መቻል ወሳኝ ድል አሳክቷል !
በኢትዮጵያ ፕርሚየር ሊግ የሀያ አምስተኛ ሳምንት መርሐ ግብር መቻል ከሀዋሳ ከተማ ጋር ያደረጉትን ጨዋታ 3ለ2 በሆነ ውጤት ማሸነፍ ችለዋል።
የመቻልን የማሸነፊያ ግቦች ከነዓን ማርክነህ 2x እና አብዱ ሞታላቡ ከመረብ ሲያሳርፉ ለሀዋሳ ከተማ ዓሊ ሱሌይማን 2x አስቆጥሯል።
ኤርትራዊው የሀዋሳ ከተማ የፊት መስመር ተጨዋች ዓሊ ሱሌይማን በውድድር አመቱ ያስቆጠራቸውን የሊግ ግቦች አስራ አምስት አድርሷል።
መቻል ተከታታይ ሶስተኛ ድሉን በማስመዝገብ ከሊጉ መሪ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ያለውን የነጥብ ልዩነት ወደ ሶስት ማጥበብ ችለዋል።
የሊግ ደረጃቸው ምን ይመስላል ?
2️⃣ መቻል :- 50 ነጥብ
1️⃣0️⃣ ሀዋሳ ከተማ :- 33 ነጥብ
ቀጣይ ጨዋታ ምን ይመስላል ?
አርብ - መቻል ከ ሻሸመኔ ከተማ
እሁድ - ሀድያ ሆሳዕና ከ ሀዋሳ ከተማ
@tikvahethsport @kidusyoftaheShow more ...