በዛሬው ዕለት መስከረም 10/2017 ዓ.ም
የጎንደር ፋኖ ጀብድ እጅን በአፍ ማስጫኑን ቀጥሎበታል።
ዛሬ መስከረም 10/2017 ዓ.ም የአማራ ፋኖ በጎንደር፦
ተከዜ ክ/ጦር፣ ራስ አሞራው ብርጌድ ላይ አርማጭሆ ልዩ ቦታው ሙሴአምባ ላይ ደፈጣ በመጣል በእንቅስቃሴ ላይ የነበረን መከላከያና ጸረ ሽምቅ ኃይልን አሳሩን ሲያሳየው ውሏል። ዛሬ በጠዋት 3:00 ሰዓት ላይ ሙሴአምባ ላይ ደፈጣ የጣለው በአርበኛ ዘነበ ገላ የተመራው የራስ አሞራው ብርጌድ ነበልባሎች በርካቶችን አቁስለው፣ በርካቶችን ወደፈጠራቸው ሸኝተው ከ20 በላይ መሣሪያዎችንም በምርኮ ታጥቀዋል።
#በሌላ ዜና በምዕራብ ጎንደር ገንዳ ውሃና መተማ ዮሐንስ አካባቢ ጎንደርን ከአራዊት ሠራዊቱ የማጽዳት ተግባር ተጠናክሮ ቀጥሏል። የአማራ ፋኖ በጎንደር፦ አጣናው ዋሴ ክ/ጦር እንዲሁም ካራማራ ክ/ጦርና የአማራ ፋኖ ጎንደር እዝ አርበኞች ክ/ጦር ቅንጅታዊ ኦፕሬሽን ከምዕራብ ጎንደር ዞን መቀመጫ ገንዳ ውሃ በ9 ኦራልና በ4 ፓትሮል የተጫነ አራዊት ሠራዊት ከገንዳ ዉሃ 7 ኪሜ ርቀት ልዩ ስሙ አፍጥጥ እሚባል ቦታ ላይ አቀባበል በማድረግ አነጋግረዋቸዋል። ከመጣው የአራዊት ሠራዊቱ ኃይልም 5ቱ ኦራል ሙሉ ለሙሉ ሲደመመስ የጫነው ዙ 23ንም በማቃጠል ከጥቅም ውጭ ተደርጓል። ከዚህ በተጨማሪም ከመተማ ዮሐንስ ማስከርን አልፈው ስትራቴጅክ ቦታን በመያዝ በሱዳን ጠረፍ ከገድላባት 17 ኪሜ ርቀት ላይ በኤሊኮፍተር የተራገፈውን የአብይ አሕመድ ጨፍጫፊ ቀይ ቦኔት ለባሽ ሠራዊት እንደከብት ነድተው በርካታውንም ደምስሰው መልሰውታል።
ኅልውናችን በተባበረ ክንዳችን!!!
የአማራ ፋኖ በጎንደር የሚዲያና ሕ/ግንኙነት መምሪያ
Показати повністю ...