MAN U VS ARSENAL Analysis
በሁሉም ደጋፊዎች ዘንድ ያልተለመደውን አርሰናል አይተናል ፤ አብዛኛው የእግር ኳስ ደጋፊም ማን ዩናይትድ ነጥብ ይዞ መውጣት ነበረበት የሚለውን እይታ ይዟል ።
ግን በTactical እና በStatistical ዕይታ ስንመለከተው ግን አርሰናል እንደተወራው መጥፎ አልነበርም በFinal Third ላይም የተሻለ ከዩናይትድ የተሻለ መሆኑን አሳይቶናል ዩናይትድም ከተጠበቀው በላይ ሆኖ ተገኝቷል።
ለዚህም ነው በእግር ኳስ ተመልካቾች ዘንዳ ማን ዩናይትድ የተሻለ ሆኖ የታያቸው ፤ ዩናይትድ ሰሞኑን ከነበረበት የውጤት ቀውስ ፣ እና ደረጃቸው አንፃር ሊጉን ለመብላት ከሚታገል ቲም ጋር ተጫውቶ በመጠኑም አርሰናልን በመፈተን በደጋፊው አዕምሮ ላይ ሌላን ነገር ስለዋል ።
አርሰናል የዛሬውን ጨወታ በLow-Block በመጫወት (ወደኋላ መለስ ብለን) ከሌላ ጊዜ የተለየውን አርሰናል አይተናል በአብዛኛው የሊግ ጨዋታ አርሰናል የMid-Block የመከላከል ስራን ነበር ሚያሳየን
(መሀል አከባቢ ላይ Constant pressureን በመፍጠር ነበር ከተጋጣሚ ኳስ የምንቀማው) ለዚህም ነበር ዩናይትድ ከተለመደው ጊዜ በላይ ኳስ የያዙት እና የሞከሩት በዚህም ላይ የአርቴታ ታክቲክ ሰርቷል ያገኙትን ዕድሎች በራሳቸው ችግር እና በአርሰናል የመከላከል ብቃት ግብ ሳያስቆጥሩ ወተዋል ለዚህም ደግሞ ሳሊባ ትልቁን ሚና ተወቷል ፤ አርቴታም ይህንን ነበር ማረግ የፈለገው ከጨዋታው እንደተረዳነው ። ማን ዩናይትድም ጨዋታውን impact ማረግ የፈለጉት የነበረው በሁለቱ ክንፍ ተጫዋቾቻቸው ነበር ፤ በትንሹም ጨዋታው ላይ ተፅዕኖ ቢያሳዩም ሙሉ ከ60ኛው ደቂቃ በኋላ ተዳክመው ነበር ።
በአጠቃላይ XGውን ስንመለከት በጨዋታው ላይ አርሰናል ለግብ የበለጠ መቃረቡን እና ማን ዩናይትድም ዕድሎቹን እንዳበላሸ ያሳየናል ።
ጨዋታውም ብዙ የሚወራለት አልነበረም እንደተጠበቀውም አልሆነም ።
"SHARE"
@ETHIO_ARSENALShow more ...