የሱፊያ ጭፈራ በዑለማእ እይታ
~
1. ኢማሙ ማሊክ፡-
“እኛ ዘንድ ሱፊያ የሚባሉ ሰዎች አሉ። በብዛት ይበሉና ከዚያ ያንጎራጉራሉ። ከዚያም ተነስተው ይጨፍራሉ” ሲሏቸው
* “ህፃናት ናቸው?” ብለው ጠየቁ።
- “አይደሉም” አሏቸው።
* “እብዶች ናቸው?” ሲሉ
- “አይደሉም። ሸይኾች ናቸው” አሏቸው።
* “እኔ ከኢስላም ሰዎች ይህን የሚሰራ አንድም አልሰማሁም” አሉ። [ተርቲቡል መዳሪክ፡ 2/53]
2. አቡል ወፋእ ኢብኑ ዐቂል፡-
"በዜማና የመሳሪያ ድምፅ እየተከተለ የሚደንስና የሚጨፍር ባለ ፂም ማየት ምንኛ አስቀያሚ ነው? ባለ ሽበት ሲሆን ደግሞ የባሰ ነው! በተለይ ደግሞ በወጣቶችና በሴቶች ድምፅ ሲታጀብ። ከፊቱ ሞት፣ ጥያቄ፣ መቀስቀስና ሲራጥ ያለበት፣ ከዚያም ከሁለቱ አገሮች ወደ አንዱ የሚሆን ሰው እንደ እንስሳት ዝላይ ሊዘል፣ እንደ ሴቶች ማጨብጨብ ሊያጨበጭብ እንዴት ይዋጥለታል?" “ሱፊዮች ስራን ያበላሻሉ። የእምነት መሰረቶችን ያናጋሉ። ቦዘኔነትንና ዜማ ማዳመጥን ይወዳሉ።” [ተፍሲሩል ቁርጡቢይ፡ 10/263]
3. ኢብኑል ጀውዚይ፡-
የሱፊያ ክፍሎችን ተግባር አንስተው ባወገዙበት እንዲህ ብለዋል:– “በየምግቡ ላይ ይቀመጣሉ፡፡ ሲጠግቡ ጊዜ ይደንሳሉ፡፡ … ከመዐቶቻቸው ሁሉ የከፋው መዐት ግን ይህንን (ጭፈራ) መቃረቢያ (ዒባዳ) አድርገው መሞገታቸው ነው፡፡ ዳንስን ወደ ላቀው አላህ መቃረቢያ ነው ብሎ የሞገተ ሰው እንደሚከ -ፍ*ር በርግጥም የዑለማዎች ኢጅማዕ ተቋጥሯል፡፡” [ሶይዱል ኻጢር፡ 168]
4. ቁርጡቢይ፡-
“ሱፊዮች የፈጠሩትን (ዜማ) በተመለከተ በክልክልነቱ ላይ ውዝግብ ከማይነሳበት ነገሮች ነው። ነገር ግን ብዙ በመልካም የሚታሰቡ ሰዎችን ስሜት አሸንፏቸዋል። ብዙዎቹ ላይ የእ-ብ-ዶችና የህፃናት ስራዎች እስከሚታዩባቸውና በተጠና መልኩ እስከሚደንሱ ደርሰዋል። ከዚያም ከፊል ሰዎች መቃረቢያና መልካም ስራ እስከማድረግ ደረሱ።…” [ተፍሲሩል ቁርጡቢ፡ 14/54]
5. ሲዩጢይ፡-
"ከነዚህም (ከቢድዐዎች) ውስጥ የሆነው በመስጂድ ውስጥ የሚፈፀም ጭፈራ፣ ዘፈን፣ ድቤ መምታት፣ ማሲንቆና ሌሎችም የሙዚቃ መሳሪያዎች ናቸው፡፡ ይህንን ከመስጂድ ውስጥ የፈፀመ ሊባረርና ሊደበደብ የሚገባው ጠ -ማ -ማ ሙብ -ተ-ዲዕ ነው፡፡ ምክንያቱም አላህ እንዲላ፞ቅ ያዘዘውን ነገር እያቃለለ ነውና፡፡ … (ከመስጂድ ውስጥ) የዘፈነ ወይም የጨፈረ ቅጣት የሚገባው የሆነ ጠሞ አጥ -ማሚ ሙብ -ተ-ዲዕ ነው፡፡” [ሐቂቀቱ ሱና፞ ወልቢድዐ፡ 191]
በነገራችን ላይ ይሄ መስጂድ ውስጥ መጨፈር የመካ ሙሽሪkoች ተግባር ነው። አላህ እንዲህ ብሏል:-
﴿وما كان صلاتهم عند البيت إلا مكاء وتصدية فذوقوا العذاب بما كنتم تكفرون﴾
"በቤቱ ዘንድም (በካዕባ) ስግደታቸው ማፏጨትና ማጨብጨብ እንጂ ሌላ አልነበረም። ትክዱት በነበራችሁትም ነገር ቅጣትን ቅመሱ (ይባላሉ)።" [አንፋል፡ 35]
Ko'proq ko'rsatish ...