መ) ከዜማ ቤቱ ደግሞ ዮሐንስን በብሔረ ሕያዋን አየሁት የሚለን የኘቅዱስ ያሬድ ነው። በድጓው ደጋግሞ ምስክርነቱን ሠጥቶናል
«ይኔጽር ዓየራተ
ይነግር ኅቡዓተ
እንዘ ይጽሐፍ በእደዊሑ ዘወንጌል ቃላተ
በቅናተ እግዚኡ ሐቌሁ ቀነተ
ዮሐንስ ድንግል ዘኢጥዕመ ሞተ »
【በድጓ በግእዝ አርያሙ ክፍል ለጥር ፬ቱ ቁመት መነሻ እንዲሆን የጻፈልን ነው። ብራና ገጽ ፻፺፩】
በንጽሕና በድንግልና የኖረው ዮሐንስ ሞትን አልቀመሰም ይልና በሌላም ሥፍራ ከሞት ተለይቶ እንደመላእክቱ በሕይወት አለ ሲል ዳግመኛ ምስክርነቱን እንዲህ እያለ ያጸናዋል «በንጽሕ ከመ መላእክት ተሠርገወ ወእመዊት ከማሆሙ ሐይወ»
ሠ) በመልኩ ክፍልና በገድለ ሐዋርያት ማጠቃለያ የመሰወሩ ምስክርነት ተቀምጦ እናገኛለን
« ሰላም ለልብስከ ወለአሣእኒከ ደርገ፤
ተዝካረ ሕይወትከ ያዑቅ ለአብሮኮሮስ ዘተኃድገ፤
ዮሐንስ ዘኮንከ ምስለ መላእክት ዘውገ፤
ምሉዓ ወድግዱገ ዘሰላምከ ፈለገ፤
በውሣጤ ከርሥየ ኢይኩን ንቱገ፡፡ »
【የመኖርህን ነገር ያስረዳ ዘንድ ለተተወ ፤ ለልብስህ ከጫማህ ጋር ክብር ይገባል፤ ከመላእክት ጋር ወዳጅ የሆንክ ዮሐንስ ሆይ! ሞልቶ የተትረፈረፈ የፍቅር አንድነትህ ወንዝ በሆዴ ውስጥ የጎደለ አይሁን /ይሙላ/።】
ረ) የሊቃውንት ቅኔ ለጊዜው በዝክረ ሊቃውንት ከተዘገቡት ሁለቱን ልጠቁም
« ወልደ ነጐድጓድ ተሰደ እንዘ የኀድግ ሀገረ፤
እምኅበ አጥፍአ ሞተ ሰብእ ሦረ፤
ገራህቱ መቅበርት አምጣነ አብቈለት ሣዕረ»
«ዘማ መቅበርት ለወልደ ነጎድጓድ ትቤሎ፤
እመ ትጸልአኒ አንተ ዘያፈቅረኒ ሀሎ»
ሰ) ከውጭ የተገኙ ቀደምት ምንጮች
በውጭ ሀገራት ቀደምት ድርሳናትና ሊቃውንትም ዘንድ ቢሆን ከላይ ያነሳነውን ጭብጥ የሚደግፍ ታሪክ ተመዝግቦ ይገኛል።
https://www.stjohnaz.org/about-us/our-patron-saint/#:~:text=He%20bade%20them%20prepare%20for,disobedient%2C%20they%20fulfilled%20his%20bidding.
በሌላ ሥፍራ የተገኘው ደግሞ ይህን ይላል ቅዱስ ዮሐንስ የሚነጠቅበት ሠዓት እንደደረሰ ሲያውቅ በመስቀል ቅርጽ የተሰናዳ መቃብር እንዲያዘጋጁለት አርድእቱን አዟል እነርሱም በበዛ እንባ መምህራቸውን እየሳሙ ካለመታዘዝ እንዳይቆጠርባቸው ፊቱን በጨርቅ ሸፍነው ወደ መቃብሩ ሥፍራ አኑረውት ሄደዋል። ከደቀ መዛሙርቱ አንዱ ( ቅዱስ አብሮኮሮስ) ወደቦታው ተመልሶ ቢመጣ መቃብሩን ቢከፍተው ባዶ ሆኖ አግኝቶታል።
«He bade them prepare for him a cross-shaped grave, in which he lay, telling his disciples that they should cover him over with the soil. The disciples tearfully kissed their beloved teacher, but not wanting to be disobedient, they fulfilled his bidding. They covered the face of the saint with a cloth and filled in the grave. Learning of this, other disciples of Saint John came to the place of his burial.
#When_they_opened_the_grave, they found it empty.»
በአብሮኮሮስ ስለተሠጠው ምስክርነት (testimony of St. Prochorus) ደግሞ ተከታዩት አስረጂ በሊንኩ ታግዘው ቢያዩ የበከጠ ሐሳባችንን ያግዛል።
https://www.johnsanidopoulos.com/2009/09/repose-of-st-john-theologian-according.html?m=1
✧ ለማስማማት በሚነሳው የማስታረቂያ ሐሳብ
በኤፌሶን/ ቱርክ የመቃብሩ ሥፍራ ይህ ነው እየተባለ ዛሬም ለጎብኚዎች ይታያል።
ይሁንና ግን ☞ገራህቱ መቅበርት አምጣነ አብቈለት ሣዕረ ፣
☞ልብሱ ለዮሐንስ ወአሣእኑ ዘተኃድገ ለአብሮኮሮስ ከመ ያዑቅ ሕይወቱ ፣
☞ When they opened the grave, they found it empty ከሚሉቱ ሳይስማማ ሞቷል ለሚሉቱ ድጋፍ መስሎ ቀርቧል። በመላእክት ቢሎ በደቀመዛሙርቱ መቃብሩ መዘጋጀቱ እውነት ቢሆንም ሥጋው ከዚያ መታጣቱና የአብሮኮሮስ ምስክርነት ተሰውሯል ወደሚለው ያደርሰናል።
የስንክሳሩን አገላለጥ በሚመለከት ደግሞ ወደ ብሔረ ሕያዋን ተነጥቀዋል ብላ ቤ/ክርስቲያን የምትናገርላቸውን ቅዱሳንን ዐዕረፈ ብሎ ማስቀመጥ በአያሌው የተለመደ ነው። ዐረፈ የሚለው በአገባቡ ሞትን ብቻ አይገልጥም ከዚህ ዐለም ድካም መለየትን ካለንበት ዓለመ መሬት (ምድር) በሕይወት ወደ ብሔረ ብፁዓን አልያም ብሔረ ሕያዋን መሻገር ዕረፍት ተብሎ ይነገራል
የሌሎቹን አበው ወደብሔረ ሕያዋን መሔድ ዕረፍት ይለዋል
ለአብነት ግንቦት ፲፩ ስለ ቅዱስ ያሬድ ሲናገር «በዚህች ዕለት የሱራፌል አምሳያቸው ኢትዮጵያዊው ማሕሌታይ ያሬድ ዐረፈ» ይላል።
እንደመውጫ ቅዱስ ዳዊት “ሕያው ሆኖ የሚኖር፥ ሞትንስ የማያይ ማን ነው? ነፍሱንስ ከሲኦል እጅ የሚያድን ማን ነው?” ይላል【መዝ ፹፱ ፥፵፰ 】ከሰው ወገን ሕያው ሆኖ ለዘለዓለም ነዋሪ ሞትንም ሳያይ በምድር ላይ ቀሪ የሆነ ማንም የለም። የሐዋርያው ክብርና ቅድስናም ከመሞቱ አልያም ወደ ብሔረ ሕያዋን ከመነጠቁ ጋር በቀጥታ የሚያያዝበት ልኬት የለውም። ባለመሞቱ የሚከብርበት በመሞቱ የሚቀርበት መንገድ ስለሌለ ክርስቶስ አይሞትም አላለም እስክመጣ ቢኖር… አለ እንጂ።
ሰው ሕያዊት ነፍሱበ በሞት ከተለየችው እንደፈሰሰ ውኃ ነው
ፈሶ የታፈሰ ውኃ 【ማይ ዘገብኣ እምድኅረ ተክዕወ】
የቅዱሱ መጽሐፍ ብሂል እንዲህ ይላል "ዘእምከመ ተክዕወ ማይ ውስተ ምድር ኢይትገባእ" እኛም እንጂ ይህን ይዘን «የፈሰሰ ውኃ አይታፈስም» እንል የለ!?
【፪ኛ ሳሙ፲፬፥፲፬ 】
ዮሐንስ ግን ሞቶ ተቀበረ ሲሉት ተነስቶ የተነጠቀ ነውና የታፈሰ ውኃ ነውና "ማይ ዘገብኣ እምድኅረ ተክዕወ" አልነው።
ሞተ የተባለ በሰዎች ኅሊና የተቀበረውን ማንነታችን ወደልዕልናው በቸርነቱ ይንጠቅልን
ሎቱ ስብሐት ለዘበስብሐተ አቡሁ ይሴባሕ፤ ወሎቱ ቅድሳት
ለዘበቅድሳተ መንፈ ሱይትቄደስ 🙏
በቴዎድሮስ በለጠ ጥር ፬ ቀን ፳፻፲፮ ዓ.ም. ከደብረ ነጎድጓድ
https://m.facebook.com/story.php?story_fbid=pfbid0Gwrw5N6DhSGtkzJqWWYwogjSJc9eyKA8fzp21g7zPCexn89qRvApZNRbfypLLyTpl&id=100001155652281&mibextid=Nif5ozKo'proq ko'rsatish ...
Our Patron Saint - St. John the Evangelist Orthodox Church
The Holy, Glorious All-laudable Apostle and Evangelist, Virgin, and Beloved Friend of Christ, John the Theologian was the son of Zebedee and Salome, a daughter of St Joseph the Betrothed. He was called by our Lord Jesus Christ to be one of His Apostles at the same time as his elder brother James. This took place at Lake Gennesareth (i.e. the Sea of Galilee). Leaving behind their father, both brothers followed the Lord.The Apostle John was especially loved by the […]