፈርም ነው ምትቀሰቀሱት" እያለ አፅናናቸው።
ከዚያም አደም እና ሀዋ መሬት ላይ ቁጭ ብለው ሳለ ጂብሪል( ዐ.ሰ ) 7 የስንዴ ፍሬዎችን ይዞለት መጣ እያንዳንዱ ፍሬ 70ሺህ ዘለላ ያበቅል ነበር።አደምም ለጅብሪል፦"ምን ላድርገው" አለው።
ጂብሪልም፦"መሬት ላይ ዝራው" አለው።
አደምም ዘራው'ና ጂብሪል እያሳየው አጨደ።
አዚያም ፈጨው...ከዚያም አቦከው...ከዚያም ጋገረው እና ሲቀዘቅዝ ከባለቤቱ ጋር በመብላት የህይወትን ውጣ ውረድ ይላመድ ጀመር...
ሁለቱም ሚለብሱት ነገር ስላልነበራቸው በግ አረደ'ና ቆዳውን ለራሱም ለሷም ልብስ ሰርቶ ለበሱ። እንዲ እንዲ እያሉ የህይወትን ውጣ ውረዶች ለመዱት ልጆችም መውለድ ጀመሩ።ሀዋ ሁሌ ምትወልደው መንታ መንታ ነበር አንድ ወንድ እና አንድ ሴት...ልጆቻቸውን ሲያጋቡ በአንድ ላይ የተወለዱትን አያጋቡም ነበር አንድ ላይ የተወለዱት ሴቷ በሌላ ግዜ የተወለደውን ወንድ ስታገባ ወንዱም እንደዛው።
እናላችሁ አንድ ግዜ ሀቢል እና ቃቢል የተባሉ የአደም ልጆች ሁለቱም መንትያ እህቶች አሏቸው እና ሀቢል የቃቢልን እህት(አብራው የተወለደችውን) ማግባት ፈልጎ ሲጠይቅ ቆንጆ ስለነበረች ቃቢል ለራሱ ፈልጓት ለሀቢል ከለከለው።
አደምም ቃቢል እህቱን ለሀቢል እንዲድርለት ሲጠይቅም ፍቃደኛ አልሆን አለ።ከዚያም አደምም ለሁለቱ ልጆችቁርባን እንዲያዘገጁ አዘዛቸው'ና አድም ሀጅ ሊያደርግ ወደ መካ ተነሳ(ሀጅ በኢብራሂ ግዜ የተጀመረ እንዳይመስላችሁ ድሮም ቦታዋ ትታወቃለች)
ከዚያም አደም ልጆቹን የሚያስጠብቀው አካል የለም'ና ሰማያትን ልጆቹን እንዲጠብቁ አደራ ሲል እንቢ አሉ...ምድርንም ሲጠይቃት እንቢ አለች ተራራዎችንም ሲለምን ሀላፊነት መውሰድ ሀሉም ፈሩ።ግን ልጁ ቃቢል እኔ እወስዳለሁ ብሎ የአደምን ልጆች ሀላፊነት ቃቢል ተሸከመ። አደምም ጉዞውን ቀጠለ..
አደም ከሄደ በኋላ ልጆቹ ሀቢል እና ቃቢል ልጅቷን ለማግባት ለአላህ ቁርባን አቀረቡ።ሀቢል እረኛ ነገር ስለነበር ጥሩ የሚያምር ለአይን ሚማርክ ሙኩት አቀረበ...ቃቢል ደሞ ገበሬ ነበር ግን ተራ ውዳቂ እህል ነው ያቀረበው።
የሁለቱም ቁርባኖች አንድ ቦታ ሳሉ ከሰማይ እሳት ወረደች'ና የሀቢልን ቁርባን በላች(ቁርባኑ ተቀባይነት አግኝቷል ማለት ነው) የቃቢልን ግን ተወችው።(አላህ አልተቀበለውም ማለት ነው)
ያን ግዜ ቃቢልም፦"እህቴን ምታገባ እንደሆን እገድልሀለሁ" አለው ሀቢልን።
ሀቢልም፦"አላህ የሚቀበለው ከጥንቁቆች(እሱን ከሚፈሩት) ነው" አለው።
ያን ግዜ ቃቢልም ወንድሙን ሀቢልን በያዘው ብረት ጭንቅላቱን መቶት ጣለው።(ስለአገዳደሉ የኡለማኦች ልዩነት አለ እሱን ልዘረዝር አልፈልግም)
ቃቢል ወንድሙን ከገደለው በኋላ ሬሳውን ምን እንደሚያደርግ ጠፍቶበት አንድ አመት ሙሉ በጀርባው ተሸክሞ ሲዞር ከርሟል ይባላል።
በዚህ ሁኔታ ላይ ሳለ አንድ ቀን የወንድሙን ሬሳ እንዴት እንደሚሸሽግ ያሳየው ዘንድ አላህ መሬትን የሚጭር ቁራ ላከለት፡፡ ቃቢልም፦«ወይ እኔ የወንድሜን ሬሳ እሸሽግ ዘንድ እንደዚህ ቁራ ብጤ መኾን አቃተኝን» አለ፡፡ ቃቢል ወንድሙን ሀቢል ከቀበረው በኋላ በመግደሉ በጣም ተፀፀተ። አደምም የልጁን ሞት ሲሰማ በከፍተኛ ሁኔታ አዘነ።
ክፍል 3 ይቀጥላል .....
#share
@alahu_akber1Show more ...