መቻል በፎርፌ አሸንፏል !
ወልቂጤ ከተማ ተጫዋቾች የክለብ ላይሰንሲግ ፈቃድ አለማግኘታቸው ተከትሎ መቻል በፎርፌ የጨዋታው አሸናፊ ሆነዋል።
በዚህም መሰረት መቻሎች ሦስት ነጥብ እና ሦስት ግቦች አግኝተዋል።
ወልቂጤ ከተማ በተጨማሪ በውድድሩ ደንብ መሠረት ከ30ሺህ ብር በላይ የገንዘብ ቅጣት የሚጠብቃቸው ይሆናል።
ወልቂጤዎች በሁለተኛው የጨዋታ ሳምንት ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጋር በሚያደርጉት ጨዋታ የክለብ ላይሰንሲግ ፈቃድ በድጋሚ የማያሟሉ ከሆነ በውድድሩ ስነ ሥርዓት ደንብ መሰረት ከፍተኛ የገንዘብ ቅጣት እና ከውድድሩ እንዲታገዱ ከመደረጋቸው ባሻገር በታችኛው የውድድር ዕርከን(ከፍተኛ ሊግ)ወርደው እንዲጫወቱ ሊደረጉ እንደሚችል ተገልጿል።
SHARE
@MULESPORT