ጥልቅ ትንታኔ፡ በ
#ህወሀት አመራሮች መካከል የተፈጠረው ክፍፍል የ #ትግራይን ሰላምና የማገገም ሂደት አደጋ ላይ እየጣለ ይገኛል
በአንድ ወቅት በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ አብይ ፓርቲ የነበረው ህዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ (ህወሀት)፤ በአሁኑ ወቅት የትግራይ ክልል መረጋጋትን አደጋ ላይ ከሚጥሉና የመልሶ ማገገም ጥረትን ከሚያደናቅፍ ከባድ ውስጣዊ ክፍፍል ጋር እየታገለ ይገኛል። እነዚህ ውጥረቶች፤ ለሁለት ዓመታት በተካሄደው ጦርነት ሳቢያ በተከሰተው መፈናቀል እና በሰብአዊ ቀውሶች ተጎጂ በሆነው የክልሉ ህዝብ ላይ ተጨማሪ ስጋቶች አስከትለዋል።
ስማቸው ኢንዲጠቀስ ያልፈለጉ የ
#መቀለ ከተማ ነዋሪ፤ በትግራይ ያሉ የፖለቲካ አመራሮች “ህልውናቸው የማስቀጠል ጉዳይ ልዩነታቸውን በሰላማዊ መንገድ በመፍታት ላይ የተመርኮዘ የመሆኑን እውነታ መረዳት አልቻሉም” ሲሉ ገልጸዋል። ህወሀት “መግባባት ላይ የማይደርስ ከሆነ የትግራይን ህዝብ ወደ አስከፊ ሁኔታ መምራቱ የማይቀር ነው” ብለዋል።
የውድብ ናፅነት ትግራይ ፓርቲ ነባር አባል የሆኑት መሃሪ ግርማይ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ “የግጭትን ዋና መንስኤዎች ለመቅረፍ እና የሰብአዊ እርዳታ ተደራሽነትን ለማረጋገጥ፤ የክልል ምክር ቤት በአሳታፊ ሂደት ማቋቋም ወሳኝ ነው” ብለዋል።
የ
#መቀለ ዩኒቨርሲቲ መምህርና ተመራማሪ ገብረመድህን ያለው፤ ተቃዋሚ ፓርቲዎችን፣ ሲቪክ ማኅበራት ድርጅቶችን እና አጠቃላይ ህዝቡን ጨምሮ በርካታ ባለድርሻ አካላትን ያካተተ የመንግስት መዋቅር መመስረት አለበት ብለዋል።
@Yenetube @Fikerassefaادامه مطلب ...