Best analytics service

Add your telegram channel for

  • get advanced analytics
  • get more advertisers
  • find out the gender of subscriber
Category
Channel location and language

audience statistics TIKVAH-ETHIOPIA

ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።  @tikvahuniversity   @tikvahethAfaanOromoo   @tikvahethmagazine   @tikvahethsport   @tikvahethiopiatigrigna   #ኢትዮጵያ  
Show more
1 353 197-178
~253 514
~19
19.74%
Telegram general rating
Globally
250place
of 78 777
1place
of 396
In category
6place
of 2 347

Subscribers gender

Find out how many male and female subscibers you have on the channel.
?%
?%

Audience language

Find out the distribution of channel subscribers by language
Russian?%English?%Arabic?%
Subscribers count
ChartTable
D
W
M
Y
help

Data loading is in progress

User lifetime on the channel

Find out how long subscribers stay on the channel.
Up to a week?%Old Timers?%Up to a month?%
Subscribers gain
ChartTable
D
W
M
Y
help

Data loading is in progress

Since the beginning of the war, more than 2000 civilians have been killed by Russian missiles, according to official data. Help us protect Ukrainians from missiles - provide max military assisstance to Ukraine #Ukraine. #StandWithUkraine
66 539
35
78 594
34
5
0
80 628
0
" ችግሩ በሚባለዉ ደረጃ የተጋነነ ባይሆንም ጊዜያዊ እርምጃ ለመዉሰድ እንቅስቃሴ ጀምሬያለሁ " - የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ትምህርት ቢሮ ከሰሞኑ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ባሉ መምህራን ማሰልጠኛ ኮሌጆች ለመማር የተመደቡ ዕጩ መምህራን ሁሉም በሚባል መልኩ ትምህርታቸዉን በፋይናንስ እጥረት እየተማሩ አለመሆኑን የደቡብ ኢትዬጵያ ክልል መምህራን ማህበር ለቲክቫህ ኢትዮጵያ መግለጹ ይታወሳል። ወንዶች ትምህርት መማር ሲገባቸው የቀን ስራ እየሰሩ እንደሆነና ሴቶችም ላልተፈለገ ችግር መጋለጣቸውን ጠቁሞ ነበር። ተማሪዎቹ በ2015 ዓ/ም ወደ ኮሌጆች ሲገቡ ከመንግስት የሚሰጣቸዉ 450 ብር በቂ እንዳልሆነ እየታወቀ ቢጀመርም እስካሁን አለመስተካከሉንና ለዚህም በተከታታይ ደብዳቤ መጠየቁን ማህበሩ መግለጹ አይዘነጋም። ጉዳዩን በተመለከተ የክልሉ ትምህርት ቢሮ አስተያየቱን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ሰጥቷል። የቢሮው ምክትል ሀላፊ ዶ/ር ታምራት ይገዙ ፤ " ጉዳዩ በተባለዉ ልክ የተጋነነ ባይሆንም የተወሰነ ችግር መኖሩን አውቀን እየሰራንበት ነው " ብለዋል። " ለችግሩ የአጭር ጊዜ መፍትሄ ለመስጠት እንቅስቃሴ ጀምረናል " ያሉት ሀላፊው " አሁን ላይ ተማሪዎቹ ያለባቸዉን የቤት ኪራይ ችግር ለማቅለል ከዲላ እና ከአርባምንጭ ዩኒቨርሲቲዎች ጋር መነጋገር ጀምረናል " ብለዋል። ከዲላ ዩኒቨርሲቲ ጋር ጥሩ መግባባት ላይ መደረሱን የገለጹት ዶ/ር ታምራት ከአርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ ጋርም ሂደቱ ጥሩ መሆኑን አመልክተዋል። " በቋሚነት ችግሩን ለማስተካከል እየሰራን ነው። ምናልባትም ለሚቀጥለዉ አመት ሲመጡ የሚከፈላቸዉ ገንዘብም ይጨምራል ብዬ አስባለሁ " ሲሉ ገልጸዋል።
Show more ...
72 629
0
#DStvEthiopia 💥 አንድም ጎል ፣ አንድም ደቂቃ እንዳያመልጣችሁ! 👉 ዛሬውኑ ደንበኝነትዎን ያራዝሙ ፣ ሁሉንም ጨዋታ በላቀ ጥራት ይመልከቱ! የዲኤስቲቪ አገልግሎቶችን ለማግኘት ከታች ያለውን የMyDStv Telegram bot ሊንክ ይጫኑ ወይም *9299# ይደውሉ! 👇
63 206
0
#Big5Ethiopia ቢግ ፋይቭ ኮንስትራክት ኢትዮጵያ አውደ ርዕይ ያካተተው የሲፒዲ ነጥብን የሚያስገኘው መድረክ ስድስት የሙያ ዘርፎችን የያዘ ነው። እነዚህም ቴክኖሎጂ፣ የፕሮጀክት አስተዳደር፣ አርክቴክቸርና ንድፍ፣ ዘላቂነት(ሰስተነብሊቲ)፣ ምህንድስና እና መሠረተ ልማት ናችው። ሁሉም ውይይቶች በየራሳቸው ብቁ ባለሙያዎች የሚመሩ ሲሆን፣ ፋይዳ ያላቸው እይታዎችንና አመለካከቶችን ያጋራሉ። የውሃ አቅርቦት መሠረተ ልማት ፕሮጀክቶች፣ ሞጁላር ግንባታ በዲጅታል ንድፍ ልምምድ ውስጥ፣ የመገኛ ቦታ(geospatial) ቴክኖሎጂና ቢም እንዲሁም አርክቴክቸር በከተማ ቅየሳ ውስጥ ያለው ሚና፣ ከሚዳሰሱ ርዕሶች መካከል ይገኛሉ። በነጻ ለመጎብኘትና ለመታደም አሁኑኑ ይመዝገቡ፡- የሁነቱን የቴሌግራም ቻናል ይቀላቀሉ፡-
Show more ...

animation.gif.mp4

70 710
0

file

197 636
123
#ቡሬ ➡️ “ 15 ተፈናቃዮች ናቸው በሚሊሻ የተወሰዱት ” - በአማራ ክልል የሚገኙ የወለጋ ተፈናቃዮች ➡️“ በቡሬ በኩል ስላለው መረጃ የለኝም ” - አቶ ኃይሉ አዱኛ በ2013 ዓ/ም ከኦሮማያ ክልል በአማራ ክልል ቡሬ ፣ ቻግኒ ፣ ፍኖተ ሰላም ፣ ባሕር ዳር የነበሩ ተፈናቃዮች ሰሞኑን ወደ ወለጋ ለመመለስ እየተጓዙ በነበረበት ወቅት ሰንቶም ቀበሌና ጣቦ የገጠር ከተማ ላይ ድንገተኛ ችግር እንደገጠማቸው አሳውቀዋል። ተፈናቃዮቹ ለቲክቫህ በሰጡት ቃል ፣ “ እየሄድን እያለ ሶንቶምና ጣቦ ላይ አደጋ አጋጠመን። የሕዝብ ማዕበል መጣብን። ኬላ ላይ ተይዘን በ1ዐ ተሽከርካሪዎች የተሳፈርን ተፈናቃዮች አወረዱን እና ተሰቃየን በጣም ” ብለዋል። “ ወጣቶች ድንጋይ፣ መሳሪያ ይዘው (ያልያዙት መሳሪያ የለም) ወጡ፣ ልክ አሸባሪ እንደሄደ እንጂ ተፈናቃይ አልመሰልናቸውም። ‘ከዚህ ቀደም በጦርነት ሲሳተፉ የነበሩ ናቸው’ እየተባለ ተፈናቃዮቹ እየተመረጡ ተያዙ ” ነው ያሉት። “ 15 ተፈናቃዮች በሚሊሻ ተወስደዋል ፤ ሊገድሏቸው ሲሉ መከላከያ ወደ ካምፕ ወስዷቸዋል። ቀሪዎቹ ጫካ አድረን ወደ ። በድንጋይ የተመቱ አሉ። ሰዎቹ ' እንደምትመጡ ማወቅ ነበረብን ጠብ እንዳንፈጥር ' ነው ያሉት ” ሲሉ ተናግረዋል። ተፈናቃዮቹን ወደ ምሥራቅ እና ሆሮ ጉድሩ ወለጋ ሀገር መከላከያ አጅቦ ሊመልሳቸው ፣ የወለጋ ኃላፊዎች ደግሞ ሊቀበሏቸው ቅድሚያ ቢነገራቸውም የሸኟቸው ሚሊሻዎች መሆናቸውን ተፈናቃዮቹ አስረድተዋል። ሚሊሻዎቹ ከዓባይ ወደዛ ለመሻገር ስላልቻሉ፣ የወለጋ ዞኖች ኃላፊዎችም ‘ ትዕዛዝ አልተሰጠንም ’ በማለት ለመቀበል ፈቃደኛ ባለመሆናቸው ከሞት አምልጠው ወደ ቡሬ ለመመለስ መገደዳቸውን ገልጸዋል። የአማራ ክልል ለጉዳዩ ምላሽ እንዲሰጥ ያደረግነው ጥረት አልተሳካም። ለምን ጥበቃ እንዳልተደረገላቸው ጥያቄ የቀረበላቸው የኦሮሚያ ክልል ኮሚዩኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ አቶ ኃይሉ አዱኛም፣ “ በቡሬ በኩል ስላለው መረጃ የለኝም ” ነው ያሉት። “ ደብረ ብርሃን፣ ወሎ ካምፕ ያሉትን ቅድሚያ ተሰጥቶ በ1ኛው ዙር 1,600፣ በ2ኛው ከ400 በላይ ሰዎች ተመልሰዋል” ሲሉ አስታውሰው ፣ “ በሶስተኛው ዙር ለመመለስ ደግሞ ከአማራ ክልል መንግስት ጋር በቅንጅት እየሰራን ነው ” ብለዋል።
Show more ...
176 987
26
#KAF_Boutique ኦሪጂናል አልባሳት እና ጫማዎች ከ15% ቅናሽ ጋር ! ለተወሰነ ጊዜ የሚቆይ ቅናሽ ላይ ነን። ለበለጠ መረጃ፦ ስልክ ቁጥር ፡ 251944390123 አድራሻ፦ መገናኛ ቤተልሄም ፕላዛ ግራውንድ ሱቅ ቁጥር 08 ወይም ይደውሉልን ያሉበት ቦታ እናደርሳለን። 👉Telegram: 👉Instagram: 👉Facebook:
157 997
22
#ሴጅ_ማሰልጠኛ የፊታችን ሰኞ ግንቦት 12/2016 ዓ.ም 13ኛ ዙር የድህረ-ገፅ እና ሞባይል መተግበሪያ ማበልፀግ ስልጠና ይጀምራል። 👉 100 % በተግባር የተደገፈ ስልጠና 👉 መሠረታዊ ኮምፒውተርና ፕሮግራሚንግ ትምህርቶችን አካቶ የሚሰጥ 👉 Front-end እና Back-end በአንድ ላይ እስከ Deployment ያካተተ 👉 በተግባር ድህረ ገጾችን እና ሞባይል መተግበሪያዎችን እያበለፀጉ የሚሰለጥኑበት 👉 የሥራ ላይ ስልጠና (Internship) የተመቻቸለት ስልክ፦ NaN / NaN አድራሻ፦ ፒያሣ ቸርችል ጎዳና ኤልያና ሆቴል 2ኛ ፎቅ
172 071
35
#USA አሜሪካ በአማራ ክልል ይንቀሳቀሳሉ ያለቻቸው የፋኖ ኃይሎች " ውይይትን አልቀበልም " ማለታቸውን በመግለጽ ይህ " ለራሳቸውም አይጠቅማቸውም " አለች። ሀገሪቱ ይህን ያለችው በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር በሆኑት ኢርቪን ማሲንጋ አማካኝነት ነው። አምባሳደሩ ፤ " በአማራ ክልል ውስጥ ውጊያ እያደረጉ የሚገኙት እራሳቸውን ' ፋኖ ' ብለው የሚጠሩ ኃይሎች ' ውይይትን አንቀበልም ' ማለታቸው ለራሳቸውም አይጠቅማቸውም " ብለዋል። ከመንግስት ጋር በታንዛንያ የሰላም ንግግር ሲያደርጉ የቆዩት የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት (OLA) ተዋጊዎችን " በድርድር ተስፋ ሳትቆርጡ ፤ መተማመንን ለመገንባት ጥረት አድርጉ " ብለዋቸዋል። አሜሪካ ይህን ያለችው ዛሬ ግንቦት 7 ቀን 2016 ዓ/ም ኢትዮጵያን በተመለከተ የምትከተለውን ፖሊሲ አስመልክቶ በአምባሳደሯ በኩል ባስተላለፈችው መልዕክት ነው። በአዲስ አበባ ፤ መርካቶ አካባቢ በሚገኘው የቀድሞ የአሜሪካን ግቢ በነበረ መርሀ ግብር የአሜሪካ አፍሪካ ቀንድ ልዩ ልዑክ ማይክ ሐመርን ጨምሮ ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተው ነበር። Video Credit : US Embassy Addis Ababa / Ethiopia Insider
Show more ...

file

240 707
229
224 979
45
" ሞተዋል !! " - ዓለም አቀፉ ፍ/ቤት በዓለም አቀፍ ፍርድ ቤት ይፈለጉ የነበሩ የመጨረሻው ሁለት የሩዋንዳ የዘር ፍጅት ተከሳሾች መሞታቸውን ማረጋገጡን በጉዳዩ ላይ የተቋቋመው ችሎት አስታውቋል። ርያንዱካዮ በሚል ስም ብቻ የሚጠራው እና ቻርለስ ሲኩብዋቦ በሩዋንዳ የዘር ፍጅት ጉዳይ በተቋቋመው ዓለም አቀፍ ችሎት ሲፈለጉ የነበሩ የመጨረሻዎቹ ተከሳሾች ናቸው። በብሔራዊ ደረጃ ግን አሁንም ድረስ ከ1 ሺህ በላይ ተጠርጣሪዎች በመፈለግ ላይ ናቸው። 2ቱ ግለሰቦች ከ30 ዓመት በፊት 800 ሺ ቱትሲዎችን እና ለዘብተኛ ሁትዎችን በጨረሰው የዘር ፍጅት ላይ ተሳትፎ አላቸው በሚል ለሩዋንዳ በተቋቋመው ዓለም አቀፍ የወንጀል ችሎት በእ.አ.አ 1995 ክስ ቀርቦባቸው ነበር። ሲኩብዋቦ በእ.አ.አ 1998 በቻድ መሞቱን እና በዛው መቀበሩን እንዲሁም ርያንዱካዮ ደግሞ ወደ ኮንጎ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ከሸሸ በኋላ ከዛም ወደ ዛየር ተሻግሮ ኪንሻሳ ላይ በ1998 ሕይወቱ ማለፉን ፍ/ቤቱ አስታውቋል። በሩዋንዳው የዘር ፍጅት ጉዳይ በዓለም አቀፉ ፍ/ቤት ሲፈለጉ የነበሩ ተከሳሾች ሁሉ መለየታቸውንም ችሎቱ አስታውቋል።
Show more ...
246 404
46
198 426
47
🇪🇹 የፖለቲካ ፓርቲዎች ምን ይላሉ ? 🇪🇹 " ... አሁንም ቢሆን ለያዥ እና ገናዥ አስቸጋሪ የሆነው የመንግስት አቋም ነው " - መረራ ጉዲና (ፕሮፌሰር) የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ ( ) ሊቀመንበር መረራ ጉዲና (ፕ/ር) በሀገራችን ጉዳይ ላይ ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ጋር ቆይታ አድርገዋል። Q. በተለያዩ ቦታዎች ያለውን የጸጥታው ችግር እንዴት ትገመግሙታላቹ ? መፍትሄውስ ምንድን ነው ? ፕ/ር መረራ ጉዲና ፦ " ብሔራዊ እርቅ እና ብሔራዊ መግባባት የሚባለውን እኮ ከኢህአዴግ መጀመሪያ ዓመት ጀምሮ እስከ 30 ዓመታት ስንጠይቅ ቆይተናል። አሁንም ቢሆን መልክ አልይዝ እያለ ያስቸገረው / ለያዥና ለገናዥ አስቸጋሪ የሆነው የመንግስት አቋም ነው። ስልጣንን በMonopoly መያዝ ከንጉሱ ዘመን ጀምሮ እንደ ባህል ተይዟል። አሁንም ቀጥሏል። የኢትዮጵያ መሪዎች ከዛ አልወጣ አሉ። ውጤቱ ደግሞ የታወቀ ነው።  ደርግ ወጣቶችን ጨፍልቆ ነው የሄደው ፤ ኢህአዴግ ለ27 ዓመታት አገሪቱን ቀላል ያልሆነ ቀውስ ውስጥ ከቷት ነው ጡረታ የወጣው ፤ ብልጽግናም በባሰ መንገድ ይህንኑ ሁኔታ እየተከተለ ነው። የኢትዮጵያ ጸጥታ ሁኔታ ' ከድጡ ወደ ማጡ ' ተብሎ የሚገለጽበት ደረጃ ላይ ነው።  መፍትሄው ቁጭ ብሎ መወያዬት ነው። ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ፓለቲካ ወደ ፓለቲካ ማምጣት እጅግ በጣም አስፈላጊ ነው። " Q. በየጊዜው የንጹሐን ሕይወት በግፍ እየተቀጠፈ ነው። ከቦታ ቦታ ተንቀሳቅሶ መስራትም የሞት ጊዜን እንደማፋጠን ሆኖ ይስተዋላል።  መፍትሄ እንዲመጣ ምን እየሰራችሁ ነው ? ፕ/ር መራራ ጉዲና፦ " ለ30 ይሁን ለ6ቱ ዓመታት በዴሞክራሲ የሚደረገው ለውጥ በተለይ ዴሞክራሲያዊ ምህዳርን እንዲያሰፉ ደጋግመን ስንጠይቅ ነበር። አሁንም ያን መጠየቅ ቀጥለናል። ሜዳው / ምህዳሩ ግን በተቃራኒው እየጠበበ፣ አስቸጋሪ ሁኔታዎች በአገሪቷ ላይ እየተንሰራፉ የመጡበት ሁኔታ ነው ያለው። ምህዳሩ ካልሰፋ፣ ለዴሞክራሲ የሚደረገው ትግል መልክ ካልያዘ፣ ወጣቱንም ወደ ጫካ እየተገፋ የትም አያደርሰንም። " Q. ከመንግስት የሚደርስባችሁ ጫና ምንድን ነው ? ፕ/ር መረራ ጉዲና ፦ " ከኦነግ ቀጥሎ ከፍተኛ ጫና ያለበት የእኛ ፓርቲ ነው። ለምሳሌ የዛሬ 4 ዓመት ከ200 በላይ ቢሮዎች ነበሩን፤ አሁን ያሉን 3 ብቻ ናቸው። አባሎቻችን እና ይፈጸምባቸዋል።  ለምሳሌ ፦ የምሥራቅ ወለጋ የቢሮ ኃላፊ ከተወሰደ የት እንደገባ አላወቅንም 2 ዓመታት ሊሆነው ነው። የምሥራቅ ሸዋ የማዕከላዊ ኮሚቴ አባላችን ለዚያውም የዩኒቨርሲቲ የሕግ መምህር ታስሯል። አምቦ 4 ወጣቶች ታስረው 2 ሳምንታት ሆኗቸዋል። " Q. በተመለከተ ኢትዮጵያ በምን ደረጃ ትገኛለች ? መፍትሄውስ ? ፕ/ር መራራ ጉዲና ፦ " በኢትዮጵያ ታሪክ የተለዬ/የከፋ የሙስና ደረጃ ነው ያለው። መንግስትና ተቋማቱ የአንድ ቡድን ጉዳይ አስፈጻሚ ሆነው ሲዋቀሩ እንዲህ አይነት ሁኔታዎች ይፈጠራሉ። አሁንም መንግስት ተጠያቂነት ባለው መንገድ እንደገና ካልተዋቀረ በስተቀር፣ ከዚህ በሽታ የምንወጣበት መንገድ ያለ አይመስለኝም። Q. የኑሮ ውድነቱ ሕዝቡን በእጅጉ አማሮታል። ፓርቲያችሁ ለመንግስት ያላችሁ ግምገማን ቢያጋሩ ? ፕ/ር መረራ ጉዲና ፦ " ዜጎች እጅግ አስቸጋሪ ፣ ፈታኝ ሁኔታ ላይ ደርሰዋል። መንግስት አስፈላጊ እርምጃ እንዲወስድ በተደጋጋሚ ተይቀናል። መንግስት ግን ጆሮ ያለው አይመስልም። ችግሩ ግን እጅግ በጣም ፈታኝ ነው። " Q. በቀጣዩ ሀገራዊ ምርጫ ተመራጭ ሆኖ ለመቅረብ ዝግጅት እያደረጋችሁ ነው ? ፕ/ር መረራ ጉዲና ፦ " የፓለቲካ ምህዳር ለማግኘት የመገዳደል ፓለቲካው እንዲቆም እየጠየቅን ነው። ምርጫ ከዚያ በኋላ የሚመጣ ነው። ለነፃና ፍትሃዊ ምርጫ አስቻይ የሆነ ሁኔታ ኢትዮጵያ ውስጥ የለም። ትልልቆቹ አማራና ኦሮሚያ ክልሎች ጦርነት ውስጥ ናቸው። በዚህ ሁኔታ ምን አይነት ምርጫ እንደሚካሄ የምናየው ነው። መደራጀቱን ቀጥለናል። " ?
Show more ...
204 397
105
180 516
27
#KAF_Boutique ኦሪጂናል  አልባሳት እና ጫማዎች ከ15% ቅናሽ ጋር ! ለተወሰነ ጊዜ የሚቆይ ቅናሽ ላይ ነን። ለበለጠ መረጃ፦ ስልክ ቁጥር ፡ +251 94 439 0123 አድራሻ፦ መገናኛ ቤተልሄም ፕላዛ ግራውንድ ሱቅ ቁጥር 08 ወይም ይደውሉልን ያሉበት ቦታ እናደርሳለን። 👉Telegram: 👉Instagram: 👉Facebook:
187 314
21
BK  C  O  M  P  U  T  E  R S ማንኛውንም አይነት አዳዲስ ላፕቶፖች ዱባይ ዩዝድ ላፕቶፖች ዴስክ ቶፖችን ጨምሮ ከብዛት እና ከታላቅ ቅናሽ ጋር ያዘንላቹ መተናል። ለቢሮዎች ፣ ለተማሪዎች፣ለግሪፊክስ ዲዛይን ባለሙያዎች ፣ ለጌመሮች እንዲሁም ለጨረታ የሚሆኑ በጥራት እና በ ብዛት  ከ1 አመት ዋስትና ጋር እኛ ያገኛሉ። ለተጨማሪ መረጃ እና የላፕቶፕ አማራጮችን ለማየት የቴሌግራም ፔጃችንን Join ያድርጉ። Tg. Inbox አድራሻ አዲስ አበባ መገናኛ ሲቲ ሞል ከ መሰረት ደፋር ህንፃ አጠገብ 1 ፎቅ ላይ እንገኛለን ፤ NaN. NaN            we make IT easy!
171 118
25
ዮናታን ቢቲ ፈርኒቸር Yonatan BT Furniture የዘመናዊነት ተምሳሌት! አድራሻችን 1. ዊንጌት አደባባዩን ተሻግሮ: +251 995 27 2727 2. ፒያሳ እሪ በከንቱ : +251 957 86 8686 3. ሲ ኤም ሲ አደባባዩን አለፍ ብሎ: +251 993 82 8282 👉 Telegram:  👉 Facebook:  👉 TikTok: 👉 Instagram:
205 238
29
" በዝርፊያው ለጊዜው የተለያዩ የጦር መሳሪያዎችን ተወስደዋል " - የወልቂጤ ከተማ ሰላምና ፀጥታ ፅህፈት ቤት በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል፣ የወልቂጤ ከተማ ፖሊስ ጣቢያ ዝርፊያ እንደተፈጸመበት ተነግሯል። በፖሊስ ጣቢያው ላይ ዝረፊያ የተፈፀመው ሰኞ ለሊት 7፡40 ገደማ ነው። " በዝርፊያው ለጊዜው ተለይተው ያልታወቁ የተለያዩ የጦር መሳሪያዎችን ከፖሊስ ጣቢያው ተወስደዋል " ሲል የከተማው ሰላምና ፀጥታ ፅ / ቤት አሳውቋል። በተጨማሪም ከጣቢያው ተዘርፎ የነበረ ፓትሮል መኪና መንገድ ላይ መገኘቱን አመልክቷል። ፖሊስ ጣቢያው ታሽጎ የማጣራት ሂደት እየተከናወነ እንደሆን ገልጿል። ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የሸገር ኤፍ ኤም 102.1 ሬድዮ ጣቢያ ነው።
262 968
219
#ኮሬ ° " የንጹሀን ሞት ይቁም፤ገዳዮች ለፍትህ ይቅረቡልን !! " - የዳኖ ቀበሌ ነዋሪዎች ° " በግጭቱ ሁለት ሰዎች ሲጎዱ የአንደኛው ህይዎቱ አልፏል " - የኮሬ ዞን የሰላምና ጸጥታ ሀላፊዉ ተፈራ ቦንዶሮ በኮሬ ዞን ፤ ዳኖ ቀበሌ ከትናንት ጀምሮ የደረሰ በቆሎ ታጥቀው በመጡ አካላት በመጨፍጨፉ ምክንያት በተነሳው ግጭት የሰው ህይወት አልፏል። የአካባቢው ነዋሪዎች ይህ ድርጊት ታጥቀው ከምዕራብ ጉጂ ዞን ጋላናና ሱሮ ባርጉዳ ወረዳ ቀበሌያት ወደ ኮሬ ዞን ዘልቀው በገቡ አካላት ነው የተፈጸመው ብለዋል። እነዚሁ ታጣቂዎች " ከዚህ ቀደምም ከብቶች ሲነዱብን አርሶአደሮች ሲገደሉብን ቆይተዋል " ሲሉ ገልጸዋል። በዚህ አመት ብቻ ሰዎች መሞታቸውን አስረድተዋል። በመሆኑም " እነዚህን አካላት መንግስት አስታግሶ ለህግ / ለፍትህ ያቅርብልን ፤ የንጹሀን ሞት ይቁም ፤ ሰሚ በማጣታችን እሄዉ ዛሬም ግጭቱ ቀጥሏል " ብለዋል። በአካባቢው ያለዉ ተኩስም የታጠቁ አካላትን ወሰን አልፈዉና ወደመንደሩ ተጠግተዉ የጀመሩት ነው ሲሉ አስረድተዋል። ይህን ጉዳይ በተመለከተ ቃላቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የሰጡት የኮሬ ዞን የሰላምና ጸጥታ ሀላፊዉ ተፈራ ቦንዶሮ ፥ (ቃላቸውን በሰጡበት ሰዓት / ከሰዓት ) አካባቢው ላይ ከባድ ተኩስ እንደነበር ገልጸዋል። ግጭቱን ለማርገብ ርብርብ ላይ በመሆናቸዉ ምላሽ ለመስጠት አይመችም ቢሉም ቆይተዉ የተብራራ ምላሽ ሰጥተዋል። ከምዕራብ ጉጂ ዞን የመጡ ታጣቂ ሀይሎች አካባቢው በመመንጠርና የበቆሎ ማሳዎችን በመጨፍጨፋቸው ከአካባቢው አርሶ አደሮች ጋር ግጭት ውስጥ መግባታቸውን ገልጸዋል። በግጭቱ አንድ ሰው ፤ አንድ ሰው ቆስሏል ብለወል። ግጭቱን በቀሰቀሱት በኩል የደረሰ ጉዳት ስለመኖሩ የሚያዉቁት ነገር እንደሌለ ገልጸው አሁን ላይ አካባቢዉ መረጋጋቱን ተናግረዋል። ቲክቫህ ኢትዮጵያ ለዘላቂ ሰላም ምን ታስቧል ? ሲል ጠይቋል። እሳቸውም ፤ ከአካባቢው በተወሰነ ርቀት ላይ የሀገር መከላከያ ሀይሎች እንደሚኖሩና ከሚቆጣጠሩት ቦታ በተጨማሪ የታጠቁ ሀይሎች የሚመጡበትን መንገድ እንዲቆጣጠሩ ለመነጋገር ማሰባቸዉን ገልጸዉ ይህ ግን በመከላከያው ፈቃድና የስምሪት ሁኔታ የሚወሰን ነው ብለዋል። ግጭቱ ያለበት የኮሬና ጉጂ ማህበረሰብ መሀከል በአካባቢዉ ባህል መሰረት የእርቅ ስርዓት በተደጋጋሚ ቢካሄድም ዕርቁ ውጤታማ ሳይሆን መቅረቱን ለማወቅ ችለናል። ቲክቫህ ኢትዮጵያ ፤ በምዕራብ ጉጂ ዞን በኩል ምላሽ ለማግኘት ሙከራ ቢያደርግም አልተሳካም ፤ ከዚህ ቀደምም ሙከራ ቢደረግም ምላሽ ሰጪ አልተገኘም። አሁንም ምላሽ አለኝ የሚል ምላሹን መስጠት ይችላል።
Show more ...
250 791
40
235 757
998
#Ethiopia የገጠር መሬትን በሸጠ ወይም በገዛ ማንኛውም ሰው ላይ እስከ 5 ዓመት የሚደርስ ፅኑ እስራት ቅጣት የሚጥል አዋጅ በተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ጸድቋል። አዲሱ አዋጅ የግል ፣ የወል ወይም የመንግስት ይዞታን በህገ ወጥ መንገድ ወርሮ ለተገኘ ሰው ተመሳሳይ የእስራት ቅጣት ደንግጓል። ዛሬ የጸደቀው አዋጅ ከ18 ዓመት በፊት የወጣውን የገጠር መሬት አስተዳደር እና አጠቃቀም አዋጅን ያሻሻለ ነው። አርሶ አደሮች፣ አርብቶ አደሮች እና ከፊል አርብቶ አደሮች በመሬት ላይ ያላቸውን መብቶች አሻሽሏል የተባለ ሲሆን የሴቶች እና ድጋፍ የሚሹ ሰዎችን የመሬት ተጠቃሚነት መብት ያረጋገጡ ድንጋጌዎችንም አካትቷል ተብሏል። አዋጁ ምን ይዟል ? - ማንኛውም ሰው መሬት የሸጠ ወይም የገዛ እንደሆነ፤ ከ100 ሺህ እስከ 200 ሺህ ብር ወይም ከ1 ዓመት እስከ 5 ዓመት በሚደርስ ፅኑ እስራት ወይም በሁለቱም ሊቀጣ ይችላል። NB. በኢፌዲሪ ሕገ መንግስት መሰረት " መሬት የማይሸጥ፣ የማይለወጥ የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች የጋራ ንብረት ነው "። ሕገ መንግስቱ የገጠርም ሆነ የከተማ መሬት የባለቤትነት መብትን የሰጠው " ለመንግስት እና ለህዝብ " ነው። - የወል ወይም የመንግስት ይዞታን በህገ ወጥ መንገድ የወረረ ማንኛውም ሰው፤ ከ1 ዓመት እስከ 5 ዓመት በሚደርስ ፅኑ እስራት አሊያም ከ30 ሺህ እስከ 100 ሺህ ብር ቅጣት ይጣልበታል። - የወል ወይም የመንግስት ይዞታ ላይ ጉዳት አድርሶ የተገኘ ማንኛውም ሰው፤ ከ3 ዓመት እስከ 7 ዓመት በሚደርስ ፅኑ እስራት ወይም ከ50 ሺህ እስከ 150 ሺህ ብር ይቀጣል። - ባልተፈቀደ ቦታ ላይ ማንኛውንም ግንባታ የሰራ ወይም እንዲሰራ የፈቀደ ሰው ደግሞ በአዲሱ አዋጅ መሰረት ከ1 ዓመት እስከ 3 ዓመት በሚደርስ እስራት አሊያም ከ25 ሺህ እስከ 50 ሺህ ብር ይቀጣል። - ከመሬት አጠቃቀም ዕቅድ ውጪ ይዞታውን ጥቅም ላይ አውሎ የተገኘ ሰው ከ1 ዓመት እስከ 3 ዓመት በሚደርስ እስራት አሊያም ከ25 ሺህ እስከ 50 ሺህ ብር ይቀጣል። - ሀሰተኛ የመሬት ይዞታ ማስረጃ ያቀረበ ባለይዞታ እንዲሁም ማስረጃ የሰወረ ወይም የተሳሳተ ማስረጃ የሰጠ ባለሙያ ላይ የሚጣለው እስራት ከላይ እንዳሉት የህግ ጥሰቶች ተመሳሳይ ቢሆንም የገንዘብ ቅጣቱ መነሻ ግን ወደ 20 ሺህ ብር ዝቅ ብሏል። ምንጭ፦ የገጠር መሬት አስተዳደርና አጠቃቀም አዋጅ (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር)
Show more ...
235 522
1 152
ባልተገደበ የፕሪሚየም ጥቅላችን ከወዳጅ ዘመድ ጋር ግንኙነትዎ ሳይቋረጥ የስራ እንቅስቃሴዎ ሳይገደብ ዘና ብለው ይጠቀሙ ! በሳምንታዊና በወርሃዊ ያልተገደበ ፕሪሚየም አማራጮች የቀረቡትን ጥቅሎች በቴሌብር  ሱፐርአፕ፣ በማይ ኢትዮቴል፣ አርዲ ቻትቦት ወይም በ*999# ያገኟቸዋል!
222 345
2
258 771
467
Last updated: 11.07.23
Privacy Policy Telemetrio