Best analytics service

Add your telegram channel for

  • get advanced analytics
  • get more advertisers
  • find out the gender of subscriber
Channel location and language

audience statistics ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ አስተምህሮና ስርዓትን የጠበቁ ትምህርቶች፣ ስንክሳር፣ መዝሙራትን ከነዜማቸው ለማግኘት ቻናላችንን ይጎብኙ። ለማንኛውም አስተያየት  @Zimaredawitmessanger  ላይ ቢያስቀምጡልን ይደርሰናል። ስለሚሰጡን ገንቢ ሃሳብ እናመሰግናለን። YouTube Page -  https://bit.ly/2O1Z3d8  Facebook Page -  https://www.fb.com/l/6lp1kJRRR  
Show more
140 875+9
~19 498
~3
14.38%
Telegram general rating
Globally
7 650place
of 78 777
47place
of 396
In category
152place
of 2 333

Subscribers gender

Find out how many male and female subscibers you have on the channel.
?%
?%

Audience language

Find out the distribution of channel subscribers by language
Russian?%English?%Arabic?%
Subscribers count
ChartTable
D
W
M
Y
help

Data loading is in progress

User lifetime on the channel

Find out how long subscribers stay on the channel.
Up to a week?%Old Timers?%Up to a month?%
Subscribers gain
ChartTable
D
W
M
Y
help

Data loading is in progress

Since the beginning of the war, more than 2000 civilians have been killed by Russian missiles, according to official data. Help us protect Ukrainians from missiles - provide max military assisstance to Ukraine #Ukraine. #StandWithUkraine

[object Object]

[object Object]
[object Object]
[object Object]
[object Object]
[object Object]
0
Anonymous voting
5 098
20
ሰላም ውድ የዝማሬ ዳዊት ቤተሰቦች እንደምን ዋላችሁ? እግዚአብሔር ይመስገን። መንፈሳዊ የዜማ መስሪያ ወይም ስቱዲዮ ያላችሁ ወንድሞች በውስጥ በኩል መልዕክት ይላኩልን። የምታውቁም ካለችሁ ጠቁሙልን
5 185
3
ይላል አንደበቴ ይላል አንደበቴ እግዚአብሔር ቅዱስ ነው አይተወኝምና ወላጅ እንደሌለው ትናንት የጠበቀኝ የነገም ተስፋዬ ትልሃለች ነፍሴ ፍቅር ነህ ጌታዬ አዝ የትናንት ሕይወቴን ዞር ብዬ ሳየው ማምለጫ የሌለው አጥሩም እሾህ ነው ወደ እረፍቴ ወጣሁ ይድረስ ምስጋናዬ ደጆች ቢዘጉብኝ በር ሆኖኝ ጌታዬ (2) አዝ በጥልቁ በረሃ ምግብ መጠጥ ሆኖኝ መንገዴን አቀናው እጄን በአፌ አስጫነኝ በእሳትና ውሃ መካከል አልፌ ተመስገን እላለሁ ቅኔ ሞልቶት አፌ (2) አዝ የብቸኝነቴን ማዕበል ገስጿል ለእኔ ብርሃን ሆኖ ለከሳሽ ጨልሟል ቀስቱን እያጠፈ ታደገኝ ከስቃይ የጌታዬ ሃሳብ ፍቅር ነው በእኔ ላይ (2) አዝ ትናንት ዛሬ ነገ ዘላለም ጠባቂ የልቤን ፍላጎት ሳልነግረው አዋቂ በባሕርይው ቅዱስ የሌለው አምሳያ ስሙ ወደቤ ነው መልህቄን መጣያ ሊቀ መዘምራን ቴዎድሮስ ዮሴፍ 💚 💚 💛 💛 ❤️ ❤️
Show more ...

ይላል_አንደበቴ_Yilal_Andebete_ሊቀ_መዘምራን_ቴዎድሮስ_ዮሴፍ.m4a

9 036
129
መስከረም ፲፩ በዚህችም ቀን በእስክንድርያ አገር ትህትናን ገንዘብ ያደረገች ቅድስት ታዖድራ አረፈች። ቅድስት ታዖድራ እድሜዋ በደረሰ ግዜ ወላጆቿ ያመጡላትን ባል እሺ ብላ አገባች። በሥጋ ወደሙም ተወስነው ኖሩ። አንድ ቀን ግን ከቤተክርስቲያን ስትመለስ፤ በመልኳ ምክንያት ለኃጢአት ይፈልጋት የነበር አንድ ጎረምሳ ያዛት። በአቅምም አልቻለችውም፤ የሚፈልገውንም አድርጎ ከክብር አሳነሳት። ታላቅ ኀዘን አዘነች፤ መሪር የሆነ ልቅሶንም አለቀሰች። የወንዶችንም ልብስ ለብሳ ወንድ መስላ ስሟንም ቴዎድሮስ በማለት በወቅቱ የሴቶች ገዳም አልነበረምና የወንዶች ገዳም ገባች። የምንኩስና ልብስንም ለበሰች። ሰይጣን ግን ፈተናውን አጸናባት። በአንድ ወቅትም አንድ ወንድ ከአንዲት ብላቴና ጋር አመነዘረ፤ እርሷም ወንድ ልጅ ወለደች። ወላጆቿም ድንግልናሽን ያጠፋው ማነው ብለው ጠየቋት። ሰይጣንም በእርሷ አድሮ፤ በገዳም ውስጥ የሚኖር አባ ቴዎድሮስ የሚባል ነው አለች። ወላጆቿም የተወለደውን ልጅ ወስደው ለገዳሙ አበምኔት የአባ ቴዎድሮስ ልጅ ነው ብለው ሰጡት። አበምኔቱም ቅድስት ታዖድራን ልጁን አስይዘው ከገዳም አባረሯት። በበረሀም በብዙ ፈተና ሰባት አመት ኖረች። በኋላም ዳግመኛ ተቀብለው ወደ ገዳም አስገቧት። ጥቂት ቀንም ኖረች፤ መልካም ተጋድሎዋንም ፈጽማ በዚህች እለት አረፈች። በረከቷ ይደርብን! አሜን ወስብሐት ለእግዚአብሔር ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር 💚 💚 💛 💛 ❤️ ❤️
Show more ...
11 016
42
በብርሃን ፀዳል በብርሃን ፀዳል ተከባ እመቤቴ በደመና ዙፋን ተቀምጣ ከፊቴ የፅጌውን ዜማ ስንዘምር በደስታ በምስጋናሽ መጠጥ ሲሰማኝ እርካታ/2/ አዝ እንባዬ ሲቀዳ ናፍቆትሽ መስጦኝ ከደስታ በላይ አንቺን ስላየሁኝ ምኞቴ ተሳክቶ ፊትሽን አይቼው የሌሊቱ ሕልሜ የቀን ምኞቴ ነው/2/ አዝ እሩሩህ ነሽና ይህ ህልሜ ተሳክቶ አመስግኜሽ ድንግል ህሊናዬ እረክቶ ልጅሽ ልሁን ድንግል ከስርሽ አልጥፋ አንቺን በማመስገን ሕሊናዬ ይትጋ/2/ አዝ ልጅሽ ልሁን ድንግል ከስርሽ አልጥፋ አንቺን በማመስገን ህሊናዬ ይርካ የምስጋናሽ ብዕር ብራናሽ ልሁን ስምሽ ይጻፍብኝ በልዩ ሕብር/2/ ሊቀ መዘምራን ይልማ ኃይሉ 💚 💚 💛 💛 ❤️ ❤️

በብርሃን_ፀዳል_Be_Berhan_Tsedal_ሊቀ_መዘምራን_ይልማ_ኃይሉ.m4a

9 943
117
​​ንስሐ ንስሐ ማለት ሐዘን፣ፀፀት፣ ቁጭት፣ ቀኖና፣ የኃጢአት ካሣ ማለት ነው፡፡ ንስሐ አንድ ሰው በሠራው ጥፋት፣ ባደረገው ስህተት፣ በፈጸመው ኃጢአት ማዘኑና መፀፀቱን ዳግመኛም ያንን የመሰለ ኃጢአት ላለማድረግ የሚወስነው ውሳኔ ነው፡ ንስሐ የመንግሥተ ሰማያት መግቢያ በር ነው፡፡ በሌላ አገላለፅ ደግሞ ንስሐ ማለት  ወደ እግዚአብሔር መመለስ፣ ከእግዚአብሔር ጋር መታረቅ፣ ከኃጢአት መራቅ፣ ወደ መንፈሳዊ ሕይወት መመለስ ነው።   ንስሐ ለመግባት ስናሳብ ከታች የተዘረዘሩትን ሁኔታዎች ማሟላት አለብን፦ 1. በአጥቢያችን ከሚገኝ ቤ/ክ  ክህነት ያላቸው በአገልግሎት ላይ ያሉ መልካም መንፈሳዊ ምግባር ያለቸውን አባቶች የንስሐ አባት መያዝ፤ 2. የሰራነውን ኃጢአት ማመንእና በሰራነው ኃጢአት ከልብ አብዝተን መፀፀት፣ማዘንና ማልቀስ፤ 3. እግዚአብሔር ይቅር እንዲለን በፍጹም ትህትና ራስን በማዋረድ መጠየቅ፤ 4. ከእኛ ኃጢአት ይልቅ የእግዚአብሔር ቸርነትና ይቅር ባይነት እንደሚበልጥ እና ይቅር እንደሚለን ያለጥርጥር ፍጹም ማመን፤ 5. ወደ ንስሐ አባታችን ሄደን ንስሐ ለመግባት እና ቀኖናችንን ለመቀበል ማሰብ እና መወሰን፤ 6. ከልጅነት እስከ ዕውቀት የሰራናቸውን ኃጢአቶች ለማስታወስ መሞከር ከተቻለም ለማስታወስ ይረዳን ዘንድ በጽሑፍ መያዝ፤ 7. ዳግም ወደ ሰራነው ኃጢአት እንደማንመለስ ለራሳችን ቃል መግባትና መወሰን፣ኃጢአትን መጸየፍ፤ 8. ወደ ንስሐ አባታችን ሄደን የሰራነውን ኃጢአት ሳንደብቅ በግልፅ መናዘዝ። 9.የሚሰጠንን ቀኖና በትክክል መተግበር፤ 10. ዳግም ወደ ኃጢአት እንዳንመለስ ራሳችንን በቃለ እግዚአብሔር ማነጽ፤ 11. ዳግመኛ ለንስሐ መዘጋጀት። ንስሐ ከሚደገሙ ምስጢራት መካከል አንዱ ነው። ሰዎች እንደመሆናችን በተደጋጋሚ በኃጢአት እንወድቃለን ስለዚህ በተደጋጋሚ ንስሐ ልንገባ ይገባናል ማለት ነው። ኃጢአት ለንስሐ አባት መናዘዝ ለምን አስፈለገ? ራሱ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ያዘዘው ትዕዛዝ ስለሆነ ነው። ሄደህ ራስህን ለካህን አሳይ፡ ለእነርሱም ምስክር እንዲሆን ስለመንጻትህ ሙሴ እንዳዘዘ መሥዋዕት አቅርብ አለው። ሉቃ.፭፥፲፬ ንስሐ ከገባን ቀኖናችንን በስርዓቱ ከፈፀምን በኋላ ንስሐችንን ፍፁም የሚያደርገው ቅዱስ ሥጋውንና ክቡር ደሙን መቀበል ነው። ዮሐ 6፥33 ብዙዎቻችን መቁረብን እንደ ትርፍ ነገርና በዕድሜ የተገደበ ለአዛውንቶች ብቻ አድርገን ስለምንቆጥር ለመቀበል ዝግጁ አይደለንም። ነገር ግን ክርስቲያን የሆነ ሁሉ ቅዱስ ቁርባን የግድ ያስፈልገዋል። ቀኖና የተቀበልንበት በደላችን የሚሰረየው ሥጋውን ስንበላ፣ ደሙንም ስንጠጣ ነውና። ንስሐ ገብተን ቅዱስ ሥጋውን ክቡር ደሙን ለመቀበል ያብቃን። አሜን። ወስብሐት ለእግዚአብሔር 💚 💚 💛 💛 ❤️ ❤️
Show more ...
image
12 227
186

[object Object]

[object Object]
[object Object]
[object Object]
[object Object]
[object Object]
0
Anonymous voting
12 102
18
ሰባቱ መንጦላይት ሰባቱ መንጦላይት ወዴት ተጋረዱ ሰባቱ መብራቶች ወዴት ተሰናዱ ታናሽ ሙሽራ ነሽ የአሥራ አምስት ዓመት በአንቺ ላይ ሲፈጸም እንግዳ ሥርዓት አዝ አንዴ እየታጠቀ አንዴም እየፈታ ገብርኤል ሲያበስርሽ በፍጹም ሰላምታ ይኩነኒ ብለሽ ስትቀበይው መለኮት እንዴት ነው የተዋሐደው ይህን ባሰብኩ ቁጥር ልቤ ይመሰጣል ከዚህ በላይ ፍቅርስ እንዴት ይገለጣል    አዝ ሁሉን የሚወስን ባንቺ ተወሰነ ከሦስቱ አካል አንዱ ቃልም ሥጋ ሆነ ስፋት እና ጥበት ሰማይ እና ምድር ባንቺ ተገናኙ ገባሪና ግብር ይህን ባሰብኩ ቁጥር ልቤ ይመሰጣል ከዚህ በላይ ፍቅርስ እንዴት ይገለጣል አዝ እንዴት ቢመርጥሽ ነው እንዴት ቢያከብርሽ ትናንት እና ዛሬን ያገናኘብሽ ምልዐትና ወሰን ግዝፈትና ርቀት ባንቺ ተዋሐዱ ፈጣሪና ፍጥረት ይህን ባሰብኩ ቁጥር ልቤ ይመሰጣል ከዚህ በላይ ፍቅርስ እንዴት ይገለጣል      አዝ ምስጢር ሊመረምር ይወጣል ኀሊና ያልፋል ይሻገራል ከሰማይ ደመና ነገር ግን አይችልም ምንም ቢገሠግሥ ከመሰወሪያው ዘንድ ከልጅሽም ሊደርስ ስለዚህ አቅቶት ደክሞት ይመለሳል መልክዐ ውዳሴሽን በአድናቆት ያደርሳል ዘማሪ ቀሲስ ምንዳዬ ብርሃኑ 💚 💚 💛 💛 ❤️ ❤️
Show more ...

ሰባቱ_መንጦላይት_ዘማሪ_ቀሲስ_ምንዳዬ_ብርሃኑ.m4a

13 673
181
መስከረም ፲ በዚህች ዕለት ጼዴንያ በምትባል አገር ሥጋ የለበሰች ከምትመስል፤ ከሠሌዳዋም ቅባት የሚንጠፈጠፍባት የእመቤታችን የድንግል ማርያም ሥዕል ተዐምር ተገለጠ። ይህችን ሥዕል የሳላት ቅዱስ ሉቃስ ነው። ወደ ጸዴንያ እንዴት መጣች ቢሉ፤ አንዲት ማርታ የምትባል ሴት ነበረች በቤቷም እንግዳ ትቀበል ነበር። ድንግል ማርያምንም አብዝታ ትወዳት ነበር። በአንዲት ቀንም ስሙ ቴዎድሮስ የሚባል መነኩሴ በእንግድነት መጣ። በማግስቱ ስትሸኘው ወዴት ነህ ብላ ጠየቀችው። እርሱም ወደ ኢየሩሳሌም እንደሆነ ነገራት። እርሷም ሲመለስ የእመቤታችንን ሥዕል አምጣልኝ አለችው። ከዚህም በኋላ ከቦታው ደርሶ ሥዕሏን ሳይገዛ ተመለሰ፤ በመንገድም ሥዕሏን ለምን አልገዛህም? የሚል ድምጽ ሰምቶ ተመልሶ ገዛ። በጎዳናው እየተመለሰ ሳለም የሚያስፈሩ ወንበዴዎች፤ ኋላም አንበሳ ገጠመው፤ የያዛት ሥዕልም ቃል አውጥታ አዳነችው። አባ ቴዎድሮስም ይህን ድንቅ ተአምር ባየ ግዜ ሥዕሏን ወደ ሀገሩ ሊወስዳት ወደደ። በሌላ ከተማም አድርጎ ሊሄድ መርከብ ተሳፈረ። በመርከቧ ሳለም ታላቅ ነፋስ ተነስቶ አቅጣጫውን አስቀይሮ ወደ ጸዴንያ ወሰደው። ኋላም ቢመሽበት ማርታ ቤት ሄደ እራሱን ግን አልገለጠም። በማግስቱም ተሰውሮ ከከተማው ሊወጣ ቢሞክር መውጫው ጠፍቶት ሲዞር ውሎ ተመለሰ። እንዲህም እያለ ሶስት ቀን ሆነው። ማርታም ይህን ተመልክታ ምን እንደሆነ ጠየቀችው። እርሱም ሁሉንም ነገራት። በኋላም የመነኩሴውን እጅና እግር ስማ ሥዕሏን ተቀበለች። በታላቅ ክብርም አስቀመጠቻት። ያም መነኩሴ እስከሚሞትበት ቀን ድረስ የእመቤታችን ድንግል ማርያምን ሥዕል እያገለገለ ኖረ። የእመቤታችን በረከት ይደርብን! ወስብሐት ለእግዚአብሔር ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር 💚 💚 💛 💛 ❤️ ❤️
Show more ...
15 057
121
እግዚአብሔርን አመስግኑት እግዚአብሔርን አመስግኑት ሥራህ ግሩም ድንቅ ነው በሉት/2/ አዝ ሰማይን ያለምሰሶ ምድርንም ያለ መሠረት ያጸናው እርሱ ነው ሥራህ ድንቅ ነው በሉት አዝ የባሕርን ጥልቀት የመጠነ ዳርቻዋን የወሰነ እግዚአብሔርን አመስግኑት ሥራህ ግሩም ድንቅ ነው በሉት አዝ ማዕበል ነፋስ የሚገስጽ ፍጥረቱ ለስሙ የሚታዘዝ ትጉህ እረኛ ድካም የሌለበት እግዚአብሔርን ሥራህ ድንቅ ነው በሉት አዝ ንጹሀ ባሕርይ ነው ሁሉን የሚገዛ የነገስታት ንጉሥ አልፋና ኦሜጋ  ዘላለም እርሱ የማይለወጥ እግዚአብሔርን ሥራህ ድንቅ ነው በሉት አዝ  ጥበብን የሚገልጥ ጥበበኛ ፍርድን የሚያደርግ እውነተኛ ዳኛ  እንደ እርሱ ያለ ከቶ አይገኝም  እግዚአብሔር ግሩም ነው ዘለዓለም ዘማሪት ፀዳለ ጎበዜ 💚 💚 💛 💛 ❤️ ❤️
Show more ...

እግዚአብሔርን_አመስግኑት_ዘማሪት_ፀዳለ_ጎበዜ.m4a

13 454
142
ውድ የዝማሬ ዳዊት ቤተሰቦች እንደምን ዋላችሁ? እግዚአብሔር ይመስገን። ቪድዮ ኤዲት እና ግራፊክስ የተማራችሁ እና እንዲሁም ተሰጥኦ ያላችሁ ካላችሁ ወይም የምታውቁት ሰው ካለ በ ይላኩልን።
2 625
23

[object Object]

[object Object]
[object Object]
[object Object]
[object Object]
[object Object]
0
Anonymous voting
14 629
36
ምክንያት ስላለኝ ነው ምክንያት ስላለኝ ነው የምዘምርልሽ ምክንያት ስላለኝ ነው ቅኔ እምቀኝልሽ አሁንም ይብዛልኝ ፍቅርሽ/2/ ከዚህ በላይ እንዳመሰግንሽ አዝ አውቃለሁ ከደጅሽ ምን እንዳገኘሁኝ አስታውሰዋለሁ ሸክሜን እንደጣልኩኝ የለመንኩሽ ሁሉ መቼ ከንቱ ቀረ ሰይጣን ተመለሰ እያቀረቀረ ጠላት ቢከፋውም ለአንቺ በመቆሜ  አደገድጋለው ደግሜ ደግሜ/2/ አዝ ልቤ አርፏል በአንቺ በእናቴ አማላጄ እንቅፋት እሾሁ አይበቅልም በደጄ በሚጣፍጥ ዜማ በኤፍሬም ውዳሴ ሳሸበሽብልሽ ትረካለች ነፍሴ ጠላት ቢከፋውም ለአንቺ በመቆሜ  አደገድጋለው ደግሜ ደግሜ/2/ አዝ ውለታ ያለበት የማይከፈል ሲመሽም ሲነጋ ያመሰግናል ማርያም ማርያም ይላል ምድርና ሰማዩ በልጅሽ መከራ ሞቶለት ገዳዩ ጠላት ቢከፋውም ለአንቺ በመቆሜ አደገድጋለው ደግሜ ደግሜ/2/ ዘማሪት ምርትነሽ ጥላሁን 💚 💚 💛 💛 ❤️ ❤️
Show more ...

ምክንያት_ስላለኝ_ዘማሪት_ምርትነሽ_ጥላሁን_Official_Audio.m4a

15 624
193
መስከረም ፱ በዚህች ቀን መጺል በምትባል አገር ኤጲስ ቆጶስ የነበረ፤ ቅዱስ አባት አባ ቢሶራ በሰማዕትነት አረፈ። በወቅቱ ዲዮቅልጥያኖስ የተባለ ክፉ ሰው በንግስና ላይ የነበረበት ግዜ ነበር። በቤተ ክርስቲያን ታሪክ ከሰይጣን ቀጥሎ እንደዚህ የከፋ ስም የለም። የዓለም ክርስቲያኖችን የጨፈጨፈ ሰው ነው። መከራውም እየገፋ ሲመጣ ቅዱሱ በመፍራት ፈንታ የሰማዕትነት ፍቅር አደረበት። በክርስቶስ ስም ደሙን ያፈስ ዘንድ ወደደ። ሕዝቡንም ሰብስቦ አቆማቸው፤ ሊጠብቁት የሚገባውን ለጽድቅ የሚያበቃቸውን ትዕዛዝ ሁሉ አዘዛቸው። ከዚህም በኋላ ለሰማዕትነት እንደተዘጋጀ ነገራቸው። ይህንንም በሰሙ ግዜ ሁሉም አለቀሱ። የሙት ልጆች እንሆን ዘንድ ለምን ትተወናለህ፤ እንድትሄድ አንለቅህም አሉት ሊይዙትም ቃጡ። ቅዱሱም ሰላምታ ሰጥቷቸው ከእነርሱ ዘንድ ወጥቶ ተጓዘ። አንዳንድ አባቶችም አብረን እንሞታለን ብለው አብረውት ሄዱ። በኋላም መኰንኑ ጽኑ የሆነ መከራ አደረሰባቸው ፤አባቶች ግን በታላቅ ትዕግስት ጸኑ። ከዚህም በኋላ ራሶቻቸውንም በሰይፍ ይቆርጧቸው ዘንድ  አዘዘ። በዚህች ዕለትም የሕይወት አክሊልን በመንግስተ ሰማያት ተቀበሉ። በረከታቸው ይደርብን ወስብሐት ለእግዚአብሔር ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር 💚 💚 💛 💛 ❤️ ❤️
Show more ...
16 193
43
በበጎ ፍቃዱ በበጎ ፍቃዱ ሁሉ በእርሱ ሆነ (2) ነገር ሁሉ በርሱ ተከናወነ   (2) አዝ ሰማይና ምድር ግብሩን ተናገሩ ፈጥሯቸዋልና እንዲገለጥ ክብሩ በፈጠረው ፍጥረት የሚታወቅ እሱ እግዚአብሔር ይመስገን ስሙን አወድሱ አዝ አልሆነም ያለእርሱ ፍፁም አንዳች ነገር ብንመረምረው በሰማይ በምድር ፍቃዱ ነውና መልካምና በጎ ሰርቶ አሳይቶናል ሁሉን ውብ አድርጎ አዝ ክረምትና በጋ ሌሊትና ቀን ሁሉን አሳይቶ ጌታ አስተማረን ያደረገው ሁሉ እንከን የሌለው ለዚህ ቅዱስ አምላክ ምሳሌም የለው አዝ ያዘነውን ያውቃል ደስም ያለውን ሁሉ በእርሱ ፍቃድ ስለ ሚከወን ችግርና ደስታም ለበጎ ነውና ይህን ያስተማረን ይድረሰው ምሥጋና ዘማሪ ቀሲስ አሸናፊ ገ/ማርያም 💚 💚 💛 💛 ❤️ ❤️

በበጎ_ፍቃዱ_ሁሉ_በርሱ_ሆነ_ዘመን_የማይሽረው_ዝማሬ_ቀሲስ_ዘማሪ_አሸናፊ_zemari_Ashenaf.m4a

14 591
109
ስግደት ስግደት ማለት መዋረድ፣ ማጎንበስ፣ መንበርከክ፣ በግንባር መውደቅ፣ ግንባርን ምድርን አስንክቶ መሬት ስሞ መመለስ ማለት ነው። ስግደት ለምን ይጠቅማል? ስግደት ከአምላካችን ፀጋ እና በረከትን እንድናገኝ እንዲሁም ክፉ መንፈስ ከእኛ እንዲርቅ ይረዳል። በቤተ ክርስቲያን ሁለት አይነት ስግደቶች አሉ፦እነሱም ፩.የአምልኮ (የባህሪይ) ስግደት ይህ ለአምላካችን ለእግዚአብሔር ብቻ አንተ አምላኬ ነህ በማለት የምንሠግደው ስግደት ነው። ማቴ 4፥10 ፪.የአክብሮት (ጸጋ) ስግደት6 ለመላእክት ለቅዱሳን ለፃድቃን ለሰማዕታት የሚሰገድ ስግደት ነው። በፀሎት ጊዜ በተለይም ስግደትን የሚያነሳ አንቀፅ ሲገኝ ህሊና ተሰብስቦ የአንክሮ፣ የተደሞ፣ የትህትና ስግደት ይሰገዳል። ስግደት በቤተክርስቲያን እንዲሰገድ መጽሐፍ ቅዱስ ያዝዛል። ቤተክርስቲያን በሌለበት ቦታ ደግሞ በስተምስራቅ አቅጣጫ እንሰግዳለን። ስርዓተ ቤተክርስቲያን በወር ውስጥ አምስት ቀናት ስግደት እንዳይሰገዱባቸው ያዛል፦ 1. የበዓለ ወልድ እለት (በየወሩ በ29) እና በጌታችን አበይት በአላት 2. የእመቤታችን ወርሃዊ መታስቢያ (በየወሩ በ21) እና በእመቤታችን በዓላት   3. የሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል መታሰቢያ (በየወሩ በ12) 4. ቀዳሚት ሰንበት (ቅዳሜ) 5. ሰንበተ ክርስቲያን (እሁድ) እና በዓለ ሀምሳ። በእነዚህ ቀናት የማይሰገድበት ምክንያት 📌 ዕለተ ቅዳሜ ጌታችን ፍጥረታትን ሁሉ ፈጥሮ ከስራው ያረፈበት ቀን ስለሆነ። 📌 ዕለተ እሁድ ጌታ ከሙታን መካከል ተለይቶ የተነሳበት ቀን ስለሆነ። 📌 በ12 በዓለ ቅዱስ ሚካኤል ራዕ᎐፲፪ኀ ሰይጣን የወደቀበት ቀን ስለሆነ። 📌 በ21 በዓለ ማርያም የነፍሳችን ዕረፍት ነጻ የወጣንባት ስለሆነ። 📌 በ29 በዓለ እግዚአብሔር የነጻነት ቀን ጌታ የተወለደበት ቀን ስለሆነ። የአምልኮት ስግደት ሦስት ደረጃዎች አሉት እነርሱም;- ፩᎐ ሰው አድርገህ ከመሬት ፈጥረኸኛልና ስንል ወደ ምድር ጉልበትና ግንባራችንን እናስነካለን። ፪᎐ በኃጢአት ወድቄ በንስሐ እነሳለሁ ስንል ከሰገድንበት ብድግ እንላለን። ፫᎐ ብሞት በትንሣኤ እነሳለሁ ስንል ከሰገድንበት ቦታ በሁለት እግሮቻችን እንቆማለን። ወስብሐት ለእግዚአብሔር 💚 💚 💛 💛 ❤️ ❤️
Show more ...
image
16 462
235

[object Object]

[object Object]
[object Object]
[object Object]
[object Object]
[object Object]
[object Object]
[object Object]
419
Anonymous voting
15 772
61
ቸሪቱ አማላጅቱ ሆይ ቸሪቱ አማላጅቱ ሆይ እናቱ ነሽና ለአዶናይ በሥላሴ ፊት ስልጣን ያለሽ የባህሪያችን መመኪያ ነሽ (2) አዝ ተጥሎ አዝኖ የኖረው በልጅሽ ነው ቀናቀና ያለው ንጉሱን ስትወልጂ በበረት ተፈታ አዳም ከእስራት ዘጸውዓ ስምኪ ወዘገብረ ተስካርኪ ብሎ ቃልኪዳን ሰጠሽ ፍጥረትን እንዲምርብሽ አዝ ከሚያስብ ከማይዘነጋ ፍጥረቱን ከሚያረጋጋ ስላለሽ በእግዚአብሔር ቀኝ ለኃጥአን ድንግል ለምኝ ዘጸውዓ ስምኪ ወዘገብረ ተስካርኪ ብሎ ቃልኪዳን ሰጠሽ ፍጥረትን እንዲምርብሽ አዝ ከሰማይ ሰማያት ወርዶ መለኮት ሥጋን ተዋህዶ አየነው በጠባብ ደረት ወሰንሽው በአጭር ቁመት ዘጸውዓ ስምኪ ወዘገብረ ተስካርኪ ብሎ ቃልኪዳን ሰጠሽ ፍጥረትን እንዲምርብሽ አዝ ሰነድ ነሽ መታረቂያችን ከተማም መማፀኛችን በሰማይ በምድርም ያሉ ለክብርሽ ቅኔ ይቀኛሉ ዘጸውዓ ስምኪ ወዘገብረ ተስካርኪ ብሎ ቃልኪዳን ሰጠሽ ፍጥረትን እንዲምርብሽ ዘማሪ ገ/ዮሐንስ ገ/ማርያም 💚 💚 💛 💛 ❤️ ❤️
Show more ...

ቸሪቱ_አማላጅቱ_ዘማሪ_ገብረዮሐንስ_ገብረፃድቅ_ቤተ_ቅኔ_Beta_Qene.m4a

16 899
168
ኦ እንዳንተ ያለ ወዳጅ ኦ እንዳንተ ያለ ወዳጅ አላገኘሁም እኔ ኦ ውለታህን ሳስበው በእንባ ይመላል አይኔ/2/ አዝ ከእናቴም ልጆች በላይ አንተ ውድ ነህ ለኔ ወዳጅ እና ዘመዴ ጌታ የክፉ ቀኔ ምን አለኝ እና ልስጥህ የሚነገር የሚወራ እኔስ ተሸንፌያለሁ በእንባ ስምህን ልጥራ አዝ ተሰድጄ ብወጣ ወተሃል ከኔ ጋራ ትናንትናን አለፍኩት ጠላቴን እያራራ ደግሞ የነገውን ቀን አንተ ታውቃለህ ጌታ ወጥመዴን ስበር እና አፌን ሙላው በእልልታ አዝ በእስረኞች መሃል ሆኜ ሰንሰለት ለብሻለሁ አለም እውነት የላትም ፍትህ ካንተ እሻለሁ መቼ ታጽናናኛለህ ወዳጅ እና ዘመዴ አውጣኝ አውጣኝ ለሚልህ አንተ አታጣም ዘዴ አዝ መመላለስ አይደክምህ እኔን ማስታመም አንተ ደክመህ አልፈህልኛል እጆቼን አበርትተህ ሁሌ በሬ ላይ ቆመህ ደጃፌን የምትመታ ግባ የክብር ንጉስ ብያለሁ ማራናታ ብያለሁ ማራናታ/4/ ዘማሪት ምርትነሽ ጥላሁን 💚 💚 💛 💛 ❤️ ❤️
Show more ...

ቸሪቱ_አማላጅቱ_ዘማሪ_ገብረዮሐንስ_ገብረፃድቅ_ቤተ_ቅኔ_Beta_Qene.m4a

1
0
መስከረም ፰ በዚህች ቀን ደግሞ የእግዚአብሔር ሰው የሆነ፤ ቅን፤ የዋህ፤ ጻድቅ፤ የነቢያት አለቃ የቅዱስ ሙሴ ዕረፍቱ ነው። ከኮከብም ኮከብ እንደሚበልጥ ከነቢያት ሁሉ ደግሞ ቅዱስ ሙሴ ይበልጣል። የቅዱስ ሙሴ አባት እንበረም እናቱ ደግሞ ዮካብድ ይባላሉ። ቅዱስ ሙሴ በተወለደ ወቅትም የእስራኤል ወንድ ልጆች ይገደሉ ነበር። ወላጆቹም እርሱን ለማሸሽ ሲሉ ገና በ3ወሩ በግብጽ /ዓባይ/ ወንዝ ውስጥ ጣሉት። የፈርዖን ልጅም ከወንዝ ላይ ባገኘችው ግዜ ለእርሷ ልጅ ይሆናት ዘንድ ወስዳ በመልካም አስተዳደግ አሳደገችው። ስሙንም ሙሴ ያለችው እርሷ ናት፤ ትርጉሙም ከውሃ የተገኘ ማለት ነው። ወላጆቹ ግን በተወለደ ወቅት ፊቱ ያበራ ነበርና ምልክአም ብለው ስም አውጥተውለት ነበር። እናቱ ዮካብድም በሞግዚትነት ገብታ ልጇን ማንም ሳያውቅ አሳድጋዋለች። በቅዱስ መጽሐፍ እንደምናነበው ቅዱስ ሙሴ ኮልታፋ ነው፤ ይህም ገና በ5 አመቱ ፈርኦንን በጥፊ በመምታቱ እሳት አበሉት በዚህም ኮልታፋ ሆኖ ቀርቷል። 40 አመት በሞላው ግዜም አንድ የግብጽ ሰው አንዱን ዕብራዊ ሲያጠቃው ተመልክቶ ለዕብራዊው ተበቅሎ ግብጻዊውን ገደለው ከዚያም ወደ ምድያም ሸሽቷል። ቅዱስ ሙሴ በእግዚአብሔር ትዕዛዝ ግብጻውያን ላይ ዘጠኝ መቅሰፍት በአስረኛውም ሞተ በኩር መታ። እሥራኤልንም ነጻ አወጣ። መልካም ተጋድሎንም ፈጽሞ በዚህች ዕለት ዐረፈ። በረከቱ ይደርብን! አሜን ወስብሐት ለእግዚአብሔር ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር 💚 💚 💛 💛 ❤️ ❤️
Show more ...
17 812
81
ኦ እንዳንተ ያለ ወዳጅ ኦ እንዳንተ ያለ ወዳጅ አላገኘሁም እኔ ኦ ውለታህን ሳስበው በእንባ ይመላል አይኔ/2/ አዝ ከእናቴም ልጆች በላይ አንተ ውድ ነህ ለኔ ወዳጅ እና ዘመዴ ጌታ የክፉ ቀኔ ምን አለኝ እና ልስጥህ የሚነገር የሚወራ እኔስ ተሸንፌያለሁ በእንባ ስምህን ልጥራ አዝ ተሰድጄ ብወጣ ወተሃል ከኔ ጋራ ትናንትናን አለፍኩት ጠላቴን እያራራ ደግሞ የነገውን ቀን አንተ ታውቃለህ ጌታ ወጥመዴን ስበር እና አፌን ሙላው በእልልታ አዝ በእስረኞች መሃል ሆኜ ሰንሰለት ለብሻለሁ አለም እውነት የላትም ፍትህ ካንተ እሻለሁ መቼ ታጽናናኛለህ ወዳጅ እና ዘመዴ አውጣኝ አውጣኝ ለሚልህ አንተ አታጣም ዘዴ አዝ መመላለስ አይደክምህ እኔን ማስታመም አንተ ደክመህ አልፈህልኛል እጆቼን አበርትተህ ሁሌ በሬ ላይ ቆመህ ደጃፌን የምትመታ ግባ የክብር ንጉስ ብያለሁ ማራናታ ብያለሁ ማራናታ/4/ ዘማሪት ምርትነሽ ጥላሁን 💚 💚 💛 💛 ❤️ ❤️
Show more ...

ኦ_እንዳንተ_ያለ_ወዳጅ_ዘማሪት_ምርትነሽ_ጥላሁን_Official_Audio1.m4a

16 512
183

[object Object]

[object Object]
[object Object]
[object Object]
[object Object]
0
Anonymous voting
17 914
65
ድንቅ አድርጎልኛል ድንቅ አድርጎልኛል የሠራዊት ጌታ 2 አልረሳኝም አምላክ አነሳኝ ከትቢያ 2 አዝ ድንቅ አድርጎልኛል በደሌን ሳይቆጥር ድንቅ አድርጎልኛል ወደቤቱ ጠራኝ ድንቅ አድርጎልኛል እረክሼ ሳለሁ ድንቅ አድርጎልኛል ልጄ ሆይ ና አለኝ ድንቅ አድርጎልኛል በዳግም ምጻቱ ድንቅ አድርጎልኛል መንግስቱን ሊያወርሰኝ አዝ ድንቅ አድርጎልኛል ከአንበሳ መንጋጋ ድንቅ አድርጎልኛል ከጉድጓድ አወጣኝ ድንቅ አድርጎልኛል በጠላቶቼ ፊት ድንቅ አድርጎልኛል ግርማ ሞገስ ሰጠኝ ድንቅ አድርጎልኛል ምን እመልሳለሁ ድንቅ አድርጎልኛል እንዲህ ለወደደኝ አዝ ድንቅ አድርጎልኛል ጠላቶቼ ሁሉ ድንቅ አድርጎልኛል ሲጓደዱብኝ ድንቅ አድርጎልኛል ማን ይደርስለታል ድንቅ አድርጎልኛል እያሉ ሲሉኝ ድንቅ አድርጎልኛል ፈጥነህ ደረስክልኝ ድንቅ አድርጎልኛል ከሞት አዳንከኝ ዘማሪ ቀሲስ ምንዳዬ ብርሃኑ 💚 💚 💛 💛 ❤️ ❤️
Show more ...

ዘማሪ_ቀሲስ_ምንዳዬ_ብርሃኑ_Mendaye_Birhanu_ድንቅ_አድርጎልኛል_Denk_Adrgolgna.m4a

19 125
368
መስከረም ፯ በዚህች ቀን የመጥምቁ ዮሐንስ እናት፤ የከበረች ኤልሳቤጥ አረፈች። ቅድስት ኤልሳቤጥ እድሜዋ በደረሰ ግዜ ካህን ለሆነው ለቅዱስ ዘካርያስ አጋቧት። ነገር ግን እስከ እርጅና ዘመናቸው ልጅ መውለድ አልቻሉም ነበር። የኤልሳቤጥ እድሜ 90 የዘካርያስም 100 ደርሶ ነበር። እግዚአብሔርም ትዕግስታቸውን እና ጽድቃቸውን ተመልክቶ በመልዐኩ ገብርኤል አብሳሪነት ታላቅ የሆነ ነቢይን ሰጣቸው። የኤልሳቤጥ የስድስት ወር ጽንስም የድንግል ማርያምን ድምጽ በሰማ ግዜ በደስታ ዘሏል። ቅዱስ ዮሐንስም 2 ዓመት ከ6 ወር በሞላው ግዜም ንጉስ ሔሮድስ የተወለደውን ንጉስ /ኢየሱስ ክርስቶስን/ ለማጥፋት ተነሳ። አይሁዶችም ለንጉስ ሔሮድስ ሲጸነስ የአባቱን አንደበት የዘጋ ሲወለድ ደግሞ የከፈተ ዮሐንስ የሚባል አለና እርሱን ግደል አሉት። ቅድስት ኤልሳቤጥም ቅዱስ ዮሐንስን ይዛው ሸሸች። አባቱ ካህኑ ዘካርያስን ግን በቤተመቅደስ ውስጥ ገደሉት። ቅድስት ኤልሳቤጥም ዮሐንስን እያሳደገች በገዳመ ዚፋታ ለ3 ዓመታት ቆየች። ቅዱስ ዮሐንስም 5 ዓመት በሞላው ግዜ በዚህች ዕለት ቅድስት ኤልሳቤጥ በዚያው በበርሃ አረፈች። በረከቷ ይደርብን ወስብሐት ለእግዚአብሔር 💚 💚 💛 💛 ❤️ ❤️
Show more ...
20 607
75
የሥላሴን መንበር የሥላሴን መንበር ቅዱሳን ከበውት ኪሩቤል በደመና ዙፋኑን ይዘውት ድንግልን ከመሃል ሚካኤልን ከፊት አእላፍ መላዕክት ሲሰግዱ በፍራት እዩት ተመልከቱት የሰማዩን ድምቀት እዩት ተመልከቱት የሰማዩን አባት አዝ የሥላሴን መንበር ቅዱሳን ከበውት እያሸበሸቡ የሰማይ መላዕክት ካህናተ ሰማይ ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ ሲሉ ይህን ልዩ ተ0ምር ሊያዩ የታደሉ በጽድቅ ስራቸው በምድር ይታያሉ/ 2/ አዝ የቅዱሳን ህብረት የቅዱሳን ሀገር ሲያወድስ ይኖራል የሥላሴን ክብር ጽድቅና ርህራሄ የተሞላ ሰማይ እግዚአብሔር ያድለን በትንሳኤ እንድናይ/2/ አዝ የሥላሴን መንበር ቅዱሳን ከበውት እያሸበሸቡ በሰማይ መላዕክት ካህናተ ሰማይ ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ ሲሉ ይህን ልዩ ተዐምር ሊያዩ የታደሉ በጽድቅ ስራቸው በምድር ይታያሉ/ 2/ ሊቀ መዘምራን ይልማ ሀይሉ 💚 💚 💛 💛 ❤️ ❤️
Show more ...

የስላሴን_መንበር_ቅዱሳን_ከበውት_ሊቀ_መዘምራን_ይልማ_ሀይሉ.m4a

18 137
189

[object Object]

[object Object]
[object Object]
[object Object]
[object Object]
[object Object]
[object Object]
0
Anonymous voting
18 909
52
​​ አሥራት ሰው እግዚአብሔር ከሰጠው ላይ አሥራትን ካልከፈለ እግዚአብሔር አምላክ ሰርቃችሁኛል ይላል። አሥራት የሚለው ቃል ዐሠረ (ዓሥር) አደረገ ከሚለው የግዕዝ ግሥ የተገኘ ሲሆን ፍቺውም ከአሥር (10) አንድ ማለት ሲሆን ይህንንም ለእግዚአብሔር መስጠት ማለት ነው።አሥራት ሰው ጥሮ ግሮ ሠርቶ ከሚያገኘው ከላቡ ገቢ ለእግዚአብሔር ከአሥር አንድ እጁን ወይንም ከመቶ አሥር ክፍሉን ለእግዚአብሔር መሥጠት ማለት ነው። አሥራት በሕገ ልቦናና በሕገ ኦሪትም ይሠጥ ነበረ።ለምሳሌ በሕገ ልቦና አብርሃም አባታችን ለካሕኑ ለመልከጼዲቅ አሥራትን እንደከፈለ በቅዱስ መጽሐፍ  ተገልጧል። አብርሃምም ከሁሉ አሥራት ሠጠው።ዘፍ ፲፬÷፳ አባታችን ያዕቆብም ቤቴል ብሎ በሰየማት በሎዛ ምድር እግዚአብሔር ቢገለጥለት በሥፍራው የእግዚአብሔር ቤት እንደሚታነጽና እርሱም አሥራት እንደሚያደርግ ቃልኪዳን አደረገ። ከሰጠኸኝም ሁሉ ለአንተ ከአሥር እጅ አንዱን እሰጥሃለሁ። ዘፍ፳፰÷፳፪ እግዚአብሔር አምላካችን ሙሴን በሲና ተራራ ካዘዘው ትእዛዝ አንዱ አሥራትን ስለመክፈል ነው።ይሕም በዘሌ ፳፯÷፴፡፴፫ ተጽፎ ያለው ነው።ስለዚህ አሥራትን ማውጣት የአምላክን ሕግ መጠበቅና መፈጸም ነው። ሰው እግዚአብሔር ከሰጠው ላይ አሥራትን ካልከፈለ እግዚአብሔር አምላክ ሰርቃችሁኛል ይላል። ሰው እግዚአብሔርን ይሰርቃልን? እናንተ ግን እኔን ሰርቃችኋል። እናንተም። የሰረቅንህ በምንድር ነው? ብላችኋል። በአሥራትና በበኵራት ነው። ትን ሚል 3:8 አሥራት የሚከፈለው ለካሕናት መገልገያ በአጠቃላይ ለእግዚአብሔር መንግስት ማስፋፊያ ነው። ካሕናት ሙሉ በሙሉ ጊዜያቸውን ሁሉ አምላካቸውን እንዲያገለግሉ ሕዝቡንም እንዲጠብቁ ነው። አሥራትን በዘመነ ወንጌልም በዘመነ ክርስትናም እንደሚፈጸም ክብር ይግባውና ጌታችን እንዲህ ብሎ አዟል። የቄሣርን ለቄሣር የእግዚአብሔርን ለእግዚአብሔር ስጡ የማቴ ፳፪÷፳፩ እግዚአብሔር አምላክ ዘጠኙን ሊባርክልን አንዷን ብቻ ለኔ ሥጡኝ ሲለን ገንዘብ አምላኪዎች እንዳንሆን ከእርሱም ይልቅ ገንዘብን እንዳንወድ ወይም ለእርሱ ያለንን ፍቅር ያይበት ዘንድ ስለሚፈልግ  አሥራትን በኩራትን ምፅዋትንና ለጋስነትን አስተማረን አንድም ቸር ለጋስ መሆን እርሱን መምሰል ነውና። ስለዚህ እኛም ይህን በመረዳት ከምናገኛት ገቢያችን ላይ አነሰም በዛም ሳንል አስራታችንን በስርአቱና በጊዜው እናውጣ። ወስብሐት ለእግዚአብሔር!!! ምንጭ:- መጽሐፈ አሚን ወሥርዓት 💚 💚 💛 💛 ❤️ ❤️
Show more ...
image
17 868
112
መስከረም ፮ በዚህች ዕለት ታላቅ ነቢይ የአሞጽ ልጅ ኢሳይያስ አረፈ። ታላቁ ነቢይ ኢሳይያስ ከተናገራቸው ትንቢቶችም አንዱ በትንቢተ ኢሳይያስ 7፥14 "ድንግል ትጸንሳለች ወንድ ልጅም ትወልዳለች" የሚል ነበር ።በወቅቱ የነበሩ አንዳንድ ክፉ ሰዎች ግን ለንጉስ ሕዝቅያስ "ይህ ትንቢት ላንተ ነው ድንግል የተባለችዋ ኢየሩሳሌም ስትሆን ወንድ ልጅ የተባለው ደግሞ አንተ ነህ" አሉት። ንጉሱም ይህን ሰምቶ አልገሰጻቸውምና። እግዚአብሔርም በንጉሱ ተቆጥቶ ኢሳይያስን ላከው። እንዲህም አለው ትሞታለህ እንጂ አትተርፍምና ቤትህን ሥራ። መጽ ነገ ካልዕ 20:1 ይህ እንደሆነ ንጉሱ በጽኑ ታመመ ደከመ። ንጉሡም በልቡ ተጸጽቶ ጌታ ሆይ ይቅር በለኝ ሲል ተማጸነ። እግዚአብሔርም ንስሐውን እንደተቀበለው እና በዘመኑም ላይ 15 ዓመታትን እንደጨመረለት ነቢዩ ነገረው። በኋላ ዘመንም ንጉስ ምናሴ ጣዖትን ያመልክ ነበር። ነቢዩም በአደባባይ ገሰጸው። ምናሴም በዚህ ተበሳጭቶ ነቢዩ ኢሳያስን በዚህች ዕለት በእንጨት መጋዝ ለሁለት አሰነጠቀው። ቅዱሱም ተጋድሎውን ፈጸመ። በረከቱ ይደርብን ወስብሐት ለእግዚአብሔር ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር 💚 💚 💛 💛 ❤️ ❤️
Show more ...
1
0
የተወደደ ቀን የተወደደ ቀን የተወደደ ዓመት ወደ አባቴ መቅደስ የተመለስኩበት አንባር ቀለበትን የተሸለምኩበት የተወደደ ዓመት አዝ አምሽቶ የመጣ አይገባም አትበሉ(2) አባክኖ የመጣ አይገባም አትበሉ(2) ፍቅር ስለሆነ እግዚአብሔር ለሁሉ(2) ልጅ ቤቱን ይወርሳል እንደተስፋ ቃሉ(2) አዝ ከናዝሬት መልካም ሰው አይወጣም እያሉ(2) ፊልጶስ ናትናኤል ይነጋገራሉ(2) አድርጎታልና ውሀውን ወይን(2) ዛሬም ለውጦኛል ወስዶታል ልቤን(2) አዝ እኔ ነኝ አላማው እኔ ነኝ ሀሳቡ(2) አባቴ ደግ ነው የሚራራ ልቡ(2) ዘጠና ዘጠኙ ታምነውት እያለ(2) አንዱን ይፈልጋል ወዴት ነህ እያለ(2) አዝ ሁሉን አይቻለሁ ሁሉን መርምሬአለሁ(2) አለም ካንተ ሌላ እንደሌለ አውቃለሁ(2) እንደማይለወጥ አባትነትህ ወዳጅነትህ ጠፍቼ ስመጣ አየሁት ልጅህ(2) ዘማሪ ቀሲስ አሸናፊ ገ/ማርያም 💚 💚 💛 💛 ❤️ ❤️
Show more ...

የተወደደ_ቀን_ቀሲስ_አሸናፊ_ቁ_7_Yetewedede_ken_Kesis_Ashenafi_7_ethiop.m4a

17 062
203
እንደ ዝማሬ ዳዊት ገጽ ከሁለት አመት በፊት በቅዱስ ጊዮርጊስ ስዕል እና ቢራ ዙሪያ ትልቅ የሆነ የሚድያ ንቅናቄ ቢያደርግም ግቡን ሳይመታ ቀርቶ ነበር። አሁንም የተጀመረው የግዜ ጩኸት ብቻ ሆኖ እንዳይቀር ነገሩን ከኛ በዘለለ ከላይ ባሉ አባቶቻችን ትልቅ ትኩረት ሊሰጠው ይገባል። በሕግ ዕውቀት ያላችሁ የተዋህዶ ልጆችም ቤተ ክርስቲያናችሁ ትፈልጋቹሀለች። የኛን ክብር ማስጠበቅ እምንችለው እኛው ነን። እንደ ማሳሰብያ ማስተላለፍ የምንፈልገው መልዕክት ግን በተለያዩ ሶሺያል ሚድያ ይህን ድርጊት በመቃወም የተለያየ ቪድዮ በምትሰሩ ግዜ የቅዱስ ጊዮርጊስን ስዕለ አድኅኖ ክብር በማያወርድ እና ኦርቶዶክሳዊ ሥነምግባርን በተላበሰ መልኩ ሊሆን ይገባል። በአንዳንድ ቦታ ያልተገባ ድርጊት ስላስተዋልን ነው።
ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit
ቅዱስ ጊዮርጊስ - ቢራ ወይስ ሰማዕት? የቅዱሳን ስዕል አድህኖ በክብር መቀመጥ ሲገባው የቅዱስ ገዮርጊስ ስዕል ግን 1/ በየጠርሙሱ ተለጥፎ የሰካራም እጅ ያለ ንጽህና በድፍረት ይጨብጠዋል። 2/ ስዕል አድህኖው በየመጠጥ ቤቱ እየወደቀ ይረገጣል። ከቆሻሻ ጋር ተጠርጎ ይጣላል። 3/ በስሙ ታቦት መቀረጽ ሲገባው የሚያሰክር መጠጥ ሆኖ ስሙን ለማርከስ ተሰርቷል 4/ ኢትዮጵያ ከሰማዕቱ የምታገኘውን ክብርና ጥበቃ ለማሳጣት በ1915 ዓ.ም ጣሊያኖች አቅድው አቋቋሙት። የሚገርመው መጠጡን የሚጠጣው የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ተከታዩ ነው። አንዳዴ እንደቀላል የምናያቸው ነገሮች ከፍተኛ የሆነ ጥፋቶች ናቸውና እንንቃ። ይህን ጽሁፍ ያነበበ ለነፍሱ ይወስን!
18 195
12
Last updated: 11.07.23
Privacy Policy Telemetrio