እውን ቁርኣን የአላህ ቃል አይደለምን?
~
ቁርኣን የአላህ ቃል ለመሆኑ የሚጠራጠር ሙስሊም የለም። ሙስሊሙ ልጆቹን ቁርኣን እንዲቀሩለት ያላሰለሰ ጥረት የሚያደርገው፣ ያለ ውዱእ የማይነካው፣ ጧት ማታ የሚቀራው፣ የሚማረው፣ የሚያስተምረው፣ ማስረጃ አድርጎ የሚያጣቅሰው፣ የሚተገብረው “ቁርኣን የጌታዬ ንግግር ነው” ከሚል ፅኑ እምነት ተነስቶ ነው።
ግና የፈጣሪ ቃል የማይገታቸው፣ የሰለፎች ኢጅማዕ የማይከብዳቸው ሃፍረተ ቢስ ፍጡሮች ተተኩና “ቁርኣን የአላህ ሳይሆን የሙሐመድ ወይም የጂብሪል ቃል ነው” አሉ። አሻዒራ! አሕ^ባሽ የዚህ ቡድን ተቀፅላ ነው። ይህ እምነታቸው {ይህ የሰው ቃል እንጂ ሌላ አይደለም} ያለውን ሙሽ'ሪኩ ወሊድ ብኑ ሙጊራን ያስታውሰናል። [አልሙደሢር፡ 25] በተውሒድ ስም የነ አቡ ጀህል ዐቂዳ ዳግም ሲሰበክ አስቡት! የአሕ^ባሾቹ ቁንጮ ዐብደላህ አልሀረሪም ቁርኣን የጂብሪል እንጂ በሐቂቃ የአላህ ንግግር አይደለም ከሚሉት ነው። በቅርቡ ፌስቡክ ላይ ተዋሽቶበት እንጂ እሱ እንደዚህ አይልም የሚል ወዶ ገብ አሕባሽ ስላየሁኝ ንግግሩን ላጣቅስ፡-
فهو عبارة عن كلام الله بمعنى أنه يحكي كلام الله، ليس هو بنفسه كلام الله
“እሱ (ቁርኣን) የአላህን ንግግር የሚገልፅ ነው፡፡ ማለትም የአላህን ንግግር የሚተርክ ነው፡፡ እንጂ በራሱ የአላህ ንግግር አይደለም፡፡” [አደሊሉል ቀዊም፡ 66 - 69]
ሰውየው ምን ያክል ሙጅ' ሪም እንደሆነም ተመልከቱ፡፡ አዎ “ሙጅ^ሪም ነው” ሲባል የሚከፋው እንደሚኖር አይጠፋኝም፡፡ ግና ቁርኣንን የአላህ ቃል አይደለም ከማለት በላይ ምን አይነት ብል ^ግና አለ?! የሸሪዐ ግንዛቤ የሌለው ጃሂል እንኳ እንዲህ አይነት ጥፋት አይፈፅምም፡፡
"ኪታቦቹ ላይ ‘አላህ እንዲህ ብሏል’ እያለ ቁርኣንን ማጣቀሱ ‘ቁርኣን የአላህ ንግግር ነው’ ብሎ እንደሚያምን ያሳያል" በማለት ማስረጃ ሊያደርጉለት የሚሞክሩ አሉ፡፡ ሰውየው በማያሻማ ቃል “ቁርኣን በራሱ የአላህ ንግግር አይደለም” እያለ አጉል መንደፋደፍ የትም አያደርስም፡፡ “እሺ ‘አላህ እንዲህ ብሏል’ ሲል ምን ማለቱ ነው?” ከተባለ ይሄው እራሱ ሃሳቡን ግልፅ ያደርግላችኋል፡-
فكلام الله النفسي الذي ليس هو حرفا ولا لغة هو كلام الله الحقيقي؛ أما القرآن المتضمن للألفاظ فهو مخلوق، لكن يمكن إطلاق لفظ القرآن عليه من باب المجاز
“ፊደልም ሆነ ቋንቋ ያልሆነው ነፍሳዊ የሆነው የአላህ ንግግር እርሱ ነው በተጨባጭ የአላህ ንግግር የሚባለው፡፡ ቃላትን የያዘው ቁርኣን ግን እርሱ ፍጡር ነው፡፡ ባይሆን ከዘይቤያዊ አነጋገር አኳያ ቁርኣን (የአላህ ንግግር) በሚል ቃል ሊጠራ ይችላል፡፡” [አነህጁ ሰሊም፡ 26]
የዚህ የዐብደላህ አልሀረሪ ንግግር ጭብጥ፡-
- ትክክለኛው የአላህ ንግግር በፊደልም ሆነ በቋንቋ አይገለፅም፣
- በእጃችን ላይ ያለው ቁርኣን ግን በፊደልም በቋንቋም ስለሚገለፅ ፍጡር እንጂ በሐቂቃ የአላህ ንግግር አይደለም፣
- ሆኖም ግን በራሱ የአላህ ንግግር ባይሆንም፣ የአላህን ንግግር ስለሚተርክ በሐቂቃም ባይሆን በዘይቤያዊ አነጋገር ‘ቁርኣን’ (የአላህ ንግግር) ተብሎ ሊጠራ ይችላል እያለ ነው፡፡
ስለዚህ “አላህ እንዲህ ብሏል” ሲል የሚፈልገው በዚህ አገባብ ማለትም ዘይቤያዊ አነጋገርን በማሰብ እንጂ በሐቂቃ ቁርኣን የአላህ ንግግር ነው ለማለት አይደለም፡፡ ይሄ ከንቱ ዐቂዳ አሕ^ባሽ ከወላጁ አሻዒራ የቀዳው እንደሆነ ይሰመርበት፡፡ [አልኢንሷፍ፡ 147] [ሸርሑ ጀውሀረት ተውሒድ፣ አልበይጁሪ፡ 73] [ሸርሑ ጀውሀረት ተውሒድ፣ አሚር]
ይስተዋል! እነዚህ ሰዎች ለሽፋን ያክል ብቻ ቁርኣን የአላህ ንግግር ነው ይላሉ። “የሐቂቃ ነው ወይ?” ስትሉ ግን ጉዳቸው ይከተላል። በዘይቤያዊ አነጋገር (መጃዝ) የአላህ ቃል ተባለ እንጂ በተጨባጭ ግን የአላህን ንግግር የሚገልፅ፣ የሚተርክ (ዒባራ/ ሒካያ) እንጂ የጂብሪል ንግግር ነው ይላሉ። ለዚህ ብልሹ እምነታቸውም ይህቺን አንቀፅ ይጠቀማሉ፡-
إِنَّهُ لَقَوْلُ رَسُولٍ كَرِيمٍ
“እርሱ በርግጥም የክቡር መልእክተኛ ቃል ነው።”
ይህ መልእክት ቁርኣን ውስጥ ሁለት ቦታ ይገኛል፡፡ [አተክዊር፡ 19] [አልሐቃ፡ 40] በሱረቱ ተክዊር ላይ የተገለፀው “መልእክተኛ” ጂብሪል ሲሆን በሱረቱል ሐቃ ላይ ደግሞ ሙሐመድ ﷺ ናቸው። ይህም አንዱን መዞ ሌላኛውን በመተው “የጂብሪል ነው” “የለም የሙሐመድ ነው” የሚሉ ሞገደኞችን ቅርቃር ውስጥ የሚከት ነው። ከዚህ ቅርቃር መውጫው ለቁርኣኑ ሙሉ በሙሉ እንጅ መስጠት ብቻ ነው። ጂብሪልም ሆነ ሙሐመድ ﷺ መልእክተኞች እንጂ ሌላ አይደሉም። የመልእክተኛ የስራ ድርሻ ደግሞ ማድረስ ነው።
{وَمَا عَلَى الرَّسُولِ إِلَّا الْبَلاغُ الْمُبِينُ}
“በመልእክተኛውም ላይ ግልፅ ማድረስ እንጂ ሌላ የለበትም።” [አኑር፡ 54]
ቁርኣኑ ተጠብቆ እንደደረሰ ለማመላከት የሸይጧን ሳይሆን የመልአክ፣ የጠንቋይና የገጣሚ ሳይሆን የመልእክተኛ ቃል እንደሆነ ተገለፀ። ከአስተላላፊነታቸው አንፃር ብቻ ሲታይ አንድ ቦታ የጂብሪል፤ ሌላ ቦታ የሙሐመድ ﷺ ንግግር ተብሏል። እንጂ ጂብሪል ተቀባይ እንደሆነ እንዲህ ፍንትው ብሎ ተቀምጧል’ኮ፡-
(قُلۡ نَزَّلَهُۥ رُوحُ ٱلۡقُدُسِ مِن رَّبِّكَ بِٱلۡحَقِّ)
{‘ቅዱሱ መንፈስ በእውነት
#ከጌታህ አወረደው’ በላቸው።} [አነሕል፡ 102]
ይሄው የጂብሪል የራሱ ንግግር ሳይሆን ከአላህ ተቀብሎ ያወረደው እንደሆነ በግልፅ እየተነገረን ነው፡፡ ከዚህ በኋላ ልብ የሚያንሸራትት ሞገ^ደኛ ቢኖር አላህ ቅናቻን እንዲያድለው ከመማፀን ውጭ ምን እእናደርገዋለን? በተጨማሪም አላህ እንዲህ ብሏል፡-
وَإِنَّهُ لَتَنْزِيلُ رَبِّ الْعَالَمِينَ (192) نَزَلَ بِهِ الرُّوحُ الْأَمِينُ (193) عَلَى قَلْبِكَ لِتَكُونَ مِنَ الْمُنْذِرِينَ (194)
{እርሱም በእርግጥ
#ከአለማት_ጌታ_የተወረደ ነው። ታማኙ መንፈስ አወረደው። ከአስፈራሪዎቹ (ነቢያት) ትሆን ዘንድ በልብህ ላይ (አወረድነው)፡፡} [አሹዐራእ፡ 192-193]
ስለዚህ ጂብሪል ከራሱ ሳይሆን ከጌታ ተቀብሎ ነው ይዞት የወረደው። እንጂ ቁርኣኑ የአላህ ንግግር ለመሆኑማ እንዲህ ተነግሮናል’ኮ፡-
(وَإِنۡ أَحَدࣱ مِّنَ ٱلۡمُشۡرِكِینَ ٱسۡتَجَارَكَ فَأَجِرۡهُ حَتَّىٰ یَسۡمَعَ كَلَـٰمَ ٱللَّه)
{ከአጋሪዎቹም አንዱ ጥገኝነትን ከጠየቀህ
#የአላህን_ንግግር ይሰማ ዘንድ አስጠጋው።} [ተውባህ፡ 6]
ነብዩም ﷺ በዐረፋ ሐጅ ላይ ለታደመው ህዝብ እንዲህ ይሉ ነበር፡-
أَلاَ رَجُلٌ يَحْمِلُنِى إِلَى قَوْمِهِ فَإِنَّ قُرَيْشًا قَدْ مَنَعُونِى أَنْ أُبَلِّغَ كَلاَمَ رَبِّى
Mostrar más ...