ከስድስት ቢልየን ብር በላይ የሚፈጀው የህንዳውያን ባለሀብቶች ልጅ ሰርግ በመጪው ሐምሌ ይካሄዳል
111 ቢልየን ዶላር ሀብቱ የሚገመተው ህንዳዊው ሙኬሽ አምባኒ የመጨረ ልጅ አንንት አምባኒ የወደፊት ሙሽራው ራዲካ ባለፈው ሳምንት የቅድመ ጋብቻ በዓል አድርገዋል
ጥንዶቹ አርብ ዕለት በጎጅራት በሚኖሩበት መንደር ለ51,000 ሰዎች እራት አዘጋጅተዋል።
ቀጥሎም ትናንት እሁድ ማርክ ዙከርበርግ፣ ቢል ጌትስ፣ ኢቫንካ ትራምፕ እና ዘፋኝ ሪሃናን ጨምሮ 1,200 እንግዶች የተገኙበት እራት ግብዣ አርገዋል።
ለእንግዶች 500 አይነት ምግብ ቀርቦ ነበር።
በዚህ አመት በሀምሌ ወር ዋናው ሰርግ የሚካሄድ ሲሆን ጥንዶቹን 113 ሚሊየን ዶላር ወይንም ከስድሰት ቢልየን ብር በላይ ያስወጣል ተብሎ ይገመታል።
በሰርጋቸው ዕለት ለሚገኙ ዕንግዶች የአለባበስን አስመልክቶ ዘጠኝ ሉክ መመሪያ ተልኮላቸዋል።
Показати повністю ...