የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና !
የሀገር አቀፍ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች ኤጀንሲ ከጥቅምት 29 እስከ ኀዳር 02/2014 ዓ.ም የሚሰጠውን የ2013 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተናን አስመልክቶ መግለጫ ሰጥቷል።
በመግለጫው የተነሱ ዋና ዋና ነጥቦች፦
• 617, 991 ተፈታኞች የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተናውን ለመውሰድ ተመዝግበዋል። ይህም ከባለፈው ዓመት የተፈታኞች ቁጥር በእጥፍ ይበልጣል።
• የፈተናውን ዝግጅት ለማስተባበር በተቋቋመው ኮማንድ ፖስት አማካኝነት ፈተናውን ወደ መፈተኛ ጣቢያ የማድረሱ ሥራ በተሳካ ሁኔታ ተከናውኗል። ለዚህም የየብስ እና የአየር ትራንስፖርት ግልጋሎት ላይ ውሏል።
• ፈተናው በመጀመሪያ ዙር የጸጥታ ችግር በሌለባቸው አካባቢዎች ይሰጣል ተብሏል።
• በአማራ ክልል በፌደራል በተወሰነ ውሳኔ መሰረት በደቡብ ወሎ፣ በሰሜን ወሎ በኦሮሞ ብሔረሰብ በዋግኽምራ ዞኖች፤ በሰሜን ጎንደር ዞን አዲአርቃይ ጠለምት ወረዳዎች፤ በሰሜን ሸዋ ዞን ኤፍራታና ግድም፣ አንጾኪያ ጋምዛ እና ግሼ ራበን ወረዳዎች በሁለተኛው ዙር ተካተዋል።
• በአጠቃላይ በአማራ ክልል 36, 340 ተማሪዎች ፈተናውን አይወስዱም ተብሏል።
• በሌሎች ክልሎች ያለውን የጸጥታ ሁኔታ ከግምት ውስጥ በማስገባት ወደ ሁለተኛ ዙር ሊጠቃለሉ እንደሚችሉ ተጠቁሟል።
• ፈተናውን ለመውሰድ ከተመዘገቡ ተማሪዎች ከ92 እስከ 94 በመቶ ያህሉ በፈተና ወንበራቸው ላይ ይቀመጣሉ ተብሏል። via: tikvahuniversity
@tamagnzena @tamagnzenaПоказати повністю ...